Lalibela Government Communication Affairs Office

Lalibela Government Communication Affairs Office Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Lalibela Government Communication Affairs Office, Government Official, Lalibela.

የአሸንድዬ በዓልን በድምቀት ለማክበር ቅድመ ዝግጅቶች ተከናውነዋል።ቅዱስ ላሊበላ፦ነሐሴ፣12፣2018(ቅዱስ ላሊበላ ኮሙኒኬሽን) የአሸንድዬ በዓልን በድምቀት ለማክበር ዝግጅት ማድረጋቸውን ነው ...
18/08/2026

የአሸንድዬ በዓልን በድምቀት ለማክበር ቅድመ ዝግጅቶች ተከናውነዋል።

ቅዱስ ላሊበላ፦ነሐሴ፣12፣2018(ቅዱስ ላሊበላ ኮሙኒኬሽን) የአሸንድዬ በዓልን በድምቀት ለማክበር ዝግጅት ማድረጋቸውን ነው የቅዱስ ላሊበላ ከተማ ነዋሪዎች የገለፁት።

አሸንድዬ ክረምቱ ሊገባደድ ሲቃረብ ከወርሐ ነሐሴ አጋማሽ ጀምሮ በላስታ ላሊበላ አካባቢዎች በውብ ልጃገረዶች ጨዋታ ደምቆ የሚከበር በዓል ነው ።

በየዓመቱ ከነሐሴ 16 ጀምሮ እስከ ነሐሴ 20 ባሉት ቀናት ሴቶች አምረውና ተውበው በቡድን በቡድን በመሆን ከአብያተ ክርስቲያናት በመጀመር በየሰፈሩ እየዞሩ የበዓሉን አከባበር ትዕይንት የሚያሳዩበት ነው።

ደረቃማው ምድር አረንጓዴ ለብሶ፣ሳር ቅጠሉ አብቦ፣ የደፈረሱ ወንዞች ጠርተው፣ሰማይ ብሩህ ሲሆን ወጣት ሴቶች እና ወንዶች አምሮባቸው አደባባይ ይወጣሉ።

በዓሉን ለማክበር ሴቶች፣በአካባቢው ባህል አለባበስ፣ አጊያጊያጥ ተውበው፣ፀጉራቸውን ሳዱላና ሹሩባ ተሰርተው ሲዘጋጁ፣ሴቶቹን የሚያጅቡት ወንዶች ደግሞ ንጹህ ለብሰው ጅራፋቸውን የሚያዘጋጁበት ወቅት ነው።

ከተማ አስተዳደሩ ከከተማው ሴቶች ጋር የአሸንድዬ በዓል አከባበር ዝግጅት ላይ ያተኮረ ውይይት አደርጓል።

ከውይይቱ ተሳታፊዎች መካከል ወይዘሮ ደስታ ጓንቸ ፦ አሸንድዬ ለሴቶች ልዩ በዓል ነው መሆኑን ነው የገለፁት።

ከአያት ቅድመ አያት ሲተላለፍ የመጣውን ባህላዊና ሃይማኖታዊ እሴት በተራቸው ጠብቀው ለትውልድ ለማስተላለፍ ሃላፊነታቸውን እየተወጡ ስለመሆኑ ነው የተናገሩት።

ሌላኛዋ የከተማዋ ነዋሪ አስታጥቂው ቢሰጥ በበኩሏ
ሁሌም አሸንድዬን በድምቀት የሚያከብሩት በዓል መሆኑን በመጥቀስ ዘንድሮም በዓሉን በድምቀት ለማክበር ቅድመ ዝግጅታቸውን ማጠናቀቃቸውን ነው የገለፀችው።

ባህሉን ማጠናከርና ለቀጣይ ትውልድ ሳይበረዝ ለማስተላለፍም የድርሻቸውን እየተወጡ ስለመሆኑ ነው የከተማዋ ነዋሪዎች ያመለከቱት።

አሸንድዬ ባህላዊና ሃይማኖታዊ እሴቱ ሳይበረዝ ለቀጣይ ትውልድ እንዲተላለፍ ለማድረግእየተሰራ መሆኑን ያነሱት ደግሞ የቅዱስ ላሊበላ ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ሃላፊዋ ዮርዳኖስ መርሻ ናቸው።

በዓሉን በድምቀት ለማክበር ቅድመ ዝግጅቶች መጠናቀቃቸውንም ነው ያነሱት ።

በየአካባቢው የአሸንድዬ አጨዋወትን የሚያሳዩ የልጃ ገረዶች፣የወጣቶች ዝግጅት፣የአካባቢው የአመጋገብ ስርዓትና ሌሎችም የበዓሉ አካል የሆኑ ቅድመ ዝግጅቶች መጠናቀቃቸውም ተመላክቷል።

በዓሉ ከነሐሴ13 ጀምሮ የሚከበር ሲሆን ወጣቶች ባህላዊ እሴቶቻቸውን የሚያሳዩበት መሆኑንም ነው የተናገሩት።

ባህሉን መሰረት ያደረጉ ፅሁፎችም ቀርበው ውይይት እንደሚደረግባቸውም ነው የተመላከተው።

የቅዱስ ላሊበላ ከተማ አስተዳደር ሴቶች ህፃናት ወጣቶች ማህበራዊ ጉዳይ ፅህፈት ቤት ሃላፊዋ ሰርኬ መኳንንት በበኩላቸው የአሸንድዬን ባህላዊና ሃይማኖታዊ እሴቱን ለመጠቅ እየተሰራ ነው ብለዋል።

