Menz Gera werda Comunication office

Menz Gera werda Comunication  office Ensure smooth flow of information between the Menz Gera Government and the public and facilitate the

በመንዝ ጌራ ምድር ወረዳ አፍተነት ቀበሌ የጓሮ አትክልት ሥርጭት ተደረገመ/ሜዳ፦ ግንቦት 27/2018 (መጌወመኮ)በአማራ ክልል በሰ/ሸዋ ዞን መንዝ ጌራ ምድር ወረዳ የጓሮ አትክልት ሥርጭት ተ...
04/06/2026

በመንዝ ጌራ ምድር ወረዳ አፍተነት ቀበሌ የጓሮ አትክልት ሥርጭት ተደረገ

መ/ሜዳ፦ ግንቦት 27/2018 (መጌወመኮ)

በአማራ ክልል በሰ/ሸዋ ዞን መንዝ ጌራ ምድር ወረዳ የጓሮ አትክልት ሥርጭት ተደርጓል።

በዚህም የጓሮ አትክልት ሥርጭቱ በወረዳው አፍተነት ቀበሌ መደረጉን የወረዳው ም/አስተዳዳሪና የግብርና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዑስማን ኢብራሂም በማህበራዊ ገፃቸው አስፍረዋል።

የጓሮ አትክልት ሥርጭቱ የግብርና ዕድገትን ከማጎልበት ባለፈ የምግብና ሥርዓተ-ምግብ ትግበራን እውን እንደሚያደርግ ይታመናል።

በሶስት ወር የግንባታ ጊዜ የተጠናቀቀው የማህበረሰብ አቀፍ መድሃኒት ቤት ተመረቀ፤መ/ሜዳ፤ግንቦት 27/2018(መጌወመኮ)የመንዝ ጌራ ምድር ወረዳ በበጀት አመቱ በካፒታል በጀት ከሚያስገነባቸው ...
04/06/2026

በሶስት ወር የግንባታ ጊዜ የተጠናቀቀው የማህበረሰብ አቀፍ መድሃኒት ቤት ተመረቀ፤

መ/ሜዳ፤ግንቦት 27/2018(መጌወመኮ)

የመንዝ ጌራ ምድር ወረዳ በበጀት አመቱ በካፒታል በጀት ከሚያስገነባቸው ፕሮጀክቶች አንዱ የሆነው የማህበረሰብ አቀፍ መድሃኒት ቤት ግንባታው ከ2ሚሊዮን 362ሺ በላይ በሚሆን በጀት በተጀራጁ ወጣቶች ተጠናቆ የክልልና የዞን ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል።

በአማራ ክልል ምክር ቤት የሰው ኃብትና ቱሪዝም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ አበራ ፋንታሁን፣የሰ/ሸዋ ዞን ም/አስተዳዳሪ አቶ ተክለየስ በለጠ፣የሰ/ሸዋ ዞን ጤና መምሪያ ም/ኃላፊ አቶ ተፈሪ ይድነቅ፣የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማሩ ቸርነት፣የወረዳው ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ እሸቱ አሰፋ እና ሌሎች የስራ ኃላፊዎች በምረቃ መርሃ ግብሩ ተገኝተዋል።

የግንባታው መጠናቀቅ የማህበረሰቡን የመድሃኒት አቅርቦት፣ተደራሽነት፣ደህንነቱ የተጠበቀ መድሃኒት ማቅረብ፣የጤና ግንዛቤ መፍጠር፣የመረጃ ተደራሽነት እና የጤና ድጋፍና እንክብካቤ ላይ ትኩረት ሰጥቶ ስለሚሰራ የማህበረሰቡን እንግልት ሊፈታ የሚችል መሆኑን የወረዳው ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ እሸቱ አሰፋ ገልፀዋል።

በ3 ወር የተቀላጠፈ የግንባታ ጊዜ የተጠና ቀቀው ይህ ፕሮጀክት ሌሎች ፕሮጀክቶችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ማሳያ መሆኑን የገለፁት የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማሩ ቸርነት በኢንተርፕራይዝ ተደራጅተው ጥራት ያለውና በአጭር ጊዜ የተጠናቀቀ ፕሮጀክት ላስረከቡን ወጣቶች ምስጋና ይገባል ብለዋል።

ተጨማሪ መረጃዎችን ከመንዝ ጌራ ምድር ወረዳ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://www.youtube.com/channel/UC2sGeulo1xi7MFoOM1X3-rg
በዌብሳይት http://www.menzgera.gov.et/
በቴሌግራም https://t.me/menzegeracom
ትዊተር https://twitter.com/MenzgeraCom
https://www.youtube.com/watch?v=DskFVQ6Av0M
ቲክ ቶክ www.tiktok.com/

