Oromo Special Zone High Court

Oromo Special Zone High Court It is An Official Page Where We Communicate the Work of the Court to The Public.

31/05/2026
30/05/2026
የደዋ ጨፋ ወረዳ ፍ/ቤት ለከሚሴ ከተማ ቀበሌዎች የባህል ፍርድ ቤት ዳኞች  እና ጸሀፊዎች ስልጠና መስጠት ጀመረ።    ከሚሴ:ግንቦት 22/2018 ዓ.ም (የኦሮሞ ብሄ/ብ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት)...
30/05/2026

የደዋ ጨፋ ወረዳ ፍ/ቤት ለከሚሴ ከተማ ቀበሌዎች የባህል ፍርድ ቤት ዳኞች እና ጸሀፊዎች ስልጠና መስጠት ጀመረ።

ከሚሴ:ግንቦት 22/2018 ዓ.ም (የኦሮሞ ብሄ/ብ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት)

የደዋ ጨፋ ወረዳ ፍ/ቤት ለከሚሴ ከተማ ቀበሌዎች ለተመረጡ የባህል ፍርድ ቤት ሽማግሌዎ እና ጸሀፊዎች ስልጠና እየሰጠ ይገኛል።

በስልጠናው ላይ የኦሮሞ ብሄ/ብ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ አሊ መሀመድ፣የደዋ ጨፋ ወረዳ ፍ/ቤት ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ መሀመድ ፋሪስ፣የደዋ ጨፋ ወረዳ ፍ/ቤት ዳኞች፣
የከ/ከተማ ፍትህ ጽ/ቤት ሀላፊ፣የከተማ ምክትል ከንቲባ፣
ዋና አፈጉባኤ ፣የህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት ሀላፊ ፣የሴቶችና ህጻናት ጽ/ቤት ሀላፊ፣ከተማ የሰባቱም ቀበሌ የባህል ፍርድ ቤት
ዳኞች እና ጸሀፊዎች ፣የሀገር ሽማግሌዎች፣አባገዳና ሀደሲንቄዎች ይገኙበታል።

የደዋ ጨፋ ወረዳ ፍ/ቤት ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ መሀመድ ፋሪስ የእንኳን ደህና መጣህሁ መልዕክትና ስለሚሰጡት ስልጠና አስፈላጊነት አጭር ገለጻ በመስጠት የመክፈቻ ንግግር አድርገዋል።

የኦሮሞ ብሄረሰብ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አቶ አሊ መሀመድ የአማራ ክልል ህብረተሰብ የባህል ሽምግልና ስርዓትን ለብዙ ዘመናት ሲጠቀምበት እንደነበር በማብራረት ፣እንደዚሁም የኦሮሞ ብሄረሰብ ዞን ህብረተሰብም ይህንኑ ስርዓት እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ እየተጠቀመበት ያለ መሆኑን በመግለጽ ፣የአብክመ ጠቅላይ ፍ/ቤት የባህል ፍርድ ቤት ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 298/2017 እና ይህንን አዋጅ ለማስተግበር ባወጣው መመሪያ ቁጥር 23/2018 መሰረት ስልጠናዉ የሚሰጣቸዉ መሆኑን፣ ለባህል ፍርድ ቤት ዳኛ በመሆን የተመረጡት አካላት የህዝቡና የመንግስት አደራ የተጣለባቸዉ መሆኑን ተገንዝበዉ ስልጠናዉን በአግባቡ መከታተል እንዳለባቸዉ አስገንዝበዋል።

የአርጡማ ፉርሲ ወረዳ ፍ/ቤት ለተመረጡ  የባህል ፍርድ ቤት ሽማግሌዎች  እና ጸሀፊዎች ስልጠና መስጠት ጀመረ።    ከሚሴ:ግንቦት 21/2018 ዓ.ም (የኦሮሞ ብሄ/ብ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት)  ...
29/05/2026

የአርጡማ ፉርሲ ወረዳ ፍ/ቤት ለተመረጡ የባህል ፍርድ ቤት ሽማግሌዎች እና ጸሀፊዎች ስልጠና መስጠት ጀመረ።

ከሚሴ:ግንቦት 21/2018 ዓ.ም (የኦሮሞ ብሄ/ብ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት)

የአርጡማ ፉርሲ ወረዳ ፍ/ቤት በባህል ፍርድ ቤት ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 298/2017 እና ይህንን አዋጅ ለማስተግበር በወጣው መመሪያ ቁጥር 23/2018 መሰረት በወረዳዉ ለባህል ፍርድ ቤት ሽማግሌ እና ጸሀፊ በመሆን ለተመረጡ አካላት የስልጠና ማስጀመሪያ ፕሮግራም በመሠጠት ላይ ይገኛል።

የኦሮሞ ብሄረሰብ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አቶ አሊ መሀመድ የስልጠናው አስፈላጊነት አስመልከቶ መክፈቻ ንግግር አድረገዋል።

ስልጠናዉ ለሁለት ተከታታይ ቀናት የሚሰጥ ሲሆን፣
በስልጠናው ላይ የኦሮሞ ብሄረሰብ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ሃላፊ አቶ ጀማል ሀሰን፣የአ/ፉርሲ ወ/ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አህመድ ኢብራሂም፣የጨ/ሮቢት ከተማ አ/ር ዋና አ/ጉባዔ አቶ አህመድ ግዛውና ሌሎችም የፕሮግራሙ ታዳሚዎች ይገኙበታል።

Ergaa Baga Geessanii!የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት!Manni Murtii Ol'anaa Go/Sa/Oromoo Hordoftoota amantaa Kiristaanaa Abbootii seera...
26/05/2026

Ergaa Baga Geessanii!
የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት!

Manni Murtii Ol'anaa Go/Sa/Oromoo
Hordoftoota amantaa Kiristaanaa
Abbootii seeraa,muudamtoota, hojjettoota bulchiinsaa, abbotii dhimmaa fi qooda fudhattoonni manneen murtii Go/Sa/Oromoo keessatti hojjetan hundaaf baga ayyaana Faasikaa bara 2018 geessan jechaa,
Ayyaanichi kan Nagaa, kan jaalalaa fi kan milkii isiniif haa ta’u jechuun hawwii qabu ibsa.

Ayyaana Gaarii!

kabajamoo obbo Ali Mahammad (pirezidanti)

Manni Murtii Ol'anaa Go/Sa/Oromoo

የኦሮሞ ብሄ/ብ ዞን ከፍ/ፍ/ቤት በዞናችን ፍርድ ቤቶች የምታገለግሉ የክርስትና እምነት ተከታይ ዳኞች፣ ተሿሚዎች፣ የአስተዳደር ሰራተኞች፣ ባለጉዳዮች እና ባለድርሻ አካላት፣ እንኳን ለ 2018 ዓ.ም ለ ፋሲካ በዓል አደረሳችሁ! በማለት
በዓሉ የሰላም፣የፍቅር እና የስኬት እንዲሆንላችሁ ይመኛል!

መልካም በዓል

ክቡር አቶ አሊ መሀመድ (ፕሬዝዳንት)
የኦሮሞ ብሄ/ብ ዞን ከፍ/ፍ/ቤት

22/05/2026
21/05/2026

Address

Kemise

Opening Hours

Monday 09:00 - 17:00
Tuesday 09:00 - 17:00
Wednesday 09:00 - 17:00
Thursday 09:00 - 17:00
Friday 09:00 - 17:00

Telephone

+251335540249

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Oromo Special Zone High Court posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share