ልጃ ገረዶች፣እናቶች፣ ከአለባበስ ጀምሮ በዓሉን በድምቀት ለማክበር ዝግጅት ማድረጋቸውን ነው የጠቀሱት።

ትውፊቱን ጠብቆ ለማቆየት ሴቶች የሚጠበቅባቸውን ሃላፊነት እንዲወጡ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑንም ነው የተናገሩት።

ባለ መልከ ብዙው"አሸንድዬ"ዓለትን ጠርበው መቅደስን ያነፁ፣ወግና ባህልን ሰንደው ታሪክን ያስቀመጡ የቀደሙ ትውልዶች ያስቀመጡልን ነው ።አሸንድዬ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም በዓለ ዕ...
16/08/2026

ባለ መልከ ብዙው"አሸንድዬ"

ዓለትን ጠርበው መቅደስን ያነፁ፣ወግና ባህልን ሰንደው ታሪክን ያስቀመጡ የቀደሙ ትውልዶች ያስቀመጡልን ነው ።

አሸንድዬ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም በዓለ ዕርገት ነው ታሪኩ የሚነሳው።

አሸንድዬ መልከ ብዙ ነው፦የነፃነት፣የተስፋ፣የአብሮነትና አንድነትም መሰረት ነው።

የቀደመ የታሪክ ውርስ፣የልምላሜ መሰረት፣የጨለማው መንጋት ብስራትም ነው።

ህፃናት የመስከረምን መንጋት ሊያበስሩን፣ወፎች በዝማሬያቸው ሊነግሩን ቀኑ ደርሷል።

ይምጡ አሸንድዬን በላስታ ላሊበላ ያክብሩ!

ማህበረሰብ የሚገለገልበትን የህክምና ተቋም ለማዘመን የህዝብን ያልተቋረጠ ድጋፍ ይጠይቃል።የቅዱስ ላሊበላ ጠቅላላ ሆስፒታል በአካባቢው ለሚገኙ አጎራባች ወረዳዎች ከ1.5 ሚሊየን በላይ ለሚሆኑ ...
14/08/2026

ማህበረሰብ የሚገለገልበትን የህክምና ተቋም ለማዘመን የህዝብን ያልተቋረጠ ድጋፍ ይጠይቃል።

የቅዱስ ላሊበላ ጠቅላላ ሆስፒታል በአካባቢው ለሚገኙ አጎራባች ወረዳዎች ከ1.5 ሚሊየን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች አገልግሎት እየሰጠ ያለ ሆስፒታል ነው።

ላለፉት 25 አመታት በሆስፒታሉ የሲቲ ስካን ማሽን ባለመኖሩ የአካባቢው ማህበረሰብ የህክምና አገልግሎት ለማግኘት ወደ ደሴ፣ባህር ዳርና አለፍ ሲል ደግሞ አዲስ አበባ ድረስ በመሄድ ለተጨማሪ ወጭና እንግልት ሲዳረግ ቆይቷል።

የጤና ቢሮው ችግሩን ለመቅረፍ ያስቻለ የCT SCAN ማሽን ለቅዱስ ላሊበላ ጠቅላላ ሆስፒታል ድጋፍ አድርጓል።

ይሁንና የዚህ ማሽን የህክምና አገልግሎት መስጫ ህንፃ ግንባታ በስታንዳርዱ መሰረት መገንባት ያለበት በመሆኑ ለግንባታው ለሚያስፈልገው ወጭ የማህበረሰቡን ድጋፍ ይጠይቃል።

ለዚህም ሲባል ከማህበረሰቡ ልዩ ልዪ የድጋፍ አሰባሳቢ ኮሚቴዎች ተዋቅረው ስራቸውን ጀምረዋል።

በሐገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሃገር ያላችሁ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን፣ባለሐብቶች፣ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆናችሁ ተቋማት፣ በገንዘብ፣በቁሳቁስና በእውቀት ድጋፍ ታደርጉ ዘንድ የድጋፍ አስተባባሪ ኮሚቴው ጥሪውን ያቀርባል።

የቅዱስ ላሊበላ ጠቅላላ ሆስፒታል CT Scan ማሽን ህንጻ ግንባታ/St.Lalibela General Hospital CT SCAN machine Building/
❤ የድጋፍ ማድረጊያ የባንክ አካውንቶች:-
✔️ዳሽን ባንክ =5078107715011
✔️አማራ ባንክ= 9900052043887
✔️አቢሲኒያ ባንክ=264 763 517
✔️አባይ ባንክ=2161113214419018
✔️ንግድ ባንክ=1000787961828
ለሆስፒታሉ ከተለያዩ አካላት የሚደረጉ ድጋፎችንም የምናሳውቅ ይሆናል

❤የቅስቀሳና የሚዲያ ክፍል ኮሚቴ

ነሐሴ 08/2018

ወጣቶች ለአካባቢያቸው ሰላም ያላቸውን አስተዋፅኦ ማበርከት ይጠበቅባቸዋል።ቅዱስ ላሊበላ፣ነሐሴ፣7፣2018(ቅዱስ ላሊበላ ኮሙኒኬሽን) ወጣቶች ስለ ሰላም አበክረው በሚሰሩበትና አካባቢያቸውን በሚ...
13/08/2026

ወጣቶች ለአካባቢያቸው ሰላም ያላቸውን አስተዋፅኦ ማበርከት ይጠበቅባቸዋል።

ቅዱስ ላሊበላ፣ነሐሴ፣7፣2018(ቅዱስ ላሊበላ ኮሙኒኬሽን) ወጣቶች ስለ ሰላም አበክረው በሚሰሩበትና አካባቢያቸውን በሚጠብቁበት ዙሪያ ያተኮረ ውይይት በቅዱስ ላሊበላ ከተማ አስተዳደር ተካሂዷል።

