Karat Town Gov't Communication Affairs Office ካራት ከተማ አስ/ር መንግስት ኮ/ጉ/ ጽ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Konso
  • Karat Town Gov't Communication Affairs Office ካራት ከተማ አስ/ር መንግስት ኮ/ጉ/ ጽ/ቤት

Karat Town Gov't Communication Affairs Office ካራት ከተማ አስ/ር መንግስት ኮ/ጉ/ ጽ/ቤት The Communication or Bridge of People to Government in order to Develope Ethiopia.

‎ከሆላንድ የመጡ እንግዶች በኮንሶ ዞን የማህበረሰብ አቀፍ ቱሪዝም እንቅስቃሴዎችን ጎበኙ፣‎‎ካራት፣ ነሐሴ 23/2018 ዓ.ም (ኮንሶ ዞን ኮሙኒኬሽን)‎‎ከሆላንድ የመጡ በአፍሪካ የማህበረሰብ ...
30/08/2026

‎ከሆላንድ የመጡ እንግዶች በኮንሶ ዞን የማህበረሰብ አቀፍ ቱሪዝም እንቅስቃሴዎችን ጎበኙ፣

‎ካራት፣ ነሐሴ 23/2018 ዓ.ም (ኮንሶ ዞን ኮሙኒኬሽን)

‎ከሆላንድ የመጡ በአፍሪካ የማህበረሰብ አቀፍ ቱሪዝም (Community-Based Tourism) ፕሮግራም ማናጀርና ደጋፊዎች፣ ከክልል፣ ከዞን፣ ከወረዳና ከከተማ የቱሪዝም ተቋማት የተውጣጡ ባለሙያዎችና አመራሮች በኮንሶ ዞን ካራት ከተማ የማህበረሰብ አቀፍ ቱሪዝም የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችንና የቱሪዝም ሀብቶችን ጎበኙ።

‎ጎብኚዎቹ ካራት ከተማ ሲደርሱ በኮንሶ ዞን ዋና አስተዳደር ጽ/ ቤት ኃላፊ አቶ ደመላሽ ጎንዲሼ፣ የካራት ከተማ አስ/ር ከንቲባን ጨምሮ የከተማው አመራሮች ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።

‎አቀባበሉን ተከትሎም ወደ ጋሞሌ አምባ መንደር በመጓዝ በፕሮግራሙ የተካተቱ የቱሪዝም ምርቶችን፣ የአካባቢውን ባህላዊ ሀብቶችና የማህበረሰቡን ተሳትፎ በማሳያ ደረጃ ተመልክተዋል።

‎የማህበረሰብ አቀፍ ቱሪዝም ፕሮግራሙ በኮንሶ ዞን ያሉ የቱሪዝም ሀብቶችን በመለየት፣ በማደራጀትና ለቱሪስት ገበያ በተስማሚ መልኩ በማቅረብ ማህበረሰቡ ከዘርፉ የሚገኘውን ኢኮኖሚያዊ ጥቅም በቀጥታ እንዲያገኝ ያለመ ነው።

‎በካራት ከተማ ባህልና ስፖርት ጽ/ቤት የቱሪዝም ባለሙያ አቶ ኦላታ ኦርካይዶ እንደገለጹት፣ ከዚህ በፊት በፕሮግራሙ የቅድመ ሁኔታ መረጃ የማሰባሰብና የማፒንግ ሥራዎች ተከናውነዋል።

አቶ ኦላታ ጨምረው ከማህበረሰቡ ጋር የተፈጠረው ቀጥተኛ መግባባትና ጎብኚዎችን በፈገግታ መቀበል የኮንሶ የቱሪዝም ሀብት አካል የሆነውን የእንግዳ ተቀባይነት በግልጽ ያሳያል ብለዋል።

‎በዚህም በጋሞሌ አምባ መንደር፣ በካራት ከተማና በኮንሶ ዞን ለቱሪስት ገበያ ሊቀርቡ የሚችሉ የቱሪዝም ምርቶችና እንቅስቃሴዎች ተለይተው በአጭር ፓኬጅ መልክ መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።

‎የተዘጋጁት መረጃዎች በክልሉ በኩል ለፌዴራል የቱሪዝም ሚኒስቴር መቅረባቸውን ጠቁመው፣ የዛሬው ጉብኝት ዋና ዓላማ በሰነድ የተዘጋጁት የቱሪዝም ምርቶች በመሬት ላይ በተግባር መኖራቸውን ማረጋገጥ፣ ያሉ ክፍተቶችን መለየትና ለቀጣይ ትግበራ መነሻ የሚሆኑ ምልከታዎችን ማድረግ መሆኑን አስረድተዋል።

‎የማህበረሰብ አቀፍ ቱሪዝም ቱሪስቶች መጥተው አንድን ቦታ ብቻ ጎብኝተው ከመሄድ ይልቅ በአካባቢው ቆይታ እንዲያደርጉ፣ ከማህበረሰቡ ጋር በቀጥታ እንዲገናኙና የአካባቢውን ባህል፣ ምግብ፣ መጠጥና እደ ጥበብ በተግባር እንዲያውቁ የሚያስችል መሆኑንም አቶ መላሽ ገልጸዋል።

