Mehal Meda City Adminstration Revenue Office

Mehal Meda City Adminstration Revenue Office Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Mehal Meda City Adminstration Revenue Office, Government Organization, Mehal Meda.

27/03/2023

የመ/ሜዳ ከተማ አስተዳደር ገቢ ፅ/ቤት "ዘመቻ ገቢ"በሚል ስያሜ ከመጋቢት 1 እስከ15 ያደረገውን የተቀናጀ ገቢ የመሰብሰብ እንቅስቃሴ ያመጣውን ውጤት ገመገመ

የመ/ሜዳ ከተማ አስተዳደር ገቢ ፅ/ቤት የገቢ አፈፃፀሙን ለማሳደግ ከተለመደው አሰራር በተለየ መንገድ አመራሩን ፣ባለሙያውን ፣አጋርና ባለድርሻ አካላትን ሊያሳትፍ የሚችል የንቅናቄ እቅድ በማቀድና ለአመራሩ አቅርቦ እውቅና በማሰጠት በእቅዱ መሰረት ለ15 ቀን የተቀናጀ ተግባራትን አከናውኗል፡፡ በ15 ቀኑ በተከናወነው የንቅናቄ ስራ የተፈፀሙ ተግባራትና የተገኘውን ውጤት በአመራሩ እንዲሁም በተቋሙ ማኔጅመንት ተገምግሟል፡፡በግምገማውም የተነሱ ሀሳቦች፡-
በቅድመ ስምሪት የተከናወኑ ተግባራት
 የንቅናቄ እቅድ በማዘጋጀት አመራሩ የጋራ እንዲያድገው ተደርጓል፡፡
 ማህበረሰቡ እውቅና እንዲኖረው ለግማሽ ቀን በሞንታርቦ ቅስቀሳ ተደርጓል እንዲሁም ህዝብ በሚሰበሰብባቸው ዋናዋና ቦታዎች ማስታወቂያዎችንና ቀስቃሽ ሞቶዎችን በመለጠፍ መረጃው ለማህበረሰቡ ተደራሽ እንዲሆን ተደርጓል፡፡
 ከባለሙያዎች፤ከማኔጅመንት አባላት ከአጋር ሴክተሮች የተውጣጣ ቡድን በሁለት ቀጠና በመመደብ ስምሪት በመስጠት ወደስራ ተገብቷል፡፡
 ገቢ ሊገኝባቸው የሚችሉ አርእስቶች ተለይተው ቼክሊስት በማዘጋጀት ወደ እንቅስቃሴ ተገብቷል፡፡
በስምሪት ወቅት የተከናወኑ ተግባራት
• ውዝፍ የፈጠረ አንድ ግብር ከፋይ ላይ ሀብት የማስከበር ስራ በመስራት ያልተከፈለው ግብር ውስጥ በውለታ ቅድሚያ ክፍያ 80,000 እንዲከፈል ማድረግ ተችሏል
• የልዩነት ውሳኔ ተወስኖ ካለከፈሉ 3 ግብር ከፋዮች 2 እንዲከፍሉ ማድረግ ተችሏል፡፡
• የሊዝ ውዝፍ ካልከፈሉ 184,656 ብር ገቢ ተደርጓል፡፡
• የአገልግሎት ክፍያ ያልከፈሉ 48 ግብር ከፋዮች ማስከፈል ተችሏል ፡፡
• ታክስ ካጭበረበረ አንድ ግብር ከፋይ ተከታትሎ 237,000 ብር ማስከፈል ተችሏል፡፡
• ዳግም ውሳኔ ከተወሰነባቸው 35 ግብር ከፋዮች 270,200.07ብር ማስከፈል ተችሏል፡፡
• የደረጃ "ሐ" ግብር ከፋዮችን መረጃ በየቀበሌው የማጥራት፣አዳዲስ ግብር ከፋዮችን የመለየት ስራ ተከነውኗል፡፡
በተከናወኑ ተግባራት የተሰበሰበ አጠቃላይ ገቢ
 መደበኛ ገቢ
• ከስምሪት በፊት የተሰበሰበ 19,360,348 በ15 ቀኑ የገባ 1,797,793.48 እስከ መጋቢት 15 የተደረሰበት 21,158,141.48
 የአገልግሎት ገቢ
• ከስምሪት በፊት የተሰበሰበ 16,081,528.06 በ15 ቀኑ የገባ 345,439.9 እስከ መጋቢት 15 የተደረሰበት16,426,967.96
 ጠቅላላ ገቢ