በውይይቱ የተገኙት የሃገር መከላከያ ሰራዊት የ13ኛ ዕዝ ዘመቻ ሃላፊ ኮሎኔል ዘላለም ማሞ ሰላም ለሃገር ዕድገት ወሳኝ በመሆኑ ለሰላም መስፈን ሁሉም አካላት በጋራ ሊሰሩ እንደሚገባ ነው የጠየቁት።

በሰላም ዕጥረት ምክንያት የከተማዋ ልማት ያን ያህል አለመሆኑን ያነሱት ኮሎኔል ዘላለም የልማት እንቅስቃሴውን ለማንሰራራት ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ ነው ያሳሰቡት።

ሰላም እንዲመጣ ወጣቶች አዎንታዊ አስተዋፅኦ ሊያደርጉ ይገባል ያሉት ደግሞ የሰሜን ወሎ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ሃላፊው ወንድምነው ወዳጅ ናቸው።

ወጣቶች አካባቢያቸውን በመጠበቅ ስለ ሰላም አበክረው ሊሰሩ እንደሚገባም ነው ያነሱት።

ወጣቱ በመደራጀት፣በመሰባሰብ፣በሃሳብ አንድ በመሆን ሰላም እንዲመጣ በተግባር መሳተፍ እንዳለበት ነው የጠየቁት።

ወጣቶች በጋራ በመሆን አካባቢያቸውን ሊጠብቁና ስለ ሰላም ያላቸውን አስተዋፅኦ እንዲያበረክቱም ነው ያሳሰቡት።

ልማት የሚመጣው ሰላም ሲኖር በመሆኑ ሁሉም ለሰላም አበክሮ ሊሰራ እንደሚገባ አፅንኦት የሰጡት ሃላፊው ከውሸትና አሉባልታ ርቆ ለሰላምና ልማት መስራት የሚያስፈልግ በመሆኑ ማህበረሰቡ ስለ ሰላም አበክሮ እንዲሰራ ነው ያስገነዘቡት።

የቅዱስ ላሊበላ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ሃላፊ ዮርዳኖስ መርሻ በበኩላቸው አካባቢው መሰረቱ ቱሪዝም በመሆኑ በሰላም ምክንያት ኢኮኖሚው በመጎዳቱ ኢኮኖሚው እንዲያንሰራራ ወጣቱ ስለ ሰላም መስራት አለበትም ነው ያሉት።

ወጣቶች በስነ ልቦና በመንቃት ህዝቡንና ቅርሱን ከሚጎዳ ነገር መጠበቅ እንዳለበት ነው ያሳሰቡት።

ወጣቶች በብሎክ አደረጃጀት ተደራጅው አካባቢያቸውን መጠበቅ እንዳለባቸውም ነው የገለፁት።

ወጣቶች ስለ ሰላም ዘብ በመሆን አካባቢያቸውን መጠበቅ አለባቸው ያሉት ደግም የቅዱስ ላሊበላ ከተማ የሰላምና ደህንነት ሃላፊው ኮሎኔል ታረቀኝ አለሙ ናቸው።

ሰላም አስፈላጊ በመሆኑ ወጣቱ ለሰላም ትኩረት መስጠት እንዳለበት የገለፁት ሃላፊው ከፀጥታ ሃይሉ ጎን በመሆን ለሰላም ሊሰራ ይገባል ነው ያሉት።

በውይይቱ የተገኙት ወጣቶች በበኩላቸው ሰላም ለሁሉም ነገር አስፈላጊ በመሆኑ ለሰላም መስፈን የድርሻቸውን እንደሚወጡ ነው ያረጋገጡት።

የአሸንድዬ በዓልን ለማክበር ለሚመጡ እንግዶች የአየር ትራንስፖርት ተዘጋጅቷል። የላሊበላ ከተማ አስተዳደርቅዱስ ላሊበላ፣ነሐሴ፣6፣2018 (ቅዲስ ላሊበላ ኮሙኒኬሽን) የሰው ልጆች የረቀቀ የስል...
12/08/2026

የአሸንድዬ በዓልን ለማክበር ለሚመጡ እንግዶች የአየር ትራንስፖርት ተዘጋጅቷል። የላሊበላ ከተማ አስተዳደር

ቅዱስ ላሊበላ፣ነሐሴ፣6፣2018 (ቅዲስ ላሊበላ ኮሙኒኬሽን) የሰው ልጆች የረቀቀ የስልጣኔ ማሳያ፣ የወርቃማ ታሪክ ማህደር፣ የኢትዮጵያውያን ከፍታ ማሳያ፣የመልከ ብዙ ጥበብ ባለቤት ነው ላስታ ላሊበላ።

እያደር አዲስ፣የወርቃማ እጆች አሻራ ምድር የሆነውን ቅዱስ ላሊበላና ከባቢውን በብዙ መልኩ ያስታውሱታል፣በሌላኛው ታሪክ ይህ ከባቢ ሁሌም ይደምቃል።

በትውልድ ቅብብሎሽ የመጡ የሰው ልጆች ልዩ ልዩ ባህላዊ እሴቶች ባለቤት የሆነው የላስታ ላሊበላ ማህበረሰብ አመቱን ጠብቆ በሚያከብረው አሸንድዬ ይደምቃል።

