Konso Zone Health Department-የኮንሶ ዞን ጤና መምሪያ

  • Home
  • Ethiopia
  • Konso
  • Konso Zone Health Department-የኮንሶ ዞን ጤና መምሪያ

Konso Zone Health Department-የኮንሶ ዞን ጤና መምሪያ ለኮንሶ ሕዝብ ጤና የሚተጋ የመንግሥት መ/ቤት ይፋዊ ገጽ ነው።
ስልክ; +251 467 730016
+251 467 730207/206

የኮንሶ ዞን ጤና መምሪያ የወቅታዊ ክስተት አስተዳደር ሥርዓት /IMS/ ተግባራት ግምገማ አካሄደ፤በመድረኩ የIMS ተግባራት ሪፖርት ያቀረቡት የእናቶችና ሕፃናት ጤናና ሥርዓተ ምግብ ዳይሬክቶሬ...
24/08/2026

የኮንሶ ዞን ጤና መምሪያ የወቅታዊ ክስተት አስተዳደር ሥርዓት /IMS/ ተግባራት ግምገማ አካሄደ፤

በመድረኩ የIMS ተግባራት ሪፖርት ያቀረቡት የእናቶችና ሕፃናት ጤናና ሥርዓተ ምግብ ዳይሬክቶሬት ቡድን መሪ አቶ በርሻ ጎሣያ የተከናወኑ ተግባራት አፈጻጸም ያለበትን ደረጃ በመዋቅሮች በመለየት አቅርበዋል፡፡

አቶ በርሻ ባቀረቡት ሪፖርት የታዩ ጠንካራ ጎኖች ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለባቸው እና የተለዩ ዋና ዋና ማነቆዎች ላይ በየደረጃው ትኩረት ተሰጥቶ መመራት እንዳለበት ጠቁመዋል፡፡ የሪፖርት ሙሉዕነት እና ወቅታዊነት ላይ ክፍተቶች እንዳሉና ሊታረም እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡

የተለያዩ የክትትልና ግምገማ ስትራቴጂዎችን በመንደፍ አሠራሮችን በታችኛው መዋቅር መስመር ማስያዝ እንደሚያስፈልግ ተጠቁሟል፡፡ ችግር ያለባቸውን አከባቢዎች በዝርዝር በመለየት ምላሽ የሚሹ ጉዳዮች ላይ የጋራ መግባባትን በመፍጠር የማስተካከያ እርምጃዎችን መውሰድ ይገባልም ተብሏል፡፡

የጤና መምሪያው ምክትል መምሪያ ኃላፊ አቶ አራርሶ ጋሮ በማጠቃለያው የወባ መከላከል ተግባራትን ጨምሮ የሥርዓተ ምግብ ሊየታውን በሚገባ የተለትርጉም ሰጥቶ መምራት ይፈልጋል ብለዋል፡፡

የጤናው ሴክተር ከሚከውናቸው የመከላከል ተግባራት በተጨማሪ የባለድርሻ አካላት ሚና ከፍተኛ በመሆኑ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመሥራት የሕብረተሰቡን ግንዛቤ ማሳደግ ላይ የምክክርና የውይይት መድረኮችን በሕብረተሰቡ ውስጥ በመፍጠር ሊሠራ እንደሚገባ አቶ አራርሶ አስገንዝበዋል፡፡

የኮንሶ ዞን ጤና መምሪያ
‎Telegram; https://t.me/konsohealth
Facebook; https://www.facebook.com/profile.php?id=61550645678671
WhatsApp; https://whatsapp.com/channe/0029VbBfsnD2phHOw0LeHd1m
E-mail; [email protected]

የማህበረሰብ ተኮር የጤና ተግባራት ለጤናው ሴክተር ስኬት የጀርባ አጥንት በመሆኑ በየደረጃው ትኩረት ሊሰጠው ይገባል፤ አቶ አራርሶ ጋሮየኮንሶ ዞን ጤና መምሪያ የወቅታዊ IMS፣ የሳምንታዊ ኮማ...
21/08/2026

የማህበረሰብ ተኮር የጤና ተግባራት ለጤናው ሴክተር ስኬት የጀርባ አጥንት በመሆኑ በየደረጃው ትኩረት ሊሰጠው ይገባል፤ አቶ አራርሶ ጋሮ

የኮንሶ ዞን ጤና መምሪያ የወቅታዊ IMS፣ የሳምንታዊ ኮማንድ ፖስት፣ የEOC እና ሌሎች በቅንጅት የተከናወኑ የጤና ተግባራት ግምገማ አካሂዷል፤

በግምገማ መድረኩ የተግባራቱ ሪፖርቶች የቀረቡ ሲሆን በቀረቡት ሪፖርቶች መነሻ በአንዳንድ መዋቅሮች የሪፖርት ወቅታዊነትና ሙሉዕነት እንድሁም የመረጃዎች ያለመጣጣም ክፍተቶች መኖራቸው ተገምግሟል፡፡