‎እንደ «ዋካ» ያሉ የኮንሶ ባህላዊ ሀብቶችን በመመልከት ብቻ ሳይሆን አጠራሩንና አሠራሩን በተግባር በመሳተፍ እንዲረዱ ማድረግ ቱሪስቶችን በአካባቢው ለማቆየትና የቱሪዝም ገቢው በአካባቢው እንዲዘዋወር ለማድረግ ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዋል።

‎በዚህ መልኩ የቱሪዝም ጥቅም ለአካባቢው ማህበረሰብ፣ በእደ ጥበብ ለተሰማሩ ወገኖችና ከቱሪዝም ጋር በተያያዙ ሥራዎች ለሚሳተፉ ግለሰቦች እንዲደርስ በማድረግ የካራት ከተማንና የዞኑን ኢኮኖሚ ለማሳደግ የሚያግዝ መሆኑን አቶ መላሽ አስረድተዋል።

‎በጉብኝቱ የክልሉ ቱሪዝም ቢሮ ተወካዮች፣ የኮንሶ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ፣ የካራት ከተማ ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ጽሕፈት ቤት ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ተሳትፈዋል። ፕሮግራሙን በፋይናንስ ከሚደግፉ አጋሮች መካከልም ከሆላንድ የመጡት እንግዶች መሆናቸው ተገልጿል።

‎በጋሞሌ አምባ መንደር የተደረገው አቀባበል የኮንሶን ባህላዊ እንግዳ ተቀባይነትና የማህበረሰቡን ቀጥተኛ ተሳትፎ ያሳየ ሲሆን፣ የአካባቢው ሽማግሌዎችና ማህበረሰቡ እንግዶቹን በፈገግታና በቅርበት መቀበላቸው ለጎብኚዎቹ ልዩ ልምድ ፈጥሯል።

‎ከሆላንድ የመጡት የCBT-CBI ፕሮግራም ማናጀር ዣኔት (Jeanette) በጉብኝቱ በመሳተፋቸው ደስተኛ መሆናቸውንና ኮንሶ በርካታና የተለያዩ የቱሪዝም መዳረሻዎችን የያዘ መሆኑን ከጉብኝታቸው መመልከታቸውን ገልጸዋል።

‎የማህበረሰብ አቀፍ ቱሪዝም ፕሮግራሙ ከፍተኛ ጠቀሜታ ያለው መሆኑን ጠቁመው፣ የዛሬው ጉብኝት በቀጣይ በጋራ ሊከናወኑ ለሚገባቸው ሥራዎች ጠንካራ መነሻ እንደሚሆን ገልጸዋል።

‎በጉብኝቱ ማጠናቀቂያም የከርቲታ ጎሳ መሪ ካላ ገዛኼኝ በሚገኙበት ባህላዊ ቤት በመገኘት የኮንሶን ባህላዊ አኗኗር፣ የአካባቢውን የቱሪዝም ሀብትና ባህላዊ ልምዶች ተመልክተዋል።

‎የጉብኝቱ ተሳታፊዎችም በቀጣይ ሊተገበሩ በሚገባቸው ጉዳዮች ላይ በቅንጅትና በጋራ መሥራት፣ የቱሪዝም ምርቶቹን በተግባር ማጠናከርና ማህበረሰቡ ከዘርፉ የሚገኘውን ጥቅም እንዲያሳድግ ማድረግ እንደሚገባ ተጠቁሟል።

‎የኮንሶ ዞን የማህበረሰብ አቀፍ ቱሪዝም እንቅስቃሴም ከቅድመ ዝግጅትና ምልከታ ወደ ተግባራዊ አፈጻጸም በመሸጋገር የአካባቢውን ባህልና ቱሪዝም ሀብት በመጠቀም ለማህበረሰቡ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት የሚፈጥር ሥራ እንደሚሆን ተገልጿል።

  በኮንሶ ዞን የኪንቢሮ ደረጃ አንድ የትራንስፖርት ማህበር 7ኛ ጠቅላላ ጉባኤ ተካሄደበኮንሶ ዞን የኪንቢሮ ደረጃ አንድ የትራንስፖርት ማህበር 7ኛ ጠቅላላ ጉባኤ ተካህዷል። ጉባኤው በሀገር ሽ...
29/08/2026

በኮንሶ ዞን የኪንቢሮ ደረጃ አንድ የትራንስፖርት ማህበር 7ኛ ጠቅላላ ጉባኤ ተካሄደ

በኮንሶ ዞን የኪንቢሮ ደረጃ አንድ የትራንስፖርት ማህበር 7ኛ ጠቅላላ ጉባኤ ተካህዷል።

ጉባኤው በሀገር ሽማግሌዎች ቡራኬ የተጀመረ ሲሆን፣ በኮንሶ ዞን ንግድና ገበያ ልማት ኃላፊ አቶ ሰለሞን ካሊታ በይፋ የተጀመረ ስሆን በጉባኤው የማህበሩ የአንድ ዓመት የሥራ አፈጻጸምና የቀጣይ ዓመት ዕቅድ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።