03/06/2026
የክልልና የዞን ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በድህረ ምርጫና የቀጣይ ተግባራት ዙሪያ ውይይት ተደረገ፤መ/ሜዳ፤ግንቦት 26/2018(መጌወመኮ)የክልልና የዞን ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በድህረ ...
03/06/2026

የክልልና የዞን ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በድህረ ምርጫና የቀጣይ ተግባራት ዙሪያ ውይይት ተደረገ፤

መ/ሜዳ፤ግንቦት 26/2018(መጌወመኮ)

የክልልና የዞን ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በድህረ ምርጫና የቀጣይ ተግባራት ዙሪያ
ከመንዝ ጌራ ምድር ወረዳ እና መ/ሜዳ ከተማ ጠቅላላ አመራሮች ጋር የጋራ ውይይት ተደርጓል።

የውይይት መድረኩን በአማራ ክልል ምክር ቤት የሰው ኃብትና ቱሪዝም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ አበራ ፋንታሁን፣በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመ/ሜዳ ምርጫ ክልል የክልል ምክር ቤት እጩ ተወዳዳሪና የሰ/ሸዋ ዞን ም/አስተዳዳሪ አቶ ተክለየስ በለጠ እና የሰ/ሸዋ ዞን ጤና መምሪያ ም/ኃላፊና የሁለቱ ወረዳ ደጋፊ አመራር አቶ ተፈሪ ይድነቅ መርተውታል።

በውይይቱ ምርጫው እንዳይሳካ የሚሞክሩ ሰላም ጠሎችን በህዝባችን ትብብርና በተሳካ የአመራር ብቃት አንገት አስደፍተን፣ለህዝባችን ደህንነትና ለውጥ ስንል በርካታ ፈተናዎችን አልፈን ለድል በመብቃታችን ተደስተናል ሲሉ ተሳታፊዎች ገልፀዋል።

ከድጋፍ ሰልፉ ጀምሮ ህዝቡ ያሳየው ድጋፍና ትብብር እንድሁም የፀጥታ መዋቅሩ የነበረው ተሳትፎ የሚደነቅ በመሆኑ ምስጋና እያቀረብን ህዝቡ ለሰጠን ድምፅ ክብር ሰጥተን የተጣለብንን አደራ ለመወጣት በድምፁ ላፀናን ህዝብ የተሳለጠ አገልግሎት በመስጠት፣የዋሉ ያደሩ የመሠረተ ልማት እና የመልካም አስተዳደር ጉድለቶችን ሊመልስ በሚችል መልኩ በየደረጃው ያለ አመራርና ባለሙያ መስራት እንደሚገባው ተመላክቷል።

የድህረ ምርጫ ተግባራትን ለይተን በመስራት ህዝቡ በድምፁ የሰጠውን እድል ተጠቅመው በአዲስ ወደ ተወካዮች ምክር ቤት እና ክልል ምክር ቤት የሚገቡ እጩዎች ለመንዝ ሀዝብ የመሠረተ ልማት ተጠቃሚነት አዲስ መፍትሄ እንደሚያመጡ በመተማመን ከምርጫ መልስ ዘላቂ ሰላም የማረጋገጥ ስራውን አጠናክረን መስራት ይጠበቅብናል ተብሏል።

በመጨረሻም መድረኩን በመሩት የክልልና የዞን አመራሮች በተሰጠው የማጠቃለያ ሀሳብ ለምርጫው መሳካት አስተዋፅኦ ለነበራቸው ከቀበሌ እስከ ወረዳ ላሉ አካላት ሁሉ ምስጋና ቀርቦ ውይይቱ ተጠናቋል።
ተጨማሪ መረጃዎችን ከመንዝ ጌራ ምድር ወረዳ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://www.youtube.com/channel/UC2sGeulo1xi7MFoOM1X3-rg
በዌብሳይት http://www.menzgera.gov.et/
በቴሌግራም https://t.me/menzegeracom
ትዊተር https://twitter.com/MenzgeraCom
https://www.youtube.com/watch?v=DskFVQ6Av0M
ቲክ ቶክ www.tiktok.com/

በድህረ ምርጫ ህዝቡን የማዳመጥ፣የመረዳት ዝግጁነትና ስትራቴጂዊ አስተውሎት ያስፈልገናል(ረዳት ፕሮፌሰር ዳምጠው ተሰማ)መ/ሜዳ፤ግንቦት 25/2018(መጌወመኮ)በመ/ሜዳ ምርጫ ክልል የአማራ ብሔራ...
02/06/2026