ከወቅታዊ የIMS ተግባራት ጋር በተያያዘ በአጣዳፊ የምግብ አለመመጣጠን የተለዩ ሕፃናት ቁጥር መጨመር፤ በማህበረሰብ ውስጥ እየተከናወኑ ያሉት የሥርዓተ ምግብ ሊየታ የተጠናከረ መሆኑን የሚያመለክት ብሆንም በቀጣይ እየቀነሰ መሄድ እንዳለበት ታውቆ ክትትል ሊደረግበት እንደሚገባ ተመላክቷል፡፡

ከቀበሌ ጀምሮ ባሉ የጤና መዋቅሮች የመከላከል ተግባራትን ጨምሮ የምግብ አለመመጣጠን ችግር ያለባቸው ሕፃናትን በአግባቡ ከማከም አንጻር የመንግሥት ጤና ተቋማትን ጨምሮ በግል ተቋማት በርካታ የሕክምና አሰጣጥ ችግሮች መኖራቸው ጠንካራ ግምገማ ይፈልጋልም ተብሏል፡፡

የጤና መምሪያው ምክትል መምሪያ ኃላፊ አቶ አራርሶ ጋሮ በማጠቃለያው የቲቢ በሽታ ሊየታን ጨምሮ የማህበረሰብ ተኮር ተግባራት ለጤናው ሴክተር ስኬት የጀርባ አጥንት በመሆኑ በየደረጃው ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡

ምክትል መምሪያ ኃላፊው አክለውም የሳምንታዊ ተግባራት ሪፖርት እና በየዕለቱ ሪፖርት የሚደረጉ ተግባራት በሳምንቱ መጨረሻ የማጠቃለያ መረጃቸው ተመጣጣኝ ሊሆን ይገባል ብለዋል፡፡ የሌሽማኒያ /ካላዛር/ በሽታ በእጅጉ እየጨመረ መሆኑን ጠቅሰው የጤና ስጋት ተግባቦትና የሕበረተሰብ ተሳትፎ ላይ ትኩረት ሰጥቶ መሥራት እንደሚገባም ጠቁመዋል፡፡

የኮንሶ ዞን ጤና መምሪያ
‎Telegram; https://t.me/konsohealth
Facebook; https://www.facebook.com/profile.php?id=61550645678671
WhatsApp; https://whatsapp.com/channe/0029VbBfsnD2phHOw0LeHd1m
E-mail; [email protected]

ተግባራቶችን በጠንካራ አቋም በመምራት በጤናው ሴክተር የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ ይቻላል፤ አቶ ገላነህ ኩሴየኮንሶ ዞን ጤና መምሪያ የ2019 በጀት ዓመት የእያንዳንዱ የሥራ ክፍል የተግባራት ዕ...
18/08/2026

ተግባራቶችን በጠንካራ አቋም በመምራት በጤናው ሴክተር የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ ይቻላል፤ አቶ ገላነህ ኩሴ

የኮንሶ ዞን ጤና መምሪያ የ2019 በጀት ዓመት የእያንዳንዱ የሥራ ክፍል የተግባራት ዕቅድ አተገባበር ላይ የጋራ ምክክር አካሄደ፤

በምክክሩ የሥራ አፈጻጸም መመሪያን መሠረት በማድረግ አመላካች የእያንዳንዱ ፒን ፖይንት ዕቅድ ያቀረቡት የጤና መምሪያው ምክትል መምሪያ ኃላፊ አቶ አራርሶ ጋሮ እንዳሉት ተቋሙን ትክክለኛ ተቋም ሆኖ እንድቀጥል ለማድረግ የመንግሥት መመሪያዎችንና ደንቦችን በአግባቡ በተግባር መተርጎም ያስፈልጋል ብለዋል፡፡

ከዚህ ቀደም የሠራተኞች የአፈጻጸም ምዘና በተለምዶ በውል የማይታወቅ ዕቅድን መነሻ በማድረግ ወይም በትክክል ሠራተኛው በሠራቸው ተግባራት ሳይመዘን መርሃ ግብር ተደርጎ እየተሞላ እንደነበር ያስታወሱት ምክትል መምሪያ ኃላፊው የጤናውን ሴክተር ውጤታማ ለማድረግ እንደዞን የተወሰዱ እርምጃዎች ውስጥ አንዱ ነው ብለዋል፡፡

ምክትል መመሪያ ኃላፊው በአዲስ መልክ የተስተካከለ ዕቅድን ለማሳካት ማነቆ ሊሆኑ የሚችሉ ጉዳዮች (በወረዳዎች የሰው ኃይል አለመሟላት፣ የደራሽ ተግባራት ጊዜ መውሰድ እና ሌሎች የተነሱት) ላይ የጋራ ግንዛቤ እንድያዝ ማብራሪያዎችን ሰጥተዋል፡፡