• ከስምሪት በፊት የተሰበሰበ 35,441,876.06 በ15 ቀኑ የገባ 2,143,233.38 መጋቢት 15 የተደረሰበት 37,585,109.44 በመሰብሰብ አፈፃፀሙን 98.3% ማድረስ ተችሏል፡፡
በአጠቃላይ የገቢ ተቋሙ ያደረገው የተቀናጀ እንቅስቃሴ ውጤታማ እንዲሆን ተግባሩ እንዲሳካ ያስተባበሩ በእንቅስቃሴው ለተሳተፉ ሰራተኞች ምስጋና እያቀረበ በቀሪ ወራትም የታቀደውን እቅድ ሙሉ በሙሉ ለማሳካት የተጀመረውን እንቅስቃሴ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡

የመ/ሜዳ ከተማ አስተዳደር ገ/ፅ/ቤት ግ/ት/ኮ/ዋ/የስራ ሂደት
መጋቢት18/2015
መ/ሜዳ

27/03/2023

የታክስ ክሊራንስ ምስክር ወረቀት ከመሰጠቱ በፊት ኦዲት የሚያስፈልጋቸው አገልግሎቶች
የሚሸጠው ወይም የሚተላለፈው የንግድ ሥራ ሀብት ከሃምሳ በመቶ ያነሰ ከሆነ የታክስ ክሊራንስ ምስክር ወረቀት ከመሰጠቱ በፊት አገልግሎት ኦዲት ሥራ መከናወን አለበት፡፡
በከፍተኛ እና በመካከለኛ ግብር ከፋዮች ቅ/ጽ/ቤት የሚስተናገድ ታክሰ ከፋይ በግብር ዘመኑ መካከለኛ እና ዝቅተኛ የስጋት ደረጃ ላይ የሚገኝ ከሆነ በሚከተሉት አገልግሎቶች ላይ የታክስ ክሊራንስ ምስክር ወረቀት ከመሰጠቱ በፊት አገልግሎት ኦዲት መደረግ አለበት፤
 ከሃምሳ በመቶ በላይ የንግድ ሥራ ሀብት ለመሸጥ ወይም ለማስተላለፍ፣
 ድርጅትን በከፊልም ሆነ በሙሉ ለመዝጋት፣
 የንግድ ዘርፍ ለመቀየር ወይም ለመቀነስ ከሆነ፡፡
በተጨማሪም በከፍተኛ እና በመካከለኛ ግብር ከፋዮች ቅ/ጽ/ቤት የሚስተናገድ ታክስ ከፋይ በግብር ዘመኑ በከፍተኛ የስጋት ደረጃ ላይ የሚገኝ ከሆነ በሚከተሉት አገልግሎቶች ላይ የታክስ ክሊራንስ ምስክር ወረቀት ከመሰጠቱ በፊት አጠቃላይ ኦዲት መደረግ አለበት፣
 ከሃምሳ በመቶ በላይ የንግድ ሥራ ሀብት ለመሸጥ ወይም ለማስተላለፍ፣
 ድርጅትን በከፊልም ሆነ በሙሉ ለመዝጋት፣
 የንግድ ዘርፍ መቀየር ወይም መቀነስ ከሆነ፣
 ድርጅቶች በአንድ ላይ ለመደራጀት ወይም ለመዋሀድ በውህደት የሚፈጠረው ድርጅት የተዋሀደውን ድርጅት የታክስ ዕዳን ለመክፈል ግዴታ ገብቶ የሚዋሃዱ ስለመሆኑ የሚያስረዳ ሰነድ ከቀረበ፣
 የንግድ መደብሩን ለሶስተኛ ወገን በሽያጭ፣ በስጦታ ወይም በውርስ ለማስተላለፍ፣
በየትኛውም የስጋት ደረጃ ላይ የሚገኝ የአነስተኛ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ታክስ ከፋይ የታክስ ክሊራንስ ምስክር ወረቀት እንዲሰጠው ሲጠይቅ ከሀምሳ በመቶ በላይ የሆነውን የንግድ ሥራ ሀብቱን ወይም የንግድ መደብሩን ለሶስተኛ ወገን በሽያጭ፣ በስጦታ ወይም በውርስ ለማስተላለፍ ወይም የንግድ ሥራውን ለማቋረጥ ካልሆነ በስተቀር በአገልግሎት ኦዲት ብቻ የሚስተናገዱ ይሆናል፡፡
የአነስተኛ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ታክስ ከፋይ ከሀምሳ በመቶ በላይ የሆነውን የንግድ ሥራ ሀብቱን ወይም የንግድ መደብሩን ለሶስተኛ ወገን በሽያጭ፣ በስጦታ ወይም በውርስ ለማስተላለፍ ወይም የንግድ ሥራውን ለማቋረጥ የክሊራንስ የምስክር ወረቀት ጥያቄ በሚያቀርብበት ጊዜ አጠቃላይ ኦዲት ተከናውኖ ዕዳ የሌለበት መሆኑ ሲረጋገጥ የታክስ ክሊራንስ ምስክር ወረቀቱ ይሰጠዋል፡፡