በውይይቱም የተሳፋሪዎችን ደህንነት ማስቀደም፣ የትራፊክ ሕጎችን ማክበር፣ ተሳፋሪዎችን በአክብሮት ማስተናገድና የሥራ ሥነ-ምግባርን ማሻሻል የሚገባቸው ተግባራት መሆናቸው ተነስቷል።

የዞኑ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ኃላፊ አቶ ካንታለ ካፖሌ፣ የትራንስፖርት ማህበራት ለህብረተሰቡ የሚሰጡትን አገልግሎት በሕግ፣ በሥነ-ምግባርና በተጠያቂነት መርህ ላይ በመመስረት ማከናወን እንዳለባቸው ገልጸዋል።

ውይይቱን የመሩት የኮንሶ ዞን ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ኃላፊ አቶ ካንታለ ካፖሌ እና የኪንቢሮ ደረጃ 1 የትራንስፖርት ማህበር ሰብሳቢ አቶ ዮናስ ጉይታ ናቸው።

በጉባኤው የተነሱ ሀሳቦች በቀጣይ የማህበሩን የውስጥ አሰራር ለማጠናከርና ለተሳፋሪዎች የተሻለና አስተማማኝ የትራንስፖርት አገልግሎት ለመስጠት እንደሚውሉ ተገልጿል።

ጉባኤውም በማህበሩ የሥራ አፈጻጸም ግምገማና በቀጣይ ዓመት ዕቅድ ላይ በመምከር ተጠናቋል።

ነሐሴ 23/2018 ዓ.ም

መረጃው፦
የካራት ከተማ አሰተዳደር መንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ዩኑት ነው

  ‎በፈረንሳይ ኢምባሲ የኢትዮጵያ የአርኪዮሎጂ ጥናት ቡድንና ሠራተኞች ኮንሶ ዞን ካራት ከተማ ገቡ፣‎‎ካራት:ነሐሴ 22/2018 ዓ.ም (ኮንሶ ዞን ኮሙኒኬሽን)‎‎ልዑካኑ ኮንሶ ዞን ካራት ከተ...
28/08/2026

‎በፈረንሳይ ኢምባሲ የኢትዮጵያ የአርኪዮሎጂ ጥናት ቡድንና ሠራተኞች ኮንሶ ዞን ካራት ከተማ ገቡ፣

‎ካራት:ነሐሴ 22/2018 ዓ.ም (ኮንሶ ዞን ኮሙኒኬሽን)

‎ልዑካኑ ኮንሶ ዞን ካራት ከተማ ሲደርሱ የዞኑ አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ደመላሽ ጎንዲሼ፣የዞኑ ቱሪዝም ከክልል ከፍተኛ ባለሙያዎች ጋር በመሆን ለሠራተኞቹና ለአርኪዮሎጂ ጥናት ቡድን በኮንሶ ማህበረሰብ የጥናትና ምርምር ማዕከል ደማቅ አቀባበል አድርገዉላቸዋል።

‎የዞኑ ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ አቶ ዝናቡ ገሠሠ እንደገለፁት እንግዶቹ የመጡት ሙዚየሙን ለጥናት እና ምርምር ማዕከል ከማድረግ አንፃር የተገኙ ውጤቶች ያሉበት ደረጃ ለማየት መሆኑን አብራርተዋል።

‎በተጨማሪ በኢምባሲዉ የሚደገፈው የኮንሶ ሙዚየም የሁለተኛ ዙር የጥገና እና የዕድሳት ሥራዎች ላይ ተግባቦት በመፍጠርና ጥገናውን ለማከናወን መሆኑንም አስረድተዋል።

‎በኢምባሲዉ የትብብር ጉዳዮች ኃላፊ Dr. Jullie DUSSEAUX በበኩላቸዉ የፈረንሳይ ኢምባሲ ለኮንሶ ማህበረሰብ የሚያደርገው ድጋፍ ለዓመታት የዘለቀ ሲሆን በሙዚየሙ የመጀመሪያ ዙር የጥገና እና የዕድሳት ሥራዎች የበጀት ድጋፍ ማድረጉን በማስታወስ ሁለተኛ ዙር ድጋፍ በቅርብ ጊዜ ወደ ሥራ እንደሚገባ አስታውቀዋል።

‎የኮንሶ አርኪዮሎጂ ሳይቶች ጥናት ቡድን መሪ ዶ/ር ዮናስ በበኩላቸው የጥናት ቡድኑ የሙዝየሙ ክፍሎች ጥገና እና ዕድሳት ያለበትን ደረጃ በማድነቅ ሥራው በቅርብ ቀናት ውስጥ እንደሚጠናቀቅ ገልጸዋል።

‎ልዑካኑ በቆይታቸውም በሙዚየም ያሉ የኮንሶ ማህበረሰብ ቅርሶች ጎብኝተው የተደሰቱ ሲሆን በውስጡ ያለዉ የቅርሶች አደረጃጀት ላይ ሙያዊ አስተያየታቸውን ለግሰዋል።