በዓሉ ሃይማኖታዊና ባህላዊ ይዘቱን በጠበቀ መልኩ እንዲበከር ለማድረግ ዝግጅቶች እየተከናወኑ መሆኑን የቅዱስ ላሊበላ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና የትምህርት ፅህፈት ቤት ሃላፊው ፈንታው አባተ ይገልፃሉ።

በዓሉን በድምቀት ለማክበር ከህዝቡ፣ከሰንበት ትምህርት ቤት ተማሪዎች፣ከቤተ ክርስቲያን አባቶችና ባለሙያዎችን ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ እየተሰራ መሆኑን ነው ምክትል ከንቲባው ያስረዱት።

የባህሉ ባለቤት የሆነው ማህበረሰብ፣ህፃናት፣ሴቶች፣ወጣቶች፣ በከተማው በሁሉም ቀበሌዎች ልምምድ እያደረጉ ነው።

ከበዓሉ አከባበር ጋር አብረው የሚሄዱ አለባበስ፣የባህል ምግቦችና፣መጠጦች ዝግጅትም እየተደረገ ነው።

በዓሉ ሃይማኖታዊና ባህላዊ ይዘቱን በጠበቀ መልኩ እንዲከበር ለማድረግ ከቅዱስ ላሊበላ ገዳም ጋር በጋራ ዝግጅት እየተደረገ ስለመሆኑም ነው የተመላከተው።

የበዓሉ መከበር አካባቢው የቱሪዝም ማዕከል በመሆኑ ቱሪዝሙን ለማነቃቃት ያግዛል ያሉት ሃላፊው በዓሉን በቦታው ተገኝተው ለሚያከብሩ ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን ነው የገለፁት።

ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ላሊበላ ኤሪፖርት ጋር በመነጋገር ነሐሴ15 ጀምሮ ከመደበኛው በተጨማሪ በረራ እንዲኖር መመቻቸቱ ነው የተገለፀው።

በተለመደው የአካባቢው የቆየ የእንግዳ አቀባበል ባህል፣ወግና ስርዓት መሰረት የከተማ አስተዳደሩ ማህበረሰብ እንግዶችን ለመቀበል ዝግጁ ስለመሆኑም ነው ምክትል ከንቲባው ያረጋገጡት።

ኢትዮጵያውያንና የውጭ ሃገር ዜጎች አሸንድዬን በቅዱስ ላሊበላ ከተማ ተገኝተው እንዲያከብሩም ጥሪ አቅርበዋል።

የእናቶችና ህፃናትን ጤና በመጠበቅ ረገዳ በ2018 በጀት አመት ውጤታማ ስራ ማከናወኑን የቅዱስ ላሊበላ ጤና ጥበቃ ፅህፈት ቤት አስታውቋል።ቅዱስ ላሊበላ፣ነሐሴ፣5፣2018 ዓ.ም (ቅዲስ ላሊበላ...
11/08/2026

የእናቶችና ህፃናትን ጤና በመጠበቅ ረገዳ በ2018 በጀት አመት ውጤታማ ስራ ማከናወኑን የቅዱስ ላሊበላ ጤና ጥበቃ ፅህፈት ቤት አስታውቋል።

ቅዱስ ላሊበላ፣ነሐሴ፣5፣2018 ዓ.ም (ቅዲስ ላሊበላ ኮሙኒኬሽን)የቅዱስ ላሊበላ ጤና ጥበቃ ፅህፈት ቤት በ2018 በጀት አመት የእናቶችንና ህፃናትን እንዲሁም ተላላፊ በሽታዎችን ቀድሞ በመከላከል ረገድ ውጤታማ ስራ ማከናወኑን ነው ያስታወቀው።

ፅህፈት ቤቱ የ2018 በጀት አመት የስራ አፈፃፀሙን የተቋሙ ባለሙያዎች ጋር ገምግሟል።

ተቋሙ በ2019 በጀት አመት ለመፈፀም በዕቅድ ያስቀመጣቸው ስራዎች ላይም ውይይት ተደርጓል።

ተቋሙ የቀበሌ የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎችን በመደገፍ ነብሰ ጡር እናቶች በጤና ተቋም እንዲወልዱ ለማድረግ መሰራቱን ነው ያመለከተው።

የመስቀል ክብራ ቀበሌ ጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያ አንጓች ጌጡ እናቶችን ቤት ለቤት በመከታተል በጤና ተቋም የወሊድ አገልግሎት እንዲያገኙ መሰራቱን ነው የገለፀችው።

የጤና ኮሚቴዎችን በማቋቋም የጤና ፓኬጆችን ለማሟላት እየተሰሩ ባሉ ስራዎች ውጤት መመዝገቡንም ነው ያነሳችው።

ህፃናት የክትባት አገልግሎት እንዲያገኙ ለማድረግ ስለመሰራቱም ነው የተገለፀው።

ሌላኛዋ የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያ አንጓች እስቲበል እናቶች ለልጆቻቸው እስከ ስድስት ወር ጡት ብቻ እንዲያጠቡ ለማድረግ በመከታተልና በማስተማር ውጤታማ ስራ መስራታቸውን ነው የገለፀችው።

ተላላፊ በሽታዎችን በመከላከል፣የማህፀን በር ካንሰር ምርመራና ህክምና በመስጠት፣ተቋሙን በማዘመን ረገድ ሰፊ ስራ መሰራቱን የገለፁት የቅዱስ ላሊበላ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ ዳይሬክተሩ ኬሮስ መንግስቱ ናቸው።