25/03/2023

ታክስን/ግብርን ዘግይቶ መክፈል የሚያስከትለው ቅጣት
ታክስዎን/ግብርዎን በወቅቱ ሲከፍሉ ከብዙ እንግልት ከመዳንዎ በተጨማሪ አላስፈላጊ ቅጣት ከመቀጣት ይድናሉ፡፡ ግብርን በወቅቱ ከከፈሉ ደግሞ ለሀገርዎ እና ለእርስዎ የሚጠቅመውን በወቅቱ እና በአስፈላጊው ወቅት እንዳደረጉ ይቆጠራል፡፡
ታክስዎን በተለያየ ምክንያት ሳይከፍሉ ካዘገዩ ከሚደርስብዎት ውጣ ውረድ በተጨማሪ ቅጣቶችንም ለማስተናገድ ይገደዳሉ፡፡ ከነኚህ ቅጣቶች ውስጥ ለእርስዎ ለግንዛቤ ይረዳዎት ዘንድ የሚከተሉት ተቀንጭበው ቀርበዋል፡፡
ማንኛውም ታክስ ከፋይ በታክስ መክፈያ ጊዜው ውስጥ ታክስ ሳይከፍል ከቀረ ለዘገየበት ጊዜ፦
1. ለአንድ ወር ወይም የወሩ ከፊል ለሆነው ጊዜ ባልተከፈለው ታክስ ላይ 5% (አምስት በመቶ)፤ እና
2. ከዚያ በኋላ ለዘገየበት ለእያንዳንዱ ወር ወይም የወሩ ከፊል ለሆነው ጊዜ ባልተከፈለው ታክስ ላይ ተጨማሪ 2% (ሁለት በመቶ)፤ ቅጣት ይከፈላል፡፡
I. የሚጣለው የቅጣት መጠን ከዋናው የታክስ ዕዳ መብለጥ የለበትም፡፡
II. መከፈል በማይገባው ታክስ ላይ ሳይከፈል በዘገየበት የተጣለ ቅጣት ለታክስ ከፋዩ ይመለሳል፡፡
III. ታክስን ዘግይቶ መክፈል የሚያስከትለው ቅጣት ከተከፋይ ሂሣብ ላይ ተቀንሶ ከሚከፈል ታክስ ጋር በተገናኘ የሚጣል ቅጣት በሚመለከተው ያልተከፈለ ታክስ ላይ ተፈጻሚ አይሆንም፡፡

25/03/2023

ሀሰተኛ ሰነድ አቅርበሻል በማለት ከአንድ ግብር ከፋይ ግለሰብ 70ሺ ብር ጉቦ የተቀበለ የገቢዎች ባለሙያን እጅ ከፍንጅ መያዙን እና በወንጀሉ ተባባሪ የሆነ አንድ ባለሙያን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ፡፡

በቂርቆስ ክ/ከተማ የአነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅርጫፍ ጽ/ቤት የአወሳሰን ባለሙያ የሆነው አንድ ሰራተኛ የቅርጫፍ ጽ/ቤቱ ግብር ከፋይ የሆኑ ግለሰብን ካቀረብሽው 10 ደረሰኞች መካከል 8ቱ የተበላሹ በመሆኑ ወደ አጣሪ ኮሚቴ መላኩንና ሁለቱ ደግሞ እጄ ላይ ይገኛሉ በማለት ጉዳዩን ለማዳፈን ግን 100ሺ ብር ጉቦ እንዲሰጠው ይጠይቃል፡፡ የግል ተበዳይ ያቀረቧቸው ሰነዶች ትክክለኛ እንደሆኑ ለማስረዳት ቢሞክሩም ባለሙያው ሳይቀበላቸው ይቀራል፡፡ የአወሳሰን ባለሙያ የሆነው ይህው ግለሰብ በቢሮ ስልክ ደጋግሞ በመደወል የግል ተበዳይን በማስጨነቅ በህግ እንደሚጠየቁ በማስፈራራት 70ሺ ብር ለመቀበል ይስማማል፡፡

