03/09/2026
የTAT ዘመናዊ የዶሮ እርባታ ኢንቨስትመንትና የTATI የግብርና አገልግሎቶች ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር መኖ ማቀነባበሪያ ሥራቸውን በአዲስ መልክ እያጠናከሩ መሆኑ ተገለጸ
ካራት፣ ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም (ኮንሶ ዞን ኮሙኒኬሽን)
በኮንሶ ዞን ካራት ዙሪያ ወረዳ፣ አርካሌ ዳራ ቀበሌ የዶሮ እርባታ ኢንቨስትመንት ሥራ የተሰማራው የTAT ዶሮ እርባታ ማኅበር እና በካራት ከተማ የተቋቋመው የTATI የግብርና አገልግሎቶች ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር መኖ ማቀነባበሪያ ማኅበር ሥራቸውን በአዲስ መልክ እያጠናከሩ መሆኑ ተገለጸ።
የማኅበሩ ዋና ሥራ አስኪያጅ ተወካይና የማኅበራዊ ሚዲያ ባለሙያ አቶ ኩሻቦ ኩሲያ እንደገለጹት፣ ማኅበሩ ለኮንሶና አካባቢው አርሶ አደሮች ጥራት ያለው የእንስሳት መኖ በማቅረብ የዶሮ ምርትንና የአርሶ አደሮችን ገቢ ማሳደግን ዋና ዓላማው አድርጎ እየሠራ መሆኑን ተናግረዋል።
የTAT ዶሮ እርባታ ማኅበር በቂና ጥራት ያለው የእንስሳት መኖ ለአካባቢው አምራቾች ለማቅረብ በካራት ከተማ የTATI የግብርና አገልግሎቶች ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር መኖ ማቀነባበሪያ አዘጋጅቶ ወደ ሥራ ማስገባቱንም አቶ ኩሻቦ ገልጸዋል።
በመኖ ማቀነባበሪያውም ለዶሮዎች ብቻ ሳይሆን ለወተት ላሞች፣ ለሰንጋና ለበሬዎች፣ ለጫጩቶች እንዲሁም ለእንቁላል ጣይ ፣ለታዳጊ ዶሮዎች የሚያገለግሉ የመኖ ዓይነቶችን እያዘጋጀ መሆኑን ተገልጸው ፣ ምርቶቹንም ከአካባቢው ባለፈ ለአጎራባች አምራቾች ወይም ዞኖች ለማቅረብ እየተሠራ መሆኑ ታውቋል።
አብዛኛዎቹ የመኖ ግብዓቶች ከእህል የሚገኙ ሲሆን፣ በተለይም በቆሎና ማሽላ እንደሚጠቀሙ ፣ እንዲሁም የመኖውን ጥራትና የንጥረ ነገር ሚዛን ለማስጠበቅ እንደ ዳይካልሲየም ፎስፌት (Dicalcium Phosphate) ፣ ኒዉትረሽ ፕርምክስ(Neturation premix) እና እንድሁም ሞላሰስ(Molasses) ከተቀነባበረ ዉጪ ማቅረብ እንደምቻል እና ሌሎች ግብዓቶችንም እያዘጋጁ መሆኑ ተጠቁሟል።
ተቋሙ በኃይል አቅርቦት እጥረት ሥራው እንዳይስተጓጎል ሁለት የማጫጫ/ማፈልፈያ ማሽኖችን ከቻይና በቅርቡ ማስገባቱንም አቶ ኩሻቦ ገልጸው ፣ እነዚህ ማሽኖች በአንድ ወር ውስጥ ከ24,800 በላይ ጫጩቶችን የመፈልፈል አቅም እንዳላቸው በመግለፅ ፣ ከዚህ ባለፈም ለጫጩቶች መድኃኒትና ክትባት ማቀዝቀዣ የሚያገለግል ፍሪጅ መገጠሙን ገልጸዋል።
ተቋሙ በአሁኑ ወቅት በአጠቃላይ 12 ሠራተኞችን ያሰማራ ሲሆን፣ ሥራውን ሙሉ በሙሉ ሲጀምር ከ24 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ ዕድል መፍጠር እንደሚችል አቶ ኩሻቦ ገልጸዋል።
በዚህም የTAT ዘመናዊ የዶሮ እርባታ ኢንቨስትመንትንና የTATI የግብርና አገልግሎቶች ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር መኖ ማቀነባበሪያ ማኅበራት የዶሮና የእንስሳት ምርትን ከማሳደግ ባለፈ፣ የአርሶ አደሮችን ገቢ ለማሳደግና የአካባቢውን የእንስሳት መኖ አቅርቦት ለማጠናከር የሚያግዙ ሥራዎችን እያከናወኑ መሆኑ ተገልጿል።