የመድሃኒት ግብአት አቅርቦትን በማሻሻል ረገድ በ5.5 ሚሊየን ብር የህክምና መድሃኒት መሟላቱንም ነው የገለፁት።

ተቋሙን ፅዱና ውብ በማድረግ ለተገልጋይ የተመቸ ማድረግ መቻሉንም ነው ያነሱት።

የእናቶችና ህፃናትን ጤንነት ለመጠበቅ የተሻለ ስራ መሰራቱን ያነሱት ደግሞ የቅዱስ ላሊበላ ጤና ጥበቃ ፅህፈት ቤት ሃላፊው እሸቱ ገስጤ ናቸው።

የቤት ውስጥ ወሊድን ማስቀረት መቻሉን የገለፁት ሃላፊው ከ600 በላይ እናቶች በጤና ተቋም የወሊድ አገልግሎት ማግኘታቸውንም ነው ሃላፊው ያነሱት።

የህፃናትን ጤንነት በመጠበቅ በኩል በወቅቱ ልዩ ልዩ የክትባት አይነቶችን እንዲያገኙ ከማድረግ አኳያ 6629 ህፃናት የክትባት አገልግሎት አግኝተዋል።

በሃይጅንና ሳኒቴሽን ስራዎች የወባ በሽታን ለመከላከል በተሰሩ ስራዎችም ውጤት መመዝገቡ የተጠቀሰው።

በጤና መድህን ማህበረሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ ከ11 ተቋማት ጋር ውል በመውሰድ የህክምና አገልግሎቱን እንዲያገኙ ለማድረግ መሰራቱንም ሃላፊው አንስተዋል።

የድንገተኛ ክፍል ግንባታ ፣የኦዲቲንግ ፋርማሲ፣ የካርድ ክፍል፣የማህበረሰብ አቀፍ መድሃኒት ቤት ማመቻቸት በ2018 የተከናወኑ ውጤታማ ስራዎች መሆናቸውንም ነው እሸቱ ገስጤ ያብራሩት።

በቀጣይ ወረቀት አልባ አሰራርን በመተግበር የጤና አገልግሎቱን ለማዘመን እንደሚሰራም ነው የተገለፀው።

በተቋሙ የስራ አፈፃፀም ግምገማ ላይ የተገኙት የቅዱስ ላሊበላ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ዋና አማካሪ ዲያቆን ፍቅረእየሱስ ሙሉጌታ በጤናው ዘርፍ የተሻለ አፈፃፀም መመዝገቡን ነው ያነሱት።

በተቋሙ ከታቀዱት ስራዎች አኳያ አብዝሃኛዎቹ የተሻለ አፈፃፀም የተመዘገበባቸው በመሆኑ ክፍተቶችን በመለየት በቀጣይ የተሻለ ስራ ለመስራት ትኩረት መደረግ እንዳለበት ነው ያሳሰቡት።

ሞዴል ቀበሌዎችን በማጠናከር በቅንጅትና በትስስር መስራት እንደሚገባም ነው ሃላፊው ያነሱት።

በቀጣይ ለጤና ፓኬጁ አፈፃፁም እንቅፋት የሆኑ ችግሮችን ለመቅረፍም ከተማ አስተዳደሩ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ ነው ሃላፊው ያረጋገጡት።

የጤና ዘርፉን ወደ ተሻለ ደረጃ ለማድረስ ስኬቶችን በማስቀጠል ክፍተቶችን ለመቅረፍ መባረብ እንደሚገባም ነው ያስገነዘቡት።

በ2018 ጥሩ አፈፃፀም ላስመዘገቡ የፅህፈት ቤቱ የጤና ባለሙያዎች፣የጤና አጠባበቅ ጣቢያና የቀበሌ ጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች የዕውቅና ማበረታቻ የምስክር ወረቀት ተበርክቷል።

የአሸንድዬ በዓልን ሃይማኖታዊና ባህላዊ ይዘቱን በጠበቀ መልኩ ለማክበር ዝግጅት እየተደረገ ነው። የቅዱስ ላሊበላ ከተማ አስተዳደር ‎ቅዱስ ላሊበላ፣ነሐሴ፣5፣2018 ዓ.ም (ቅዲስ ላሊበላ ኮሙኒ...
11/08/2026

የአሸንድዬ በዓልን ሃይማኖታዊና ባህላዊ ይዘቱን በጠበቀ መልኩ ለማክበር ዝግጅት እየተደረገ ነው። የቅዱስ ላሊበላ ከተማ አስተዳደር

‎ቅዱስ ላሊበላ፣ነሐሴ፣5፣2018 ዓ.ም (ቅዲስ ላሊበላ ኮሙኒኬሽን) አሸንድየ የልጃ ገረዶች ጨዋታ በየ አመቱ ከነሐሴ አጋማሽ ጀምሮ በድምቀት ከሚከበርባቸው ቦታዎች መካከል የቅዱስ ላሊበላ ከተማ ተጠቃሽ ነው።

ልጃ ገረዶች የነፃነታቸው በዓል ማሳያ የሆነውን "አሸንድዬን" በየዓመቱ በልዩ ዝግጅትና ተውህቦ ያከብሩታል።

በአሸንድዬ የከተማዋ ነዋሪዎች ከህጻን እስከ አዋቂ የበዓሉ መገለጫ በሆኑ አልባሳትና መዋቢያዎች አጊጠው የሚታዩበተም ነው።

የአሸንድዬ ስያሜ በክብረ በዓሉ ወቅትልጃገረዶች በወገባቸው ዙሪያ ከሚለብሱት ከታች ነጭ፣ ከላይ አረንጓዴ የሆነ ረጅም ሳር ወይም ተክል የተወሰደ ስለመሆኑ ይነገራል።