የግል ተበዳይ ጉዳዩን ለተቋሙ ኃላፊዎች በማሳወቅ በቂርቆስ ክፍለ ከተማ የደንበል አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ ባደረገው ክትትል በቅርጫፍ ፅ/ቤቱ የአወሳሳን ባለሙያ የሆነው ሙያተኛ 22 አካባቢ ከሚገኘው መስቲ ሬስቶራንት አካባቢ ሚዚያዚያ 13 ቀን 2015 ዓ/ም ገንዘቡን ሲቀበል እጅ ከፍንጅ መያዙን እና የዚህ ወንጀል ተባባሪ የሆነው በተቋሙ የጥቆማ አቀባበል ባለሙያ ከፍተኛ ኦፊሰር የሆነው ሰራተኛ ደግሞ በተመሳሳይ ቀን በጉቦ የተገኘውን ገንዘብ ሲቀበል መገናኛ አካባቢ እንደተያዘ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡

የመ/ሜዳ ከተማ አስተዳደር ገቢ ፅ/ቤት ለተቋሙ ሰራተኞች  ስልጠና ሰጠስልጠናው የተሰጠው  በቀን  12/7/2015  ሲሆን  ስልጠናውን  የፅ/ቤቱ ሀላፊ የሆኑት  ወ/ሪት  በለጠች  በቀለ  የ...
22/03/2023

የመ/ሜዳ ከተማ አስተዳደር ገቢ ፅ/ቤት ለተቋሙ ሰራተኞች ስልጠና ሰጠ
ስልጠናው የተሰጠው በቀን 12/7/2015 ሲሆን ስልጠናውን የፅ/ቤቱ ሀላፊ የሆኑት ወ/ሪት በለጠች በቀለ የከፈቱት ሲሆን በመክፈቻ ንግግራቸውም ስልጠናው የተዘጋጀው የተቋሙ ሰራተኞች አዳዲስ በሚወጡ መመሪያዎች ላይ ግልፀኝነት እንዲኖራችው ታስቦ መሆኑን አንስተው ስልጠናውን በአንክሮ እንዲከታተሉ አሳስበው ወደ ስልጠናው ተገብቷል፡፡
የእለቱን ስልጠና እንዲሰጡ የተመረጡት የገቢ አሰባሰብ የስራ ሂደት የግብር አወሳሰን ባለሙያ የሆኑት አቶ እሸቱ ታለ ሲሆኑ ስልጠና የተሠጠበትም ርዕስ፡-
 የትራንስፖርት ስመ- ንብረት ዝውውር መመሪያ ቁጥር አገቢ21/2015
 የደላላ መመሪያ አገቢ19/2015 እና በተሻሻለው መመሪያ ቁጥርአገቢ 20/2015
ላይ ሲሆን አሰልጣኙ ሰልጣኞች ሊያውቋቸው የሚገቡ ዋና ዋና ነጥቦችን በገለፃ አቅርበው እንዲሁም የግብር አወሳሰኑን በምሳሌ ልምምድ በማድረግ ግልፀኝነት እንዲያዝበት ተደርጓል፡፡ ሰልጣኞችም ግልፀኝነት በጎደላቸው ጉዳዮች ላይ ጥያቄዎችን አንስተዋል በተለይ ደግሞ የተሸከርካሪ ግምት የሚሰሩ ኮሚቴዎች በተገቢው እውቀት ላይ ተመስተው ከመገመት አንፃር ክፍተት ስላለው በደንብ ሊጤን እንደሚገባው አስተያየት ሰጥተዋል በአጠቃላይም ስልጠናውን በተመለከተ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት በተለይ ተቋሙን በአዲስ ለተቀላቀሉ ሰራተኞች ከአዋጁ ጀምሮ ስልጠና መሰጠት እንዳለበት አንስተዋል በመጨረሻም ስልጠናው ቀጣይነት እንዳለው እንዲሁም ሰራተኞች የንባብ ባህላቸውን በማጎልበት ራሳቸውን ማብቃት እንደሚጠበቅባቸው ማጠቃለያ ተሰጥቶ ስልጠናው ተጠናቋል፡፡