ተሳታፊዎች በበኩላቸው በሴክተሩ የተጀመሩ ለውጦችን አስመልክቶ ምስጋና በማቅረብ የመንግሥት መመሪያዎች በተግባር ባለመተርጎማቸው መንግሥት መድረስ ያለበት ደረጃ ላይ አለመድረሱን እና ሕብረተሰቡ በዚህ ልክ ተጠቃሚ አለመሆኑን ተናግረዋል፡፡

እስከ ታችኛው መዋቅር ተግባራቶቹ ተቆጥረው በየደረጃው ላሉ የሴክተሩ ሠራተኞች ግንዛቤ ተፈጥሮ የተሻለ ውጤት እንድመዘገብ መስራት ያስፈልጋልም ተብሏል፡፡ የጤናውን ሴክተር ፊት ከማውጣት ባሻገር የሕብረተሰቡ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ አንዱና ዋነኛው መስክ ነው ተብሏል፡፡

የመምሪያው ኃላፊ አቶ ገላነህ ኩሴ በማጠቃለያው እንዳሉት ተግባራቶችን በጠንካራ አቋም በመምራት በጤናው ሴክተር የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ ይቻላል ብለዋል፡፡ የጤናው ሴክተር ሠራተኛ የጋራ ጥረትና ትጋት ከፍተኛ ስከትን ለማምጣት የበለጠ ዕድል እንደሚሰጥ ተናግረዋል፡፡

እንደ ማነቆ የተነሱ ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ በቅንጅት መሥራት እንደሚገባ ጠቁመው የታችኛው መዋቅር ሠራተኞችን ለማብቃት በተጓዳኝ በየወረዳ በተመደቡ ባለሙያዎች መሰራት እንዳለበት አስገንዝበዋል፡፡

የኮንሶ ዞን ጤና መምሪያ
‎Telegram; https://t.me/konsohealth
Facebook; https://www.facebook.com/profile.php?id=61550645678671
WhatsApp; https://whatsapp.com/channe/0029VbBfsnD2phHOw0LeHd1m
E-mail; [email protected]

በኮንሶ ዞን ጤና መምሪያ የወቅታዊ ክስተት አስተዳደር፣ የሳምንታዊ ኮማንድ ፖስት፣ የEOC እና ሌሎች የክረምት በጎ አገልግሎት ተግባራት ግምገማ ተካሄደ፤በግምገማው የተግባራቱ ሪፖርት በሚመለከ...
17/08/2026

በኮንሶ ዞን ጤና መምሪያ የወቅታዊ ክስተት አስተዳደር፣ የሳምንታዊ ኮማንድ ፖስት፣ የEOC እና ሌሎች የክረምት በጎ አገልግሎት ተግባራት ግምገማ ተካሄደ፤

በግምገማው የተግባራቱ ሪፖርት በሚመለከታቸው ባለሙያዎች የቀረበ ሲሆን የተለዩ ዋና ዋና ጠንካራ እና ደካማ ጎኖች እንድሁም በየመዋቅሩ እየተወሰዱ ያሉ የማስተካከያ እርምጃዎችን ውጤታማ ለማድረግ በሚያስችሉ ሁኔታዎች ላይ ተመክሯል፡፡

በውይይቱም በታችኛው መዋቅር የተደረሰባቸው ምልከታዎች፣ እየተከናወኑ ያሉ የክስተት አስተዳደር ሥርዓት ተግባራት እና ተግባራቱን አጠናክሮ ከመከታተል አንፃር ያሉ ውስንነቶች በአግባቡ ጠንካራ ግምገማ እየተደረገ አለመሆኑ ተገልጿል፡፡ በቅንጅት የሚሰሩ የቁጥጥር ሥራዎች ላይ የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን በመጋፈጥ እስከመጨረሻው ሕገ-ወጥነትን መታገል እንደሚገባ ተጠቁሟል፡፡

የክረምት የጤና በጎ አገልግሎት ተግባራት ላይ የተሠሩ ሥራዎች እንደ ተንካራ ጎን የሚወሰዱ እንዳሉ ሆነው የተጠበቀውን ያክል ውጤታማ እየሆነ አለመሆኑ ተጠቅሷል፡፡ ሰፊውን ማህበረሰብ ያሳተፈ ሁሉን አቀፍ አገልግሎቶችን ማስፋት እንደሚያስፈልግና ሊሰራበት እንደሚገባም ተጠቁሟል፡፡

የጤና መምሪያው ኃላፊ አቶ ገላነህ ኩሴ በማጠቃለያው በኮማንድ ፖስት ደረጃ የሚቀርቡ ሪፖርቶች ላይ ዝቅተኛ አፈጻጸም ያስመዘገቡ አንዳንድ ተቋማት መደበኛ ክትባትን ጨምሮ ከዕቅዳቸው አንፃር ተግባራቶቻቸውን እንድለኩ አስገንዝበዋል፡፡