በድህረ ምርጫ ህዝቡን የማዳመጥ፣የመረዳት ዝግጁነትና ስትራቴጂዊ አስተውሎት ያስፈልገናል(ረዳት ፕሮፌሰር ዳምጠው ተሰማ)

መ/ሜዳ፤ግንቦት 25/2018(መጌወመኮ)

በመ/ሜዳ ምርጫ ክልል የአማራ ብሔራዊ ንቅናቂ(አብን) ፓርቲን በመወከል በ7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በእጩነት የተወዳደሩት ረዳት ፕሮፌሰር ዳምጠው ተሰማ ለመራጩ ህዝብ እና የምርጫ ሂደቱን በማስተባበር ለሰሩ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።

በድህረ ምርጫ ህዝቡን የማዳመጥ፣ የመረዳት ዝግጁነትና ስትራቴጂዊ አስተውሎት እንደሚያስፈልግም ረዳት ፕሮፌሰር ዳምጠው ተሰማ ገልፀዋል።

ረዳት ፕሮፌሰር ዳምጠው ተሰማ አክለውም
እንደ ፖለቲካ ድርጅትም ሆነ የምርጫ ክልል ህዝብ ወኪል የምርጫ ሂደቱ የህጋዊ ስርዓት ግንባታ ምሰሶ እንድሆን እና የህዝባችን የስልጣን ባለቤትነት መብት አንዲረጋገጥ ባለን ጽኑ እምነት የተነሳ ለሁሉም የምርጫ ሂደቶች መሳካት ሁለንተናዊ ጥረት ስናደርግ ቆይተን በድህረ-ምርጫ ምዕራፍ ላይ ደርሰናል፤ በዚህም ቅድም-ምርጫንና የምርጫ አለትን አጠናቀን ድህረ-ምርጫ ላይ ለመድረሳችንና ጥረታችን ፍሬ አንዲያፈራ የህዝባችን እና የፀጥታ መዋቅሩ ሚና አይተኬ እንደሆነ ስለምንረዳ ልዩ ክብር አንሰጣለን፡፡

የትግል ማዕከላችን ህዝብ አንደ መሆኑ መጠን ጥቅል የምርጫ ውጤት ባይገለጽም እንኳ ሰላማዊና ስልጡን የፖለቲካ ባህል እንዲገነባ አርዕያ ሆኖ ያሳየንን ህዝብ ተጠቃሚ ሊያደርጉ የሚችሉ ተቋማዊ ተግባራቶቻችን አንድቀጥሉ የድርሻችንን እንወጣለን፡፡

አሁን ላይ ደግሞ የምርጫ ውጤቱን በጸጋ ከመቀበል ባሻገር ከሀገራዊ አንድነት፣ ከዘላቂ ሰላም፣ ከተለያዩ የማህበረ-ኢኮኖሚ እድገቶች ጋር የሚያያዙ የትግል ፍኖተ-ካርታዎቻችን ላይ ትኩረት አድርገን እየሰራን አንገኛለን፡፡

በመሃል ሜዳ ምርጫ ክልል አንደተወዳደረ እጩም ህዝቡ በምርጫ ሂደት ያሳየው ተሳትፎ፣ ፖለቲካዊ ንቃት፣ ቁርጠኛ የስርዓት ግንባታ ባህል እና ሰላሙን ለመጠበቅ ያለው ቁርጠኝነት በርካታ መልዕክቶችን የሚያስተላልፍ አንደሆነ እረዳለሁ፡፡

ማንም ተወዳዳራሪ ቢመረጥ የትልቅና የአሰላሳይ ህዝብ ውክልና አንደተሰጠው መረዳት እንዳለበት መገንዘብ ችያለሁ፡፡

በሌላ መልኩ የዚህ ህዝብ ወኪል መሆን ከፖለቲካ ታሪኩ፣ ከማህበረሰባዊ ሞጋችነቱ እና ቀጥሮና መዝኖ ከያዛቸው የመሰረተ-ልማት አጀንዳዎች አንጻር ከባድ ኃላፊነትን አንደመሸከም ተደርጎ የሚወሰድ በመሆኑ ይህን ኃላፊነት መሸከም የሚያስችል ስትራቴጂዊ አስተውሎት እና ህዝቡን የማዳመጥና የመማር ወትሮ ዝግጁነት እና የህዝብን ጥቅም ማዕከል ደረገ ትብብር እንደሚስፈልግ አመላካች ነው፡፡

በመሆኑም ማናችንም የመሃልሜዳ ምርጫ ክልል ተወዳዳሪዎች የመንዝ ጌራን፣ የመንዝ ቀያን እና የመሃል ሜዳ ከተማ አስተዳደርን አሰላሳይ ህዝብ የሚመጥን የተልዕኮ ዝግጁነት እና ከፍ ያለ ሃላፊነት መወጣት የሚያስችል የሞራልና አብርሆታዊ ቅኝት ያስፈልገናል ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