‎በመጨረሻም በዞኑ የሚገኙ አምባ መንደራትንም መጎብኘታቸዉ መምሪያው ገልጿል።

 :-በኮንሶ ዞን ካራት ከተማ አስተዳደር ት/ቤቶች ጽ/ቤት የዓመቱን ተማሪ ምዝገባ የደረሰበት ደረጃ ግምገማ መድረክ አካሄደ።የግምገማ መድረኩን በንግግር የከፈቱት በኮንሶ ዞን ካራት ከተማ አስ...
28/08/2026

:-በኮንሶ ዞን ካራት ከተማ አስተዳደር ት/ቤቶች ጽ/ቤት የዓመቱን ተማሪ ምዝገባ የደረሰበት ደረጃ ግምገማ መድረክ አካሄደ።

የግምገማ መድረኩን በንግግር የከፈቱት በኮንሶ ዞን ካራት ከተማ አስተዳደር ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ የኃላሸት ጉዶያ በመክፈቻ ንግግራቸው ፣በዚህ ዓሜት በከተማችን ዕድሜአቸው ለትምህርት የደረሱትን ሕፃናት አጠቃለን ወደ ትምህርት ገቤታ በማምጣት ጀምረው መማር ላይ ያሉትን ይዘን፣በተለያዩ እርከኖች ያቋረጡትን በመሰብሰብ በ2019 ዓ.ም የትምህርት ተሳትፎውን ከመቸውም በላይ ከፍ ለማድረግ እየሠራን ነው ብሏል።

በመቀጠል የወቅቱ ምዝገባ ሁኔታ ዳሳሳ ሠነድ በካራት ከተማ አስተዳደር ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ የኃላሸት ጉዶያ የቀረበ ስሆን በሠነዱ በተወሰኑ ትም/ቤቶች ምዝገባው በጥሩ ሁኔታ እየተካሄደ ብሆንም እስከአሁን ዝቅተኛ አፈጻጸም ደረጃ ላይ ያሉ ትም/ት ቤቶች ከመኖራቸውም አልፎ ምዝገባ ያልጀመሩም መኖራቸው ተገልጿል።
በተመሳሳይ ሁኔታ መደበኛ ባልሆኑ ትም/ቶች ላይ ተገቢ ትኩረት እንዳልተሠጠ በሰነዱ ተመልክቷል።

በመቀጠል ተሰብሳቢዎቹ በቀረበው ሠነድና አጠቃላይ ቀጣይ የተማሪ ምምዝገባ ሁኔታ ላይ እንድ ወያይ የተደረገ ስሆን መድረኩ በኮንሶ ዞን የዋና አስተዳዳሪ ልዩ አማካሪ አቶ ግርማ በሌ፣የካራት ከተማ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ጋሻው ኩሲያና የከተማ አስተዳደሩ ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ የኃላሸት ጉዶያ
መርተዋል።

በመጨረሻ ተሰብሳቢዎች በአጀንዳው ላይ በጥልቀት ተወያይተ ከመድረክ ተገቢው ማጠቃለያ ተሰጥቶና ቀጣይ አቅጣጫ ከተቀመጠ ቦኋላ መድረኩ ተዘግቷል።

ነሀሰ 22/2018 ዓ.ም
የYouTube https://www.youtube.com/ subscribe በማድረግ

የpage
https://www.facebook.com/profile.php?id=100068159616347&mibextid=ZbWKwL like and Sher በማድረግ ቤተሰብ በመሆን መረጃ ይከታተላሉ!

መረጃው፦
የካራት ከተማ አሰተዳደር መንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ዩኑት ነው

በጎነት ከፈጣሪ ዘንድ የሚያስመሰግን ተግባር መሆኑ ተገለጸ። የኮንሶ ዞን ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያና የወጣቶች በጎ ጽ/ቤት የቴክኒክ ቡድን በካራት ከተማ አስተዳደር ተገኝተው የክረምት በ...
27/08/2026

በጎነት ከፈጣሪ ዘንድ የሚያስመሰግን ተግባር መሆኑ ተገለጸ።

የኮንሶ ዞን ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያና የወጣቶች በጎ ጽ/ቤት የቴክኒክ ቡድን በካራት ከተማ አስተዳደር ተገኝተው የክረምት በጎ ተግባራት ያለበትን ደረጃ አፈጻጸም ገምግሟል።

ግምገማውን የመሩት የዞኑ የሴቶች ማህበራዊ ጉዳይ ባለሙያ አቶ ገየቶ ገደኖና የዞኑ የወጣቶች በጎ አድራጎት ጽ/ቤት ባለ ሙያ አቶ ከበደ ለ18ቱ የክረምት በጎ ተግባራት መጠይቅ አቅርበው ከተማ አስተዳደሩ እስከ ዛሬ ያለበትን ደረጃ በጥልቀት ገምግመዋል።