ከIMS ጋር በቅንጅት የሚሰሩ የቤተሰብ ዕቅድና ቀበሌያትን ከአር ነፃ ለማድረግ የሚከናወኑ ተግባራት እንድሁም የመከላከል ሥራዎችንም ማጠናከር ይገባል ብለዋል፡፡ ከምግብ አለመመጣጠን ችግር ጋር በተያያዘ የሚሰሩ ሥራዎች መሬት ላይ ስለመኖራቸውም ማረጋገጥ እና በዞን ደረጃ እስከ ቀበሌ ማጣራት እንደሚያስፈልግ ኃላፊው ተናግረዋል፡፡

የኮንሶ ዞን ጤና መምሪያ
‎Telegram; https://t.me/konsohealth
Facebook; https://www.facebook.com/profile.php?id=61550645678671
WhatsApp; https://whatsapp.com/channe/0029VbBfsnD2phHOw0LeHd1m
E-mail; [email protected]

ትክክለኛና ተደራሽ የጤና መረጃ በማሰራጨት ወረርሽኞችን አስቀድሞ መከላከል ይቻላል — የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮካራት፣ ነሐሴ 09/2018 ዓ.ም (ኮንሶ ዞን ኮሙኒኬሽን)ማህበረሰቡን በት...
15/08/2026

ትክክለኛና ተደራሽ የጤና መረጃ በማሰራጨት ወረርሽኞችን አስቀድሞ መከላከል ይቻላል — የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ

ካራት፣ ነሐሴ 09/2018 ዓ.ም (ኮንሶ ዞን ኮሙኒኬሽን)

ማህበረሰቡን በትክክለኛና ተደራሽ የጤና መረጃ በማበልፀግ ወረርሽኞችን አስቀድሞ መከላከል እንደሚቻል የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ።

የኢቦላ ቫይረስ በሽታን ጨምሮ ወረርሽኞችን በቅድመ ጥንቃቄ ለመከላከል፣ ለሚዲያና ለጤና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ሰጥቷል።

በሥልጠናው የኢቦላ በሽታ ምልክቶችና የመተላለፊያ መንገዶች፣ ወረርሽኝን በቅድሚያ ለመከላከል የሚያስችሉ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሰነዶች እንዲሁም የሚዲያ ባለሙያዎች ሊኖራቸው ስለሚገባ ተሳትፎና ትብብር ውይይት ተደርጓል።

በሥልጠናው የሕዝብ ጤና ኢንስቲትዩት ም/ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ምንተስኖት መልካ፣ ሚዲያዎች በተከታታይ ትክክለኛና ተረጋግጦ የቀረበ የጤና መረጃ በማሰራጨት ወረርሽኝን በመከላከልና ህብረተሰቡን በማሳወቅ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ ጠይቀዋል።

በተለይም መረጃዎች ለህብረተሰቡ በቀላል አገላለጽና በአካባቢ ቋንቋዎች በተከታታይ መድረሳቸው በሽታዎችን በቅድሚያ ለመከላከልና የተሳሳተ መረጃ እንዳይስፋፋ ለማድረግ ወሳኝ መሆኑ ተጠቁሟል።

የሥልጠናው ዓላማም ሚዲያና የጤና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች የተሻለ የጤና መረጃ በማዘጋጀትና በማሰራጨት ለወረርሽኝ መከላከል የሚኖራቸውን ሚና ማጠናከር መሆኑ ተገልጿል።

ሥልጠናው በMIHR ፕሮጀክት ከJIS እና ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ጋር በመተባበር የተሰጠ ሲሆን፣ ከኮንሶ ዞን የጤና ኮሙኒኬሽንና የሚዲያ ባለሙያዎችም ተሳትፈዋል።

በመጨረሻም የጤና መረጃን በተደራሽ፣ ቀላልና ተከታታይ በሆነ መንገድ ለህብረተሰቡ በማድረስ ድንገተኛ የጤና አደጋዎችንና ወረርሽኞችን አስቀድሞ ለመከላከል ግንዛቤ መፍጠር ላይ ትኩረት እንዲደረግ ዶ/ር ምንተስኖት አስገንዝበዋል።

የኮንሶ ዞን ጤና መምሪያ
‎Telegram; https://t.me/konsohealth
Facebook; https://www.facebook.com/profile.php?id=61550645678671
WhatsApp; https://whatsapp.com/channe/0029VbBfsnD2phHOw0LeHd1m
E-mail; [email protected]

በክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት በርካታ ዜጎች የሕክምና አገልግሎቶችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ                                   ...
15/08/2026

በክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት በርካታ ዜጎች የሕክምና አገልግሎቶችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
በክልሉ የተጀመረው የዘንድሮ ክረምት በጎ ወራት ነፃ የህክምና አገልግሎት ለመስጠት በታሰበው መንገድ እየተከናወነ መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታውቋል፡፡

በጤና ተቋማት የደም ግፍት፣ የስኳር፣ የማህፀን በር እና የጡት ካንሰር ነጻ ምርመራ እና ህክምና ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ለሆኑ ዜጎች የተሰጠ ሲሆን ከ400 የሚበልጡ ሰዎች ለመጀመሪያ ጊዜ ተላላፊ በሽታዎች ባልሆኑ ህመም ተገኝቶባቸውና ተለይተው የህክምና አገልግሎት እንዲያገኙ መደረጉን የክልሉ ጤና ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ናፍቆት ብርሃኑ ገልጸዋል፡፡

በሆስፒታል የተኙ ታካሚዎችን በመጎብኘት ማዕድ ማጋራት እና መሰል ተግባራት ከተለያዩ ሴክተሮች ጋር በመቀናጀት እየተሰራ ሲሆን፤ በክረምት ወራትም 10,500 ዩኒት ደም ለመሰብሰብ ከታቀደው እስካሁን 5,036 ዩኒት ደም ተሰብስቧል፥ ሁሉም አከባቢዎች የደም ልገሳ ስራ ተሳትፎ እንዲጠናከር ጥሪ ቀርቧል፡፡

በተጨማሪም የችግኝ ተከላ፣ ቀድሞ የተተከሉ ክብካቤ፣ የጤና ተቋማት የጽዳት ዘመቻ እና እድሳት፣ ለአረጋዊያን የቤት ግንባታ እየተከናወነ ይገኛል።

እስካሁን በክረምት በጎ ተግባር ከ204 ሺ በላይ ወጣቶችን በማሳተፍ የወባ በሽታን የመቆጣጠር ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን ቢሮው አስታውቋል።

የኮንሶ ዞን ጤና መምሪያ
‎Telegram; https://t.me/konsohealth
Facebook; https://www.facebook.com/profile.php?id=61550645678671
WhatsApp; https://whatsapp.com/channe/0029VbBfsnD2phHOw0LeHd1m
E-mail; [email protected]

ጠንካራ የክስተት አስተዳደር ሥርዓትን መፍጠር የጤና አደጋዎችን ለመቆጣጠር ከፍተኛ ሚና እንዳለው ተገለጸ፤በኮንሶ ዞን ጤና መምሪያ ወቅታዊ የክስተት አስተዳደር ሥርዓት ተግባራትንና ሌሎች በቅን...
12/08/2026

ጠንካራ የክስተት አስተዳደር ሥርዓትን መፍጠር የጤና አደጋዎችን ለመቆጣጠር ከፍተኛ ሚና እንዳለው ተገለጸ፤

በኮንሶ ዞን ጤና መምሪያ ወቅታዊ የክስተት አስተዳደር ሥርዓት ተግባራትንና ሌሎች በቅንጅት የተከናወኑ ተግባራት ግምገማ ተካሄደ፤

በመድረኩ ከወቅታዊ አጣዳፊ የምግብ አለመመጣጠን እና የወባ መከላከል በሽታ መከላከል እንድሁም ሌሎች በቅንጅት የሚከናወኑ ተግባራትን ጨምሮ የክልሉ ቲም በተገኘበት ግምገማው ተካሂዷል፡፡

ከክልሉ ጤና ቢሮ ለድጋፍና ክትትል የመጡ ቲም በዞኑ ባደረጉት በቼክ ሊስት የተደገፈ ድጋፋዊ ክትትል ሊጠናከሩ የሚገቡ እና ትኩረት የሚሹ ዋና ዋና ነጥቦችን ለይተው ግብረመልስ የሰጡ ሲሆን በግብረመልሱ እና ሪፖርቶችን መነሻ በማድረግ አስፈላጊ ተግባራት ላይ ተመክሯል፡፡

የክስተት አስተዳደር ሥርዓቱ ከወረዳ ጀምሮ እስከ ቀበሌ የጤና አደጋዎችን ለመቆጣጠር ከፍተኛ ሚና እንዳለው የተገለጸ ሲሆን በማብቃት ጠንካራ ማድረግ ይገባልም ተብሏል፡፡ የጤና ስጋት አደጋዎች ጋር በተያያዘ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ተመሳሳይነት ያላቸው አለመሆናቸው የተግባራቱ አፈጻጸም ክፍተቶቹን ለማጥበብ በሚመለከታቸው አካላት እየተመራ መጠናከር እነዳለበት ተገልጿል፡፡

የጤና መምሪያው ኃላፊ አቶ ገላነህ ኩሴ በማጠቃለያው ለድጋፋዊ ክትትል የመጣው የክልሉ ቡድንን በማመስገን ከግብረመልሱ መነሻ ወስደን እስከታችኛው መዋቅር የምናስተካክላቸው ነጥቦች ላይ እንሄድበታለን ብለዋል፡፡