የመ/ሜዳ ከተማ አስተዳደር ገ/ፅ/ቤት ግ/ት/ኮ/ዋ/የስራ ሂደት
መጋቢት12/2015

17/03/2023
09/03/2023

የመ/ሜዳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ፅ/ቤት የከተማ አስተዳደሩን ገቢ ሊያሳድግ የሚችል ውይይት ከአጋር አካላት ጋር አደረገ፡፡
ውይይቱ የተካሂያደው በ29/6/2015 ሲሆን ውይይቱን የመሩት የመ/ሜዳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ችሮታው ሹመት ሲሆኑ በውይይቱም ላይ ገቢን በማሳድግ ተሳትፎ ያላቸው የ4ቱም ቀበሌ አስተዳዳሪዎች፣ የመሰረተ ልማት ሀላፊና የተመረጡ ሰራተኞች፣የገንዘብና ኢኮኖሚ፣ንግድ ገበያ ልማት፣ሰላምና ደህንነት፣ፖሊስፅ/ቤት ሀላፊዎች እንዲሁም የገቢ ፅ/ቤት ሀላፊና የማኔጅመንት አባላት ተሳትፈዋል፡፡
የውይይቱም ዋና አላማ በገቢ ፅ/ቤቱ " ዘመቻ ገቢ" ከመጋቢት 1 እሰከ መጋቢት 15 የሚል ስያሜ የተሰጠው የንቅናቄ እቅድ ላይ በመወያየት ማዳበርና በእቅዱ መሰረት ወደ ተግባር በመግባት ለውጥ ማምጣት ነው፡፡
በዚህም መሰረት የገቢ ፅ/ቤት ሀላፊ የሆኑት ወ/ሪት በለጠች በቀለ በንቅናቄ እቅዱ የተቀመጡ በእያንዳንዱ የገቢ ርዕስ ገቢ ሊያስገኙ የሚችሉ አማራጮች እንዲሁም ገቢውን ለማግኘት የተቀመጡ አሰራሮችን እና ከእያንዳንዱ ተሳታፊ ገቢውን ለማግኘት የሚጠበቁ ተግባራትን በዝርዝር አቅርበውና ሰፊ ውይይት ተደርጎበትና ከተሳታፊዎች እቅዱን ሊያዳብሩ የሚችሉ ሀሳቦች ታክሎበት ፀድቋል፡፡
እቅዱንም መሬት ማሳረፍ ይቻል ዘንድ የከተማና የቀበሌ አመራሩን፣የገቢ ተቋም ማኔጅመንትና ሰራተኞችን እንዲሁም ከየሴክተሩ አጋዥ የሚሆኑ ባለሙያዎችን ያካተተ ስምሪት በየቀበሌው ተሰጥቷል፡፡
ተግባሩንም በኮሚኒኬሽን ማጀብ ለውጤት መምጣት የራሱ ድርሻ ስላለው በቀን 30/6/2015 በሞንታርበሮ ቅስቀሳ እንዲካሂያድ እንዲሁም ቀስቃሽ መልእክቶች ህዝብ በሚገኝባቸው ቦታዎች እንዲለጠፉ፣ሶሻል ሚዲያን በመጠቀም መረጃው ለህዝቡ ተደራሽ እንዲደረግ እንዲሁም ተግባሩ ሲከናወን ስለሚኖር የክትትልና ድጋፍ ስርዓት አቅጣጫ ተቀምጦ ውይይቱ ተጠናቋል፡፡
የመ/ሜዳ ከተማ አስተዳደር ገ/ፅ/ቤት ግ/ት/ኮ/ዋ/የስራ ሂደት
መጋቢት29/2015
መ/ሜዳ

09/02/2023

የመ/ሜዳ ከተማ አስተዳደር ገቢ ፅ/ቤት ከመ/ሜዳ ከተማ አስተዳደር ስራና ስልጠና ፅ/ቤትና የመሰረተ ልማት ፅ/ቤት ጋር በጋራ በመሆን በ1/6/2015 አዲስ ለተደራጁ 4 የደረጃ ሀ ግብር ከፋይ ለሆኑ ማህበራት አመራሮች ስራ ከመጀመራቸው በፊት በታክስ ህጎች ላይ ግልፀኝነት መፍጠር የሚያስችል የግንዛቤ ፈጠራ መድረክ አካሄደ፡፡
የግንዛቤ መፍጠሪያ መድረኩን ማዘጋጀት ያስፈለገበት ዋነኛ አላማ ማህበራቱ ወደ ስራ ከመግባታቸው በፊት የታክስ ህጎችን በአግባቡ እንዲረዱ ማድረግ ማህበራቱ አላፈላጊ ከሆነ የህግ ተጠያቂነት እና ወጪ እንዲሁም መንግስት ማግኘት ያለበትን ገቢ በአግባቡ እንዲያገኝ ለማድረግ ትልቅ ፋይዳ ያለው በመሆኑ ነው፡፡
ውይይቱም የመ/ሜዳ ከተማ አስተዳር ግብር ት/ት ኮሚኒኬሽን የስራ ሂደት ባዘጋጀው ሰነድ አማካኝነት የስራ እና ስልጠና ፅ/ቤት የሆኑት አቶ ደረሰ ሙላቴና የገቢ ፅ/ቤት ሀላፊ የሆኑት ወ/ሪት በለጠች በቀለ በጋራ የመሩት ሲሆን በውይይቱ የተሳተፉት የመሀበራቱ አመራሮች ግልፅ ያልሆኑላቸውን ጥያቄዎች አንስተው ምላሽ ተሰጥቷቸዋል በውይይቱም ማጠቃለያ ለተሳታፊዎች አንብበው የበለጠ ግልፀኝ እንዲኖራቸው የውይይቱን ጭብጥ የያዘ በራሪ ወረቀት በመስጠጥ የእለቱ ውይይት ተጠናቋል፡፡