በግምገማው በዘርፎቹ የታዮ ክፍተቶችን በመለየትና በቀጣይ የመፍትሄ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ በቀሩት ጥቂት ቀናት ውስጥ ከሁሉም የጽ/ቤቶችና የዪኒት የተመደቡት ፎካል ፔርሴኖች ለሥራው ትኩረት በመሰጠት የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ እንዲሠሩ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

የከተማ አስተዳደሩ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ዩኒት አስተባባሪ ወ/ሮ አስቴር ገዛኸኝ በበኩላቸው የተደረገው የድጋፍና ክትትሉ ሥራ ለተግባሩ ስኬት ግባአት የተወሰደበት መሆኑን ተናግረው ክትትሉ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል።

በመጨረሻም የሳይት ጉብኝት በካሞሌና በባዲንካልቱ ሠፈራት በቲሙ እንደሚደረግ ተገልጿል።

ነሐሴ 21/2018 ዓ.ም
የYouTube https://www.youtube.com/ subscribe በማድረግ

የpage
https://www.facebook.com/profile.php?id=100068159616347&mibextid=ZbWKwL like and Sher በማድረግ ቤተሰብ በመሆን መረጃ ይከታተላሉ!

መረጃው፦
የካራት ከተማ አሰተዳደር መንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ዩኑት ነው

በዞኑ የቱሪስት ፍሰት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱን የኮንሶ ዞን ቱሪዝም መምሪያ አስታወቀ።‎ካራት:ነሐሴ 20/2018 ዓ.ም (ኮንሶ ዞን ኮሙኒኬሽን)‎በ2018 በጀት አመት ከ3 ሺህ  በላ...
26/08/2026

በዞኑ የቱሪስት ፍሰት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱን የኮንሶ ዞን ቱሪዝም መምሪያ አስታወቀ።

ካራት:ነሐሴ 20/2018 ዓ.ም (ኮንሶ ዞን ኮሙኒኬሽን)

‎በ2018 በጀት አመት ከ3 ሺህ በላይ የሀገር ውስጥና የውጪ ጎብኚዎች ዞኑን የጎበኙ ሲሆን ከ 4 ሚሊየን ብር በላይ ገቢ መገኘቱም ተገልጿል።

‎የኮንሶ ዞን ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ አቶ ዝናቡ ገሠሠ በ2018 በጀት አመት 438 የሀገር ውስጥና 2 ሺህ 851 የውጭ ሀገር ጎብኚዎች ዞኑን የጎበኙ ሲሆን ከዚህም 4 ሚሊየን 550 ሺህ ብር መገኘቱን አስታውቀዋል።

‎ይህም ከ2017 በጀት አመት ጋር ሲነጻጸር ከፍተኛ ቁጥር የጨመረ እና አፈፃፀሙም 168 በመቶ የገቢ ብልጫ እንዳለው አመላክተዋል።

‎በሀገር ደረጃ የተደረገው የፖሊሲ ለውጥ ፣ የዞኑ ሰላም መሆን አልፎም ቱሪዝሙን መነቃቃት ማሳየቱ የቱሪስቱንና የገቢ አቅም እንዲጨምር ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን አቶ ዝናቡ ገልጸዋል።

‎በቀጣይ የጎብኚዎችን ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ ለማሳደግ መዳረሻዎቹን ምቹና ሳቢ እንዲሆኑ ፣ ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲኖር ከማድረግም ባሻገር ማህበረሰብ አቀፍ ቱሪዝምን ለማሳደግ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመቀናጀት አዳዲስ ስትራቴጂዎች ተቀርጸዋል ብለዋል።

‎በሀገራችን የሚገኙ የቱሪዝም መዳረሻዎች ከሀገር አልፎ ለዓለም በይበልጥ ለማስተዋወቅ የሁሉም ድርሻ የጎላ በመሆኑ ሀላፊነታቸውን እንዲወጡ የመምሪያው ኃላፊ አጽንኦት ሰጥተዋል።

‎የኮንሶ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ገለቦ ጎልቶሞ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለኮንሶ ሳብቴሽን ግንባታ ለአፈር ጥናት ስራ ለመጡት የጥናት ልዑክ ደማቅ አቀባበል አደረጉ፣‎‎ካራት:ነሐሴ ...
26/08/2026

‎የኮንሶ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ገለቦ ጎልቶሞ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለኮንሶ ሳብቴሽን ግንባታ ለአፈር ጥናት ስራ ለመጡት የጥናት ልዑክ ደማቅ አቀባበል አደረጉ፣

‎ካራት:ነሐሴ 20/2018 ዓ.ም (ኮንሶ ዞን ኮሙኒኬሽን)

‎የኮንሶ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ገለቦ ጎልቶሞ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለኮንሶ ሳብቴሽን ግንባታ ለአፈር ጥናት ስራ ለመጡት የጥናት ልዑክ ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል።

‎የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ገለቦ ጎልቶሞ በአቀባበሉ ወቅት እንደገለጹት የህዝባችንን የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ትኩረት ሰጥተው እየሠሩ መሆናቸውን በመግለጽ ችግሩን ለመቅረፍ የተጀመረው የሳብስቴሽን ግንባታ ስራ በፍጥነት ወደ ተግባር እንዲገባ በየደረጃ ያሉ ሂደቶች እየተከናወኑ መሆናቸውን ገልጸዋል።