በየደረጃው የሚካሄዱ ግምገማዎችና ውይይቶች ውጤትን ማስከተል አለባቸው ብለዋል፡፡ ወባን ከመከላከል አንፃር የሚከናወኑ ተግባራት የአከባቢ ቁጥጥርን ጨምሮ ጠንካራ ክትትል እንደሚሻም አስገንዝበዋል፡፡

የኮንሶ ዞን ጤና መምሪያ
‎Telegram; https://t.me/konsohealth
Facebook; https://www.facebook.com/profile.php?id=61550645678671
WhatsApp; https://whatsapp.com/channe/0029VbBfsnD2phHOw0LeHd1m
E-mail; [email protected]

የአከባቢ ጤና ቁጥጥር ለህብረተሰቡ ጤና መሻሻልና ጉልህ ድርሻ እንዳው የክልሉ ጤና ቢሮ አስታወቀ፡፡ 31ኛ ሣምንት የድንገተኛ አደጋዎች መከላከያ ማዕከል እና 4ኛ ሣምንት መሠረታዊ  ጤና አገል...
10/08/2026

የአከባቢ ጤና ቁጥጥር ለህብረተሰቡ ጤና መሻሻልና ጉልህ ድርሻ እንዳው የክልሉ ጤና ቢሮ አስታወቀ፡፡

31ኛ ሣምንት የድንገተኛ አደጋዎች መከላከያ ማዕከል እና 4ኛ ሣምንት መሠረታዊ ጤና አገልግሎት አፈፃፀም ግምገማውን አካሂዷል፡፡

ሣምንታዊ ሪፖርቱ በማዕከሉ ከፍተኘ ባለሙያዎች ወ/ሮ ምስጋና ማቱሳላ፣ አቶ ሰለሞን ስመነህ እና አቶ ጆሹዋ አየለ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።

በሣምንቱ የተመዘገቡ የድንገተኛ አደጋዎች ሥራ እና መሠረታዊ የጤና ተግባራት ውጤት በየደረጃው ያለው የጤና ባለሙያዎችን ትጋት በመሆኑ ምክትል ቢሮ ኃላፊና ጤና ፕሮግራሞች ዘርፍ ኃላፊ አቶ መና መኩሪያ አመስግነዋል።

በሣምንቱ የመጀመሪያ ቀን በተደረገ ግምገማ የጤና ተግባራን ለማጠናከር በየደረጃው የተካሄዱ የንቅናቄ ተግባራት መጠናከር እንዳለባቸው የክልሉ ህብረተሰብ ኢንስትቲዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ አገኔ አሾሌ አስታውቀዋል፡፡

ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች የመከላከል ሂደቱ ተጠናክሮ የቀጠ ሲሆን በአንዳንድ ጤና ተቋማት የተገኙ ህሙማን ክትትልና ህክምና እንዲያገኙ ተደርጓል፡፡

የዝናብ ትንቢያ እንዳመላከተው በክልሉ አንዳንድ አከባቢዎች ላይ የተፈጥሮ አደጋ እንዳያደርስ ህብረተሰቡ ከወዲሁ ጥንቃቄ እንዲያደርግ የድንገተኛ አደጋዎች ቁጥጥር ማዕከል ጥሪ አቅርቧል።

የዝናብ ትንቢያው በሰብሎች ላይ ጉዳት ሊያደርስ ስለሚችል ስርዓተ ምግብ አገልግሎት ችግር እንዳይከሰት ማህበረሰቡ ከወዲሁ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ማዕከሉ አሳስቧል።

ወባ ከባለፈው ሣምንት አንፃር በእጅጉ የቀነሰ በመሆኑ የክስተት አስተዳደር ስርዓት ግብረኃይሉ ክትትልና ቁጥጥሩን እንዲጠናከር ተነግሯል፡፡

በጎረበት ሀገራት የተከሰቱ ወረርሽኞች ወደ ሀገራችን እንዳይዛመቱ እየተሰደረ ያለው የመከላከልና ቁጥጥር ትረት ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡

ኤች አይ ቪ ቫይረስ በሽታ አዲስ ህሙማን በሣምንቱ የተገኙ ሲሆን ወዲያው ህክምና እንዲጀምሩ ተድርጓል፡፡

የነብሰጡር እናቶችና የጨቅላ ህፃናት ጤናን ለማሻሻል እየተደረገ ያለው ክትትል የተሻለ በመሆኑ ማስቀጠል እንደሚገባ ሪፖርቱ አስደምጧል፡፡

ቤት ለቤት በተደረገው የጤና ተግባራት ክትትልና ቁጥጥር የተሻለ አፈፃፀም ያሣዩ ዞኖች ሲኖሩ፤ ውስንነት የታየባቸው በቀጣይ እንዲያሻሽሉ ተገፆአል፡፡