የፊታችን ነሐሴ16 የሚከበረውን አሸንድዬ በዓል ሃይማኖታዊና ባህላዊ ይዘቱን በጠበቀ መልኩ ለማክበር ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የገለፁት የቅዱስ ላሊበላ ከተማ አስተዳደር ባህል፣ቱሪዝምና ስፖርት ፅህፈት ቤት ሃላፊው ዲያቆን አዲሴ ደምሴ ናቸው።

ባህላዊና ሃይማኖታዊ ጨዋታው ሳይበረዝና ሳይከለስ ለቀጣይ ትውልድ ለማስተላለፍ እየተሰራ ስለመሆኑም ነው የተመላከተው።

በዓሉ ከእመቤታችን ባዕለ ዕርገት ጋር መነሻ ተደርጎ እንደሚከበርና ልጃ ገረዶች ከሚያቀርቡት የአሸንድዬ የበዓል አከባበር ስርዓት በተጨማሪ የቅዱስ ላሊበላ ካህናትና የሰንበት ትምህርት ቤት ተማሪዎች ዝማሬ በማቅረብ የሚያከብሩት በመሆኑ በዓሉ የተለየ የአከባበር ስርዓት እንዳለው ነው ሃላፊው ያነሱት።

በዓሉ የሀገር ውስጥና የውጭ ጎብኚዎችን የመሳብ አቅም እንዳለው የጠቀሱት ዲያቆን አዲሴ ባለፉት አመታት ባህላዊና ሃይማኖታዊ ይዘት ያለው አሸንድዬ የልጃ ገረዶች ጨዋታ በድምቀት እየተከበረ በመምጣቱ ለውጭ ሃገር ቱሪስቶች ተጨማሪ የቱሪስት መዳረሻ እየሆነ ስለመምጣቱም ነው የተናገሩት።

የዘንድሮውን የአሸንድዬ ባህላዊና ሃይማኖታዊ ጨዋታ"ባህል ድልድያችን፤አንድነት መዳረሻችን"በሚል መሪ ሃሳብ እንደሚከበር የገለፁት ሃላፊው ልዩ ልዩ ኮሚቴዎች ተዋቅረው ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ ስለመሆኑ ነው ያብራሩት።

ልጃ ገረዶች በየቀበሌው ልምምድ እያደረጉና ባህሉን መሰረት ያደረገ አለባበስ፣አጊያ ጌያጥና ተውህቦን ለመጠበቅ የሚያስችል ዝግጅት እያደረጉ ስለመሆኑም ነው ያነሱት።

የበዓሉ መከበር የቱሪዝም እንቅስቃሴውን ለማነቃቃት የሚያስችል በመሆኑ በዓሉን ለማክበር ወደ ከተማዋ ለሚመጡ ዕንግዶች ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር በመተባበር የጉዞ አማራጮች እንደሚዘጋጁ ነው የተገለፀው።

‎የአሸንድዬ በዓልን በቅዱስ ላሊበላ ተገኝቶ ማክበር ሌሎች በዙሪያው ያሉ ታሪካዊ ቦታዎችን ለመጎብኝት የሚያስችል በመሆኑ ኢትዮጵያውያንና የውጭ ሃገር ዜጎች አሸንድዬን በቅዱስ ላሊበላ ከተማ ተገኝተው እንዲያከብሩ ዲያቆን አዲሴ ደምሴ ጥሪ አቅርበዋል።



የዩኒቨርሲ ተማሪዎች በዕረፍት ጊዜያቸው ማህበረሰብን ተጠቃሚ በሚያደርጉ የተለያዩ ስራዎች እየተሳተፉ ነው።ቅዱስ ላሊበላ፣ነሐሴ፣4፣2018(ቅዱስ ላሊበላ ኮሙኒኬሽን) ከተለያዩ ከፍተኛ የትምህርት...
10/08/2026

የዩኒቨርሲ ተማሪዎች በዕረፍት ጊዜያቸው ማህበረሰብን ተጠቃሚ በሚያደርጉ የተለያዩ ስራዎች እየተሳተፉ ነው።

ቅዱስ ላሊበላ፣ነሐሴ፣4፣2018(ቅዱስ ላሊበላ ኮሙኒኬሽን) ከተለያዩ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በክረምት ወደ ቤተሰቦቻቸው የተመለሱ ተማሪዎች የዕረፍት ጊዜያቸውን ማህበረሰብን በሚጠቅም ስራ እያሳለፉ ነው።

ወጣቶቹ በችግኝ ተከ፣በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራ፣ የቅርስ ከባቢን በማስዋብና በሌሎች የስራ ዘርፎች ነው እየተሳተፉ ያሉት።

የቅዱስ ላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት ከባቢን በማስዋብና በሌሎችም የስራ ዘርፎች ከተሰማሩት መካከል በደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ ትምህርቱን እየተከታተለ ያለው ተማሪ ሙሉቀን ግርማ በዕረፍት ጊዜያቸው ማህበረሰብን ተጠቃሚ በሚያደርጉ ስራዎች መሰማራታቸውን ነው የገለፀው።

ለአካባቢያችን ልማት የበኩላችን ለማበርከት የዕረፍት ጊዜያችን በመጠቀማችን ደስተኞች ነን ነው ያለው።

ሌላኛዋ የወሎ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዋ ሰብለ ወንጌል አበበ በቅርስ ዙሪያ እየተሰሩ ያሉ የልማት ስራዎችን በማገዝና ለማህበረሰቡ ምቹ ለማድረግ በስራው መሳተፋቸውን ነው የገለፀችው።