"ግብር የኔም የአንተም፣የአንችም፣የሁላችንም ጉዳይ ነው!!
የመ/ሜዳ ከተማ አስተዳደር ገ/ፅ/ቤት ግ/ት/ኮ/ዋ/የስራ ሂደት
የካቲት 1/2015
መ/ሜዳ

27/01/2023

የታክስ ደረሰኝ አጠቃቀምና አስተዳደርመመሪያ ቁጥር አገቢ 13/2012
 መግቢያ
መንግስት የታክስ ሰርአቱን ለማሳለጥ የተለያዩ አዋጆች፣ መመሪያና ደንቦችን በስራ ላይ እንዲውሉ እያደረገ ይገኛል ፡፡ከወጡ መመሪያወች መካከል አንዱ የታክስ ደረሰኝ አጠቃቀምና አስተዳደር መመሪያ ቁጥር አገቢ 13/2012 ነው ፡፡ይህም መመሪያ በውስጡ አጠቃላይ የታክስ ደረሰኝ አጠቃቀም የሚመለከቱ በርካታ አንቀፆችን የያዘ ሲሆን በመመሪያው ከተካተቱ አንቀፆች አንዱ የሂሳብ መዝገብ የሚይዙ ታክስ ከፋዮች የሂሳብ መዝገብ የመያዝ ግዴታ ከሌለባቸው ወይንም በንግድ ስራ ካልተሰማራ ግለሰብ ግብይት ሲፈፅሙ እንዴት መፈፀም እንዳለባቸው ይደነግጋል ፡፡በመሆኑም በመ/ሜዳ ከተማ አስተዳደር ገቢ ፅ/ቤት ሂሳብ መዝገብ የሚይዙ ግብር ከፋዮች በመመሪያው የተቀመጠውን አሰራር በውል ተገንዝበው ተግባራዊ እንዲያደርጉ ይህ የግንዛቤ መፍጠሪያ ፅሁፍ ተዘጋጅቷል፡፡
 ትርጓሜ
የግዥ ማረጋገጫ ደረሰኝ ማለት በገቢዎች ቢሮ ዕውቅና ለተሰጣቸውና ደረሰኝ ሊቀርብላቸው
ላልቻሉ ግብይቶች ግዥ ስለመፈፀሙ ለማረጋገጥ በገዥው ተዘጋጅቶ በወጪ ማስረጃነት
የሚቀርብ ሰነድ ነው፡፡
 የተፈፃሚነት ወሰን
ይህ መመሪያ የሒሳብ መዝገብ እንዲይዙ በሚገደዱ የደረጃ "ሀ" እና "ለ" ታክስ ከፋይ ወይም በራስ ፍላጎት
የሒሳብ መዝገብ ለሚይዙ የደረጃ "ሐ" ታክስ ከፋዮች እንዲሁም የገቢ ግብር ወይም የተጨማሪ
እሴት ታክስ ቀንሰው ገቢ የማድረግ ኃላፊነት በሕግ የተጣለባቸው ወኪሎች እና በህትመት ድርጅቶች
ላይ ተፈጻሚ ይሆናል፡፡
 የደረሰኝ ህትመት ፈቃድ አሰጣጥ እና የደረሰኝ ይዘት
4. ተቀባይነት ስለሚኖረው ደረሰኝ
1) በዚህ መመሪያ መሰረት ተቀባይነት ያለው እና ጥቅም ላይ የሚውል የታክስ ደረሰኝ የሚባለው፡-
ሀ) ከመታተሙ በፊት የተፈቀደና የተመዘገበ እንዲሁም የብቃት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት
በተሰጠው የማተሚያ ቤት የታተመ ነው፡፡
ለ) በገቢዎች ቢሮ እውቅና ከተሰጠው ማተሚያ ቤት ወይም በገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ
የታተመ ወይም እንዲታተምና ጥቅም ላይ እንዲውል የተፈቀደ ነው፡፡