በሣምንቱ በበርካታ የግል ህክምና ተቋማት እና መዲሃኒት ቤቶች ላይ በተደረገ ቁጥጥር ያልተፈቀዱ መዲሃንት በመያዝና ከተፈቀደላቸው የአገልግሎት ደረጃ በላይ ሲሰሩ በተገኙ ተቋማት ላይ እርምጃ ተወስዷ፡፡

መሠረታዊ ጤና ተግባራት በሣምንቱ የእናቶች ጤና ክትትል የተሸለ አፈፃፀም የተመዘገበ ሲሆን የጨቅላ ህፃናትና ህፃናት ጤና ክትትል ከባለፉት ሣምንታት ጋር ስነፃፀር መሻሻሎችን አሳይቷል ሲሉ ተሳታፊዎች አስተያየት ሰጥተዋል።

የበሽታ ቅኝትና ቁጥጥር ሥራው በየአከባው በተደራጀ መልኩ በመሰራቱ የወባና ሌሎች በሽታዎች በመቀነሱ የቁጥጥር ሂደቱን ማጠናከር እንደሚገባ የህብረተሰብ ጤና ኢንስትቲዩት ምክትል ዳይሬክተር ዶ/ር ምንተስኖት መልካ አስታውቋል።

በአንዳንድ አከባቢዎች የሚከሰቱ የህክምና ግብዓት እጥረትን በማሟላት የህብረተሰቡን ሁለንተናዊ ጤና ማሻሻል እንደሚገባም ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ናፍቆት ብርሃኑ ተናግረዋል።

ለማህበረሰቡ የሚደረጉ የጤና አገልግሎት ጤና ባለሙያዎች በትጋትና ዕውቀት በመስራት የዜጎችን ጤና ለማሻሻል መስራት እንደሚገባ ምክትል ቢሮ ኃላፊው አቶ ዮሰፍ ሶንቆ አሳስበዋል።

የክልሉ ህብረተሰብ ጤና ኢንስትቲዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ አጉኔ አሾሌ በሣምንታዊ ግምገማ መድረኩ እንደተናገሩት የድንገተኛ አደጋዎች ቁጥጥር እና በሽታ መከላከል ተግባሩ አበረታች በመሆኑ ተጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል፡፡

ስርዓተ ምግብ አገልግሎትን በማጠናከር የነብሰጡር እናቶችና የህፃናትን ጤና ለማሻሻል በሁሉም አከባቢዎች ተጠናክሮ እንዲቀጥል ምክትል ቢሮ ኃላፊና የጤና ፕሮግራሞች ዘርፍ ኃላፊ አቶ መና መኩሪያ አሳስበዋል፡፡

የኮንሶ ዞን ጤና መምሪያ
‎Telegram; https://t.me/konsohealth
Facebook; https://www.facebook.com/profile.php?id=61550645678671
WhatsApp; https://whatsapp.com/channe/0029VbBfsnD2phHOw0LeHd1m
E-mail; [email protected]

የኮንሶ ዞን ጤና መምሪያ ወቅታዊ የክስተት አስተዳደር ሥርዓት፣ የሳምንታዊ EOC፣ የኮማንድ ፖስት እና የክረምት በጎ አገ/ሎት ተግባራትን ጫምሮ ሌሎች በሳምንቱ የተከናወኑ ተግባራትን ገመገመ፤...
10/08/2026

የኮንሶ ዞን ጤና መምሪያ ወቅታዊ የክስተት አስተዳደር ሥርዓት፣ የሳምንታዊ EOC፣ የኮማንድ ፖስት እና የክረምት በጎ አገ/ሎት ተግባራትን ጫምሮ ሌሎች በሳምንቱ የተከናወኑ ተግባራትን ገመገመ፤

በመድረኩ የፕሮግራሞቹ ሪፖርቶች በሚመለከታቸው ባለሙያዎች የቀረበ ሲሆን በቀረቡት ሪፖርቶች መነሻ መጠናከር ያለባቸው እና የተለዩ ትኩረት የሚሹ ዋና ዋና ተግባራት ላይ ቀጣይ ሊወሰዱ የሚገቡ የማስተካከያ እርምጃዎች ላይ የጋራ ምክክር ተደርጓል፡፡

በታችኛው መዋቅር በማህበረሰብ ደረጃ እየተወሰዱ ያሉ እርምጃዎች ሊበረታቱ የሚገቡ ጉዳዮች መሆኑ የተጠቆመ ሲሆን የሪፖርት ሙሉዕነት መጓደል ሊስተካከል ይገባል ተብሏል፡፡ የአከባቢ ጤና አጠባበቅ ተግባራትን ከሌሎች ፕሮግራሞች ጋር በማቀናጀት ማጠናከር ይገባልም ተብሏል፡፡