ተማሪዎች በከረምት በሚኖራቸው የዕረፍት ስዓት ጊዜያቸውን ማህበረሰብን በሚጠቅም ስራ እንዲያሳልፉ ለማድረግ፣በቅዱስ ላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት ከባቢን የማስዋብና አነስተኛ ዕርከኖችን እንዲሰሩ እየተደረገ ስለመሆኑ የገለፁት የቅዱስ ላሊበላ ባህል፤ ቱሪዝምና ስፖርት ፅህፈት ቤት የቅርስ ጥበቃና እንክብካቤ ባለሙያው ሙሉጌታ ወዳጀ ናቸው።

በፈረንሳይ ኢትዮጵያ ዘላቂ የቅርስ አድን ፕሮጀክት እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን ተማሪዎች እንዲመለከቱ በማድረግ በቅርሱ ዙሪያ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች ላይ እውቅና እንዲኖራቸው እየተደረገ ስለመሆኑም ነው ያነሱት።

በከተማ አስተዳደሩ 250 የሚሆኑ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የዕረፍትጊዜያቸውን ተጠቅመው ማህበረሰብን የሚጠቅሙ ስራዎች ላይ መሰማራታቸውም ነው የተመላከተው።

ፕሮጀክቱ ከዋናው ስራ በተጨማሪ የበጎ አድራጎት ስራዎችን በከተማው እያከናወነ ያለ ሲሆን የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን በማስተባበር የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራዎችን እያከናወነ ነው።

የቅዱስ ላሊበላ ጠቅላላ ሆስፒታልን አገልግሎት ለማዘመን የድርሻቸውን እንደሚወጡ የከተማዋ ነዋሪዎች ገለፁ።ቅዱስ ላሊበላ፣ነሐሴ፣ 1፣2018(ቅዱስ ላሊበላ ኮሙኒኬሽን) ለ25 አመታትና በላይ በላ...
07/08/2026

የቅዱስ ላሊበላ ጠቅላላ ሆስፒታልን አገልግሎት ለማዘመን የድርሻቸውን እንደሚወጡ የከተማዋ ነዋሪዎች ገለፁ።

ቅዱስ ላሊበላ፣ነሐሴ፣ 1፣2018(ቅዱስ ላሊበላ ኮሙኒኬሽን) ለ25 አመታትና በላይ በላስታ ላሊበላ ከ1.5 ሚሊየን በላይ ማህበረሰብን እያገለለ ያለው የቅዱስ ላሊበላ ጠቅላላ ሆስፒታል እንዲሟሉለት ሲጠይቃቸው ከነበሩት የህክምና መሳሪያዎች ሲቲ ስካን ቀዳሚው ነው።

የህክምና መሳሪያው ባለመኖሩ ለምርመራ ሲባል የአካባቢው ማህበረሰብ ወልዲያ፣ደሴና ባህርዳር ለመሄድ ሲገደድ ቆይቷል።

ይህ የህክምና መሳሪያ አለመሟላት ማህበረሰቡ ለእንግልትና ለአላስፈላጊ ወጭም ሲዳረግ መቆየቱን ነው የህክምና ባለሙያዎች የሚገልፁት።

የክልሉ ጤና ቢሮ ችግሩን ለመቅረፍ የሲቲ ስካን የህክምና መሳሪያ ለሆስፒታሉ መስጠቱንም ነው ሆስፒታሉ ያስታወቀው።

በሆስፒታሉ ስታንዳርዱን የጠበቀ የሲቲ ስካን ህክምና ማሽን አገልግሎት መስጫ ለመገንባት ከልዩ ልዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ጋር ውይይት ተደርጓል።

የውይይቱ ተሳታፊዎች የህክምና ማሽኑ ባለ መሟላቱ ማህበረሰቡ ለከፋ እንግልት ሲዳረግ መቆየቱን ነው ያነሱት።

የጤና ቢሮው የህክምና መሳሪያውን ድጋፍ በማድረጉ ደስተኛ መሆናቸውን ነው የከተማዋ ነዋሪዎች የገለፁት።

የሆስፒታሉን አገልግሎት አሰጣጥ ለማዘመን በሚደረገው ርብርብም የድርሻቸውን እንደሚወጡ ነው የገለፁት።

በሆስፒታሉ የሚነሱ የሰው ሃይል፣የህክምና መሳሪያ ዕጥረቶችም ሊቀረፋ እንደሚገባም ነው ያመላከቱት።

ማህበረሰብን ለማዳን ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣም ነው ጥሪ የቀረበው።

የሰሜን ወሎ ዞን ብልፅግና ፓርቲ የፖለቲካ ዘርፍ ሃላፊው ወንድምነው ወዳጅ የሆስፒታሉን የህክምና ማሽን አገልግሎት መስጫ ግንባታ ለማከናወን ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ ነው ያሳሰቡት።

የሚሰሩ የልማት ስራዎችን በራስ አቅም ለመስራት ማህበረሰቡ ትኩረት እንዲያደርግም ነው ሃላፊው የገለፁት።

የህክምና መሳሪያው በወቅቱ ለታለመለት አላማ እንዲውልም ማህበረሰቡ የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ነው የጠየቁት።

የህክምና መሳሪያው የማህበረሰቡ የቆየ ጥያቄ መሆኑን ያነሱት የላስታ ወረዳ አስተዳዳሪ ኢንጂነር ለዓለም ብርሃኑ የክልሉ መንግስት እንዲሟላ በማድረጉ ምስጋና አቅርበዋል።