 የግዥ ማረጋገጫ ደረሰኝ (Purchase Voucher)
1) የሂሳብ መዝገብ የሚይዝ ታክስ ከፋይ የሂሳብ መዝገብ የመያዝ ግዳታ ከሌለባቸው ታክስ ከፋዮች
ወይም በንግድ ስራ ላይ ካልተሰማራ ሰው ጋር ለሚያደርገው ግብይት ከገቢዎች ቢሮ በማስፈቀድ
የወጪ ማስረጃ የግዥ ማረጋገጫ ደረሰኝ (Purchase Voucher) አሳትሞ መጠቀም አለበት፡፡
2) የግዥ ማረጋገጫ ደረሰኝ /Purchase Voucher/ የሚያሳትም ታክስ ከፋይ የሚያሳትመው የግዥ
ማረጋገጫ ደረሰኝ በዚህ መመሪያው አንቀጽ 4 ንዐስ አንቀጽ 1 ላይ በተመለከተው መሠረት
መታተም ያለበት ቢሆንም ልዩ መለያ /Security feature/ እንዲያካትት አይገደድም፡፡
3) የዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 1 አፈጻጸም የግዥ ማረጋገጫ ደረሰኝ (Purchase Voucher)
መጠቀም የሚቻልባቸው ግብይቶች ከዚህ በታች የተመለከቱት ናቸው፡፡
ሀ.) ደረሰኝ መስጠት የማይችሉ በአነስተኛ ወይም በችርቻሮ ደረጃ ዕቃዎችን ከሚያቀርቡ ሲሆን፡
1) የጥቃቅን ዕደጥበብ ሥራዎች፤
2) ለኮንስትራክሽን ሥራ የሚያገለግሉ እንደ ድንጋይ፣ አሸዋ፣ ኖራ፣ እንጨት የመሳሰሉት
ግብዓት አቅራቢዎች፣
3) ለማገዶ የሚያገለግሉ ከሰል እና እንጨት የሚያቀርቡ፤
4) በባህላዊ መንገድ ከሚያመርቱ ገበሬዎች የሚገዛ እንሰሳ፣ እህል፣ ጥራጥሬ፣ አትክልትና
ፍራፍሬ የሚያቀርቡ፤
5) ያገለገለ ወይም የወዳደቁ ዕቃዎች ግዥ፣
6) ቱሪስትን መንገድ ለሚመሩና ለሚያጅቡ፣ የማጓጓዣ እንስሳት ኪራይ ለሚሰጡ፤
ለ.) ከደረጃ "ሐ" ታክስ ከፋዮች ላይ የቤት ኪራይን ጨምሮ የዕቃ ወይም የአገልግልት ግዥ
ሲፈጽሙ
ሐ.) የትራንስፖርት ተሽከርካሪ ኪራይ አገልግሎት፣
መ.) የንግድ ስራ ካቋረጠ ሰው የሚገዛ የንግድ ስራ ሀብት ፣
ሠ.) በሰው ጉልበት የሚሰራ የጫኝና አውራጅ አገልግሎት ፣

4) በዚህ አንቀጽ በንዑስ አንቀፅ 3 የተጠቀሱት ግብይቶች ስለመፈፀማቸው የሚያረጋግጡ የውል
ሰነድ ወይም በግዥ ማረጋገጫ ደረሰኙ ላይ የሻጩን ሥም፣ አድራሻ የያዘ መሆን ያለበት ሲሆን
የደረጃ ‚ሐ‛ ግብር ከፋይ ከሆነ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥሩን መመዝገብ አለበት፡፡
5) በዚህ አንቀጽ ንዐስ አንቀጽ 3 የተደነገገው ቢኖርም በፈቃድ ሰጪ ተቋማት የማምረት ፈቃድ
ወስደው በአነስተኛ ደረጃ ከሚያመርቱ አምራቾች ላይ ለሚፈጸም ግዥ በግዥ ማረጋገጫ ደረሰኝ
(Purchase voucher) ግዥ መፈጸም አይቻልም፡፡
6) በዚህ አንቀጽ ንኡስ አንቀጽ 3 የተደነገገው ቢኖርም ደረሰኝ የማይገኝላቸው ግብይቶች
በመሆናቸው በገዥው የሚሰጥ የግዥ ማረጋገጫ ደረሰኝ /Purchase Voucher/ በመጠቀም
ግብይት የሚፈጸምባቸው ተጨማሪ ዕቃዎች እና አገልግሎቶች ዝርዝር ወደፊት በገቢዎች ቢሮ ይወጣል፡፡

የመ/ሜዳ ከተማ አስተዳደር  ከልዩ ልዩ አጋርና ባለድርሻ አካለት ጋር ውይይት  አካሂያደየመ/ሜዳ ከተማ እድገትን ለማፋጠንና የህዝብ  ተጠቃሚነትን  ለማረጋገጥ  ገቢ የማሳደግ አቅምን  ከጊዜ ...
26/01/2023