‎በሀገራችን የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚነትን ለማስፋፋት እየተከናወነ ባለው ተግባር መካከል በኮንሶ ዞን ለኃይል ማከፋፈያ (ሳብስቴሽን) ጣቢያ እና ለከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ለአፈር ምርምራ ስራ መምጣታቸውን ልዑካኑ ገልጿል።

‎በመጨረሻም በዞኑ አስተዳደር በተደረገላቸው አቀባበል ልባዊ ምስጋናቸውን በማቅረብ የአፈር ጥናት ስራውን በተያዘለት ጊዜ በማጠናቀቅ የሳብስቴሽን ግንባታ ሂደት ወደ ቀጣይ ደረጃ እንደሚሻገርም ገልጸዋል።

  ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት በ2019 በጀት አመት ከ541 ሚልዮን 4 መቶ 44 ሽህ ብር በላይ ረቂቅ በጀት አጸደቀ።ሲካሄድ የነበረው የካራት ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት 8ኛ አመት16ኛ መ...
25/08/2026

ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት በ2019 በጀት አመት ከ541 ሚልዮን 4 መቶ 44 ሽህ ብር በላይ ረቂቅ በጀት አጸደቀ።

ሲካሄድ የነበረው የካራት ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት 8ኛ አመት16ኛ መደበኛ ጉባዔ ተጠናቋል።

የካራት ከተማ አስተዳደር ከንቲባ የተከበሩ አቶ ጋሻው ኩሲያ በከተማ አስተዳደሩ በ4ኛ ሩብ አመት የተከናወኑትን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተግባራትን ለጉባዔው በሰፊው አቅርበዋል።

የተከበሩ አቶ ጋሻው እንዳሉት በከተማው ሠላምን ለማረጋገጥ፣ የመልካም አስተዳደር፣ ዲሞክራሲና ልማት እንድረጋጥ ለማድረግ በርካታ ሥራዎች መሠራታቸውን ተናግረዋል።

በሩብ ዓመቱ የመብራት ዝርጋታ ተመን፣ ጥናትና የዝርጋታ ሥራዎች በናላያ ሰገን፤ በገርሳሌ እንዱሁም የኢሳሌና የኩቤ መብራት፤ የዉሃ መስመር ዕድሳት እና ጥገና በሚሌኒየምና በአውራ ጎዳና፤ የአዳዲስ መንገድ ከፈታዎች ከመር መሬ ገልድመን አልፎ እስከ ዋና አስፋልት ድረስ እና ጥገና እንዱሁም ነባርና አዲዲስ የፕሮጀክት ሥራዎችን በማስቀጠልና አልቀዉ አገልግሎት እንዲሰጡ መደረጋቸውን በሪፖርታቸው ዳስሰዋል።

ነባርና ፕሮጀክቶችን በማስቀጠልና አዳዲስ ፕሮጀክቶችን በማስጀመር አንጻር የተለያየ ሥራዎች እንደተሰሩ የተከበሩ አቶ ጋሻው ኩሲያ አንስተው ከእነዚህም የዱራይቴ ጤና ኬላ፣ የዳራ ፓሌታ ጤና ኬላ የላጋ ጉባ ጤና ኬላ፣ የእናቶች ማረፊያ ፣የቄራ ግንባታ፣ የመገናኛ ሠፈር ለአብነት አንስተዋል።

በ4ኛ ሩብ አመት በከተማው ማዘጋጃቤታዊ አገልግሎት ጽ/ቤት በፋይናንስና ፕላን ልማት ጽ/ ቤት በትምህርት ጽ/ቤት፣ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት፣ በገቢዎች ጽ/ቤት፣ በሥራና ክህሎት ጽ/ቤት፣ በሠላምና ፀጥታ ጽ/ቤት፣ በሴቶችና ማህበራዊ ጉዲይና በፍትህ ጽ/ቤት፣በፖሊስ ጽ/ቤት የተሰሩ ሥራዎች በሪፖርታቸው በሰፊው አቅርበዋል።

የተከበሩ ከንቲባ አቶ ጋሻው በህብረት ሥራ ልማት ዩኒት፣ በአካባቢ ጥበቃ አየር ንብረት ለውጥ ዩኒት፣ በትራንስፖርትና ልጄስቲክስ ዩኒት፣ ኤኖቬሽንና ኢንፍርሜሽን ቴክኖልጂ ዩኒት፣ በመሬት ዩኒት፣ በኢንቨስትሜንት ልማት ዩኒት፣ በንግድና ኢንዱስትሪ ዩኒት፣ በመንግስት ኮሚንኬሽን አገልግሎት ዩኒት፣ በባህል ናቱርዝምና ስፖርት ዩኒት፣ በከተማ ግብርና ዩኒት ፣ሲቪሌ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ዩኒት ለጉባኤው በስፋት ቀርበዋል።