የህክምና መሳሪያው አገልግሎት የሚሰጥበትን ግንባታ ለመስራት በማህበረሰቡ፣በአካባቢው መንግስትና በረጅ ድርጅቶች ድጋፍ ለማከናወን እየተሰራ ስለመሆኑም ነው ያነሱት።

በሃገር ውስጥና በውጭም ያሉ የአካባቢው ተወላጆች ድጋፍ እንዲያደርጉም ነው ጥሪ ያቀረቡት።

የቅዱስ ላሊበላ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና የትምህርት ፅህፈት ቤት ሃላፊው ፈንታው አባተ በበኩላቸው የህክምና መሳሪያው መሟላት የነበረውን ችግር የሚቀርፍ ስለመሆኑ ነው ያነሱት።

የህክምና መሳሪያው አገልግሎት የሚሰጥበትን ግንባታ ለማከናወን ማህበረሰብን ያሳተፈ ስራ ይሰራል ነው ያሉት።

የህክምና መሳሪያው አለመሟላት ማህበረሰቡን ለእንግልት፣ ለአላስፈላጊ ወጭ ዳርጎ ስለመቆየቱ ያነሱት ደግሞ የሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ መሰለ ተፈራ ናቸው።

በጤና ቢሮው የተደረገው ድጋፍ ችግሩን ይቀርፋልም ነው ያሉት።

የህክምና አገልግሎት መስጫ ግንባታው 50 ሚሊየን ብር ገደማ በጀት የሚያስፈልገው በመሆኑ ይሄን ለመሸፈን በሃገር ውስጥና በውጭ ያሉ የአካባቢው ተወላጆች ድጋፍ እንዲያደርጉም ነው የጠየቁት።

ድጋፍ ለሚያደርጉ አካላት ሆስፒታሉ በቀጣይ የባንክ አካውንት ይፋ እንደሚያደርጉም ነው ስራ አስኪያያጁ የገለፁት።

ለሃገር ሰላም በቁርጠኝነትና በታማኝነት ማገልገል ያስፈልጋል።ቅዱስ ላሊበላ፦ሃምሌ፣30፣2018(ቅዱስ ላሊበላ ኮሙኒኬሽን) የቅዱስ ላሊበላ ከተማ፤የላስታና የቡግና ወረዳዎች ለተከታታይ ቀናት ሲያ...
06/08/2026

ለሃገር ሰላም በቁርጠኝነትና በታማኝነት ማገልገል ያስፈልጋል።

ቅዱስ ላሊበላ፦ሃምሌ፣30፣2018(ቅዱስ ላሊበላ ኮሙኒኬሽን) የቅዱስ ላሊበላ ከተማ፤የላስታና የቡግና ወረዳዎች ለተከታታይ ቀናት ሲያሰለጥኗቸው የቆዩትን"የደጀን ሃይል"አባላትን አስመርቀዋል።

በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ የሶስቱም ወረዳ የስራ ሃላፊዎች፣የሃገር መከላከያ ሰራዊት ከፍተኛ መኮንኖች እና የሰሜን ወሎ ዞን የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።

የሰሜን ወሎ ዞን ብልፅግና ፓርቲ የፖለቲካ ዘርፍ ሃላፊ ወንድምነው ወዳጅ ሃገርን ለመጠበቅ ተመራቂ የደጀን ሃይል አባላት የድርሻቸውን እንዲወጡም አሳስበዋል።

በቁርጠኛ ስነ ልቦና፣በዳበረ ዕውቀት ሃገርን ማገልገል እንደሚገባም ነው ያመላከቱት።

የሃገርን ሰላም ለማስቀጠል ተመራቂዎች የድርሻቸውን እንዲወጡም ነው የጠየቁት።

የሰሜን ወሎ ዞን ፖሊስ መምሪያ የወንጀል ምርመራ መምሪያ ምክትል አዛዥ ኮማንደር እንግዳው ሆዴነው በበኩላቸው ተመራቂ የደጀን ሃይል አባላት የተሰጣቸውን የስነ-ልቦና፣የአካል ብቃትና ወታደራዊ ስልጠና ወደ ተግባር መቀየር ያስፈልጋል ነው ያሉት።

የፖሊስ ስራዊት፣የሚሊሻና የፀጥታ አካላቱ የሃገራቸውን ሰላም ለማረጋገጥ እንደሚሰሩም ነው የተናገሩት።

የሃገር መከላከያ ሰራዊት የ803ኛ ኮር አዛዥ ብርጋዴር ጀነራል አብርሃም ሞሲሳ፦ሰልጣኞች ከስልጠናው ያገኙትን ዕውቀት እና ክህሎት በመጠቀም አሁን ላይ ያለውን አንፃራዊ ሰላም ለማስቀጠል መስራትና ለሃገር ሰላም በቁርጠኝነትና በታማኝነት ማገልገል እንደሚጠበቅባቸው ነው ያሳሰቡት።

"ሰልጣኞች ለሃገር ሰላም ፊተኛ ተሰላፊ በመሆናችሁ" በወታደራዊ ታማኝነት፣በቁርጠኝነትና በስነ ልቦና በመጠንከር ግዳጅን መወጣት ይገባችኋል ሲሉም የስራ መመሪያ ሰጥተዋል።

በመድረኩ ለስልጠናው ውጤታማነት ጉልህ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ባለድርሻ አካላትና ሰልጣኞች የዕውቅና እና የምሥጋና የምስክር ወረቀት ተበርክቷል።

Address

Lalibela

Opening Hours

16:30 - 17:00

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Lalibela Government Communication Affairs Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share