የመ/ሜዳ ከተማ አስተዳደር ከልዩ ልዩ አጋርና ባለድርሻ አካለት ጋር ውይይት አካሂያደ
የመ/ሜዳ ከተማ እድገትን ለማፋጠንና የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ገቢ የማሳደግ አቅምን ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሳደጉ መሄድ ለነገ የማይባል ተግባር ነው፡፡
የመ/ሜዳ ከተማ አስተዳደር ገቢ ፅ/ቤትም ይህንን መነሻ በማድረግ ባለፉት 6 ወራት የነበረውን አፈፃፀም እንዲሁም የቀጣይ አቅጣጫ ላይ ከስትሪንግ ኮሚቴ፣ ከታክስ አንባሳደሮች እንዲሁም ከየሴክተሩ ከተውጣጡ አጋር አካላት ጋር በ17/5/2015 ሰፊ ውይይት አካሂዷል፡፡
በእለቱ የተካሄደውን ውይይት የመሩት የመ/ሜዳ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና የንግድ ገ/ልማት ፅ/ቤት ሀላፊ የሆኑት ወ/ሮ ሳምራዊት ምስራቅ ሲሆኑ ለውይይት መነሻ በገቢ ፅ/ቤቱ የተዘጋጀ ሰነድ ወ/ሪት በለጠች በቀለ የገቢ ፅ/ቤቱ ሀላፊ ያቀረቡ ሲሆን በዋነኛነትም በ6ወሩ ገቢ ለመሰብሰብ እቅድ የተያዘባቸው የመደበኛና አገልግሎት ገቢ አፈፃፀም በዝርዝር እንዲሁም ገቢውን በመሰብሰብ ሂደት የነበሩ ጥንካሬዎችና ውስንነቶች ፣እያንዳንዱ ሴክተር የነበረውን ሚና በስፋት አቅርበው ሰፊ ውይይት የተደረገበት ሲሆን በመጨረሻም ወ/ሮ ሳምራዊት ምስራቅ በቀጣይ መከናወን ያለባቸውን ተግባራት በዝርዝር አስቀምጠው ሁሉም ሴክተር በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት በተናጠልና በጋራ የሚመለከተውን ተግባር ትኩረት ሰጥቶ በማከናወን በቀጣይ በውጤት መገናኘት አለብን በሚለው የማጠቃለያ ሀሳብ የእለቱ ውይይት ተጠናቋል፡፡
"ግብር የኔም የአንተም፣የአንችም፣የሁላችንም ጉዳይ ነው!!
የመ/ሜዳ ከተማ አስተዳደር ገ/ፅ/ቤት ግ/ት/ኮ/ዋ/የስራ ሂደት
ጥር18/2015

የመ/ሜዳ ከተማ አሰተዳደር ገቢ ፅ/ቤት የግብዓት ድጋፍ አገኘ የመ/ሜዳ ከተማ አስተዳደር  ገቢ ፅ/ቤት  ከአሁን በፊት  በአካባቢው በተፈጠረ  ጦርነት ምክንያት  ይገለገልበት  የነበረው  ቢሮ...
23/01/2023

የመ/ሜዳ ከተማ አሰተዳደር ገቢ ፅ/ቤት የግብዓት ድጋፍ አገኘ
የመ/ሜዳ ከተማ አስተዳደር ገቢ ፅ/ቤት ከአሁን በፊት በአካባቢው በተፈጠረ ጦርነት ምክንያት ይገለገልበት የነበረው ቢሮ ከነሙሉ ንብረቱ በመቃጠሉ ለስራ አስፈላጊ የሆኑ ግብዓቶች ለማሟላት በርካታ ጥረት ሲያደርግ ቢቆይም ከችግሩ ስፋት የተነሳ እስካሁን ሙሉ በሙሉ ለማሟላት አልተቻለም፡፡
ተቋሙ ካሉበት የግብዓት እጥረቶች መካከልም አንዱ የግብር ከፋዮች ፋይል መደርደሪያ አለመሟላት ነው፡፡ በዚህም የተነሳ ፋይሎች መሬት ላይ ለመደርደር ተገዶ ቆይቷል ይህንን ችግር ያስተዋሉ አቶ ሀይሉ መንግስቴ የተባሉ ግብር ከፋይ በራሳቸው ፍላጎት 23,000(ሃያ ሶስት ሺ ብር )በማውጣት የፋይል መደርደሪያ በማሰራት ለተቋሙ ገቢ አድርገዋል፡፡
ገቢ ተቋሙም አቶ ሀይሉ መንግስቴ የፈፀሙት በጎ ስራ የገቢ ተቋሙን ችግር ከመቅረፍ በዘለለ ለሌሎችም ተምሳሌት የሚሆን በመሆኑ የላቀ ምስጋና ያቀርባል!!

Address

Mehal Meda
1000

Telephone

+251116851142

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Mehal Meda City Adminstration Revenue Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Mehal Meda City Adminstration Revenue Office:

Share