የ2019 በጀት አመት ረቂቅ በጀት በከተማ አሰተዳደሩ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ በአቶ ንጋቱ ጉልጉላ ለም/ቤቱ ቀርቧል።

የካራት ከተማ አስተዳደር ፋይናንስና ፕላን ጽ/ቤት ኃላፊ የተከበሩ አቶ አለማየሁ ፈረደ በበኩላቸው የ2019 ዓ.ም ጥቅል በጀት መግለጫ፣ የ2017 ዓ.ም የተሰበሰበ የማዘጋጃ ቤት ተጨማሪ በጀትና ለመንግሥት ሠራተኞች፣ የተሿሚዎችና የደሞዝ ማሻሻያ በጀት ለም/ቤቱ አስደምጠዋል።

በ2017 በጀት ዓመት በማዘጋጃ ቤት ጽ/ቤት በትርፍነት የተሰበሰበ ተጨማሪ ገቢ በ 2018 ዓ.ም በክልል ፋይናንስና ፕላን ልማት ቢሮ ፀድቆ የበጀት አካል እንድሆን መፈቀዱን የተከበሩ ከቶ አለማየሁ አብራርተዋል።

የተከበሩ አቶ አለማነሁ የ2019 ዓ.ም ጥቅል በጀት መግለጫ 541,444,119 ብር ሲሆን በዚህም 2019 በጀት አመት ረቂቅ አዋጅ ሲዘረዝሩ፦

#ከመንግሥት ግምጃ ቤት 117,717,169 ብር
#ከከተማው የሚሰበሰበው መደበኛ ገቢ 339,752,792 ብር
#ከጤና ተቋማት የሚሰበሰብ ገቢ 5,344,437 ብር
#ከማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ገቢ 73,216,742 ብር
#ከትምህርት ቤቶች ገቢ 5,413,058 ባጠቃላይ 541,444,119 ሲሆን ም/ቤቱ በበጀቱ ላይ ገንቢ አስተያየቶችን ሰጥተዋል።

የከተማ አስተዳደሩ ም/ቤት፣ አስፈፃሚ መ/ቤቶችና የከተማ አስተዳደሩ የመጀመሪያ ፍ/ቤት የ4ኛ ሩብ አመት የሥራ አፈጻጸምና የ2019 ዓ.ም ዕቅድ በስፋት ቀርበው በርካታ አስተያየቶችና ጥያቄዎች በኋላ በሙሉ ድምፅ ጸድቋል።

ነሐሴ 19/2018 ዓ.ም
የYouTube https://www.youtube.com/ subscribe በማድረግ

የpage
https://www.facebook.com/profile.php?id=100068159616347&mibextid=ZbWKwL like and Sher በማድረግ ቤተሰብ በመሆን መረጃ ይከታተላሉ!

መረጃው፦
የካራት ከተማ አሰተዳደር መንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ዩኑት ነው

የካራት ከተማ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት የውሃ ፍጆታ ክፍያ አሰባሰብ ስርዓቱን ከኢትዮ-ቴሌኮም ጋር በመተባበር በቴሌብር ዲጂታል የክፍያ ዘዴ በይፋ ማስጀመሩን አስታወቀ።ይህን አዲስ አገል...
25/08/2026

የካራት ከተማ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት የውሃ ፍጆታ ክፍያ አሰባሰብ ስርዓቱን ከኢትዮ-ቴሌኮም ጋር በመተባበር በቴሌብር ዲጂታል የክፍያ ዘዴ በይፋ ማስጀመሩን አስታወቀ።

ይህን አዲስ አገልግሎት ለማስኬድ የሚያስችል አንድ ዘመናዊ ዴስክቶፕ ኮምፒውተርና የዕድሜ ልክ የምዝገባ ሰርሽር ክፍያ በነጻ ተበርክቷል።

በዚህ የክፍያ ስርዓት ማስጀመሪያ ወቅት ንግግር ያደረጉት የካራት ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አማካሪና የከንቲባው ተወካይ አቶ ባንታየሁ መኩሪያ፣ የከተማዋን ነዋሪዎች በቴክኖሎጂ ተጠቃሚ ለማድረግ ኢትዮ ቴሌኮም እና ፓላባ ሶፍትዌር ባደረጉት ትብብርና በነጻ ባበረከቱት ድጋፍ የተሰማቸውን ደስታ ገልጸዋል።

አቶ ባንታየሁ አክለውም አዲሱ አሰራር ተገልጋዮች ያለምንም እንግልት ፈጣን አገልግሎት እንዲያገኙ የሚያስችል ከመሆኑ ባሻገር፣ የድርጅቱን ገቢ አሰባሰብ ስርዓት ዘመናዊና ግልጽነት ያለው እንዲሆን ትልቅ ፋይዳ እንዳለው አብራርተዋል።

የዞኑ ውሃና ኢነርጂ መምሪያ ኃላፊ አቶ አብርሃም ገመቹ በበኩላቸው የኢትዮ ቴሌኮም እና የፓላባ ሶፍትዌር አጋርነት ለነዋሪዎች ፈጣን፣ ተዓማኒ እና ዘመናዊ አገልግሎት ለመስጠት ቁልፍ ሚና እንደሚጫወት አረጋግጠዋል።