በየመዋቅሩ የሚከናወኑ ተግባራትን ከግብዓት ጋር በማያያዝ ማመሳከር እና እያንዳንዱ መረጃዎችን ማጠናከር ተገቢ ነው ተብሏል፡፡ በርካታ ተግባራት ላይ ግንዛቤን የማሳደግ ሥራ በክረምት ወጣቶች በጎ አገልግሎት እየተሰሩ መሆኑ በቀጣይ ከማህበረሰቡ ጋር የሚሰሩ ተግባራት ላይ ጉልህ ሚና ይኖረዋልም ተብሏል፡፡

የጤና መምሪያው ምክትል መምሪያ ኃላፊ አቶ አራርሶ ጋሮ በማጠቃለያው በየመዋቅሩ በ2 ተከታታይ ቀናት ውስጥ የክስተት አስተዳደር ሥርዓቱን /IMS/ ወደ ተግባር ማስገባትና ማጠናከር ይገባል ብለዋል፡፡

በየሰክሽኑ ያሉ ባለሙያዎች ሁሉም ሪፖርቶቻቸውን መከታተል አለባቸው ያሉት ምክትል መምሪያ ኃላፊው አቶ አራርሶ በየወረዳ የተመደቡ ባለሙያዎች ሁሉንም ተግባራት በማቀናጀት በሚገባ መምራት እንደሚገባቸው አስገንዝበዋል፡፡

ተላላፊ በሽታዎችን ከመከላከል አንፃር የሚከናወኑ ተግባራት ቁጥር ሳይሆን ሕብረተሰቡን ያሳተፈ በተግባር መረጋገጥ ያለበት ነው ብለዋል፡፡ የአከባቢ ጤና አጠባበቅን አስመልክቶ ከአር ነፃ የሆነ ቀበሌን ለመፍጠር ትኩረት መሰጠት እንዳለበትም አቶ አራርሶ ተናግረዋል፡፡

የኮንሶ ዞን ጤና መምሪያ
‎Telegram; https://t.me/konsohealth
Facebook; https://www.facebook.com/profile.php?id=61550645678671
WhatsApp; https://whatsapp.com/channe/0029VbBfsnD2phHOw0LeHd1m
E-mail; [email protected]

የግል ጤና ተቋማት ጥራት ያለው የጤና አገልግሎት ለሕብረተሰቡ በመስጠት የበኩላቸውን ሊወጡ ይገባል፤===================አቶ ገላነህ ኩሴየኮንሶ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊየመንግሥት እና ...
08/08/2026

የግል ጤና ተቋማት ጥራት ያለው የጤና አገልግሎት ለሕብረተሰቡ በመስጠት የበኩላቸውን ሊወጡ ይገባል፤
===================
አቶ ገላነህ ኩሴ
የኮንሶ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ

የመንግሥት እና የግል ጤና ተቋማት የሚያገለግሉት አንድ ሕብረተሰብ መሆኑን የኮንሶ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ ተናግረዋል፡፡

የመምሪያው ኃላፊ አቶ ገላነህ ኩሴ የሕበረተሰቡ የጤና ባለቤትነትን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት ውስጥ የግል ጤና ተቋማት ሚና የጎላ መሆኑን ጠቅሰው ጥራት ያለው የጤና አገልግሎት ለሕብረተሰቡ በመስጠት የበኩላቸውን ኃላፊነት ሊወጡ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡

ኃላፊው አቶ ገላነህ የበጀት ዓመቱ የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ ላይ ባስቀመጡት አቅጣጫ የመንግሥት ጤና ተቋማት በተለያዩ የሥራ መስኮች በሚያደርጉት ርብርብ ብቻ ሕብረተሰቡን ማሻገርና የጤና ባለቤት ማድረግ አይቻልም ብለዋል፡፡

የሕበረተሰቡ የጤና ባለቤትነትን ለማረጋገጥ የግል ጤና ተቋማት የአገልግሎት ጥራት ከፍተኛ ድርሻ ያለው መሆኑን በመጥቀስ ዘርፉ በማህበረሰብ ተኮር ተግባራት በመሳተፍ፣ ሕገ ወጥ የመዲኃኒት ዝውውርን በመከላከል እና በተቋም በሚሰጡ አገልግሎቶች ተቋማዊ ደረጃን በማከለ እና ጥራቱን በጠበቀ መልኩ መሰጠት እንዳለበት አስገንዝበዋል፡፡

የኮንሶ ዞን ጤና መምሪያ
‎Telegram; https://t.me/konsohealth
Facebook; https://www.facebook.com/profile.php?id=61550645678671
WhatsApp; https://whatsapp.com/channe/0029VbBfsnD2phHOw0LeHd1m
E-mail; [email protected]

Address

Konso

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Konso Zone Health Department-የኮንሶ ዞን ጤና መምሪያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share