ይህ አዲስ የዲጂታል ሥርዓት ተግባራዊ ሲደረግ የክፍያ ሂደቱን ግልጽ ከማድረግ ባለፈ፣ የመረጃ አያያዝን በማዘመን እና የሰው ኃይልን በአግባቡ በመጠቀም ረገድ ከፍተኛ ለውጥ ያመጣል ተብሎ ይጠበቃል።

የካራት ከተማ የውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት ዋና አስኪያጅ አቶ ጋሻው ካንሳ በበኩላቸው፣ ለህብረተሰቡ የሚሰጠውን የውሃ አገልግሎት ዘመናዊ፣ ፈጣንና ቀልጣፋ ለማድረግ ከፓላባ ሶፍትዌር ሶሉሽንስ ግዙፍ ድርጅት ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመተባበር የፍጆታ ክፍያ አሰጣጥ ስርዓቱን በዲጂታል በይፋ ማስጀመሩን ገልጸዋል።

በዚህ አዲስ የዲጂታል ክፍያ ስርዓት አማካኝነት የከተማው የውሃ ተጠቃሚዎች ጊዜንና ጉልበትን በመቆጠብ፣ ያለ ምንም እንግልት ከቤታቸው ወይም ከስራ ቦታቸው ሆነው ክፍያውን መፈጸም እንደሚችሉ አቶ ጋሻው አክለው ገልጸዋል።

ይህ የቴክኖሎጂ ትስስር (Integration) የፓላባ ሶፍትዌርን የቴክኖሎጂ ብቃት፣ የኢትዮ ቴሌኮምን ግዙፍ የዲጂታል ክፍያ መሠረተ-ልማት (ቴሌብር) እና የጽሕፈት ቤቱን የአገልግሎት ፍላጎት በአንድ ላይ ያጣመረ ሲሆን፣ ደንበኞች በየትኛውም ቦታና ጊዜ ሆነው የውሃ ክፍያቸውን በቴሌብር አማካኝነት በሰከንዶች ውስጥ እንዲፈጽሙ ያስችላል።

------------------
ነሐሴ 19/2018ዓ.ም

ነሐሴ 19/2018 ዓ.ም
የYouTube https://www.youtube.com/ subscribe በማድረግ

የpage
https://www.facebook.com/profile.php?id=100068159616347&mibextid=ZbWKwL like and Sher በማድረግ ቤተሰብ በመሆን መረጃ ይከታተላሉ!

መረጃው፦
የካራት ከተማ አሰተዳደር መንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ዩኑት ነው

  የካራት ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት 8ኛ አመት16ኛ መደበኛ ጉባዔ እንደቀጠለ ነው።የከተማው ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ የተከበሩ አቶ አዶላ አይላቴ በመክፈቻ ንግግራቸው በትናንትናው ዕለት ...
25/08/2026

የካራት ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት 8ኛ አመት16ኛ መደበኛ ጉባዔ እንደቀጠለ ነው።

የከተማው ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ የተከበሩ አቶ አዶላ አይላቴ በመክፈቻ ንግግራቸው በትናንትናው ዕለት በነበረው የመስክ ምልከታ በንቃት በመመልከታቸው የተሰማቸውን ደስታ ገልጸው ዛሬ በቀጠለው የም/ቤቱ አባላት ጉባዔው በአትኩሮት እንድከታተሉ መክረዋል።

በዛሬው ዕለት ጉባዔው የከተማ አስተዳደሩ የ2018 ዓ.ም 4ኛ ሩብ አመት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት፣ የ2019 ዓ.ም ዕቅድ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ይጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል።

የም/ቤቱ ምክትል አፈጉባኤ የተከበሩ አቶ ኦላታ ሳንጎ የም/ቤቱን ያለፈውና የዛሬውን ቃለ ጉባዔ ገምግሞ ለማጽደቅ ለጉባኤው በሚያቀርቡት ወቅት እንዳሉት የዛሬውን ጉባኤ ለየት የሚያደርገው የሀገራዊ ምክክር መድረክ በስኬት በተጠናቀቀበት ማግስት በመካሄዱ ነው ብለዋል።

ሙሉ መረጃውን ጉባዔው ሲጠናቀቅ የምናጋራችሁ ይሆናል

ነሐሴ 19/2018 ዓ.ም
የYouTube https://www.youtube.com/ subscribe በማድረግ

የpage
https://www.facebook.com/profile.php?id=100068159616347&mibextid=ZbWKwL like and Sher በማድረግ ቤተሰብ በመሆን መረጃ ይከታተላሉ!

መረጃው፦
የካራት ከተማ አሰተዳደር መንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ዩኑት ነው

Address

@ Southern
Konso

Telephone

+251943935225

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Karat Town Gov't Communication Affairs Office ካራት ከተማ አስ/ር መንግስት ኮ/ጉ/ ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share