ፈጣሪ ሀገራችንን እና ህዝባችንን ይባርክ

ዳምጠው ተሰማ ደነቀ (ረ/ት ፕሮፌሰር)

ምርጫው በሰላም መጠናቀቁን የወረዳው ሰላምና ደህንነት ጽ/ቤት ገለፀ፤መ/ሜዳ፤ግንቦት 25/2018(መጌወመኮ)በሰ/ሸዋ ዞን መ/ሜዳ ምርጫ ክልል መንዝ ጌራ ምድር ወረዳ በሚገኙ 61 የምርጫ ጣቢያ...
02/06/2026

ምርጫው በሰላም መጠናቀቁን የወረዳው ሰላምና ደህንነት ጽ/ቤት ገለፀ፤

መ/ሜዳ፤ግንቦት 25/2018(መጌወመኮ)

በሰ/ሸዋ ዞን መ/ሜዳ ምርጫ ክልል መንዝ ጌራ ምድር ወረዳ በሚገኙ 61 የምርጫ ጣቢያዎች ያለ ምንም የፀጥታ ችግር መራጩ ህዝብ በነቂስ ወጥቶ ድምፁን መስጠቱን የወረዳው ሰላምና ደህንነት ጽ/ቤት ኃላፊ ፶ አለቃ ነጋሽ አሰፋ ገልፀዋል።

ኃላፊው እንደገለፁት ምርጫን ለማካሄድ የነበሩ ፈታኝ ሁኔታዎችን በመቋቋም፣የሚነዙ አሉባልታዎችን ባለመስማት፣መንግስት መመስረትን ብቸኛው አማራጭ አድርጎ በመውሰድ፣ጠላቱን በማሳፈር ራሱንና ማንነቱን ያኮራ በቃሉ የተገኘ፣የመንዜነት ታሪኩን ዳግም የፃፈ ህዝብ ሰላሙ ተጠብቆ የሚበጀውን እንድመርጥ አስተማማኝ ሰላም እንድፈጠር ፣ምርጫው ፍፁም ሰላማዊ በሆነ መንገድ እንድጠናቀቅ ላደረጉ የሀገር መከላከያ ሰራዊት፣የአድማ መከላከል፣የወረዳው ሰላም አስከባሪ፣የፖሊስ አባላትና አጠቃላይ የፀጥታ መዋቅሩ እና መራጩ ህዝብ ምስጋና ይገባዋል ብለዋል።
ተጨማሪ መረጃዎችን ከመንዝ ጌራ ምድር ወረዳ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://www.youtube.com/channel/UC2sGeulo1xi7MFoOM1X3-rg
በዌብሳይት http://www.menzgera.gov.et/
በቴሌግራም https://t.me/menzegeracom
ትዊተር https://twitter.com/MenzgeraCom
https://www.youtube.com/watch?v=DskFVQ6Av0M
ቲክ ቶክ www.tiktok.com/

ምርጫው ነፃ፣ሰላማዊና ፍትሃዊ መሆኑን እጩ ተወዳዳሪዎች ገለፁ፤መ/ሜዳ፤ግንቦት 25/2018(መጌወመኮ)በሰ/ሸዋ ዞን የመ/ሜዳ ምርጫ ክልል ብልፅግና ፓርቲን ወክለው ለክልል ምክር ቤት አባልነት ...
02/06/2026

ምርጫው ነፃ፣ሰላማዊና ፍትሃዊ መሆኑን እጩ ተወዳዳሪዎች ገለፁ፤

መ/ሜዳ፤ግንቦት 25/2018(መጌወመኮ)

በሰ/ሸዋ ዞን የመ/ሜዳ ምርጫ ክልል ብልፅግና ፓርቲን ወክለው ለክልል ምክር ቤት አባልነት እጩ ተወዳዳሪ የሆኑት አቶ ተክለየስ በለጠ በተወዳደሩበት ምርጫ ክልል እንደታዘቡት ምርጫው ነፃ፣ሰላማዊና ፍተሃዊ በመሆኑ ሀቀኛውና ኩሩውን የመንዝ ህዝብ ወክለው በመወዳደራቸው ደስተኛ መሆናቸውን ገልፀው የተለያዩ ችግሮችን ተቋቁሞ ድምፁን ለሰጣቸው መራጩ ህዝብ ያላቸውን የላቀ ክብርና ምስጋና አቅርበዋል።

ተጨማሪ መረጃዎችን ከመንዝ ጌራ ምድር ወረዳ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://www.youtube.com/channel/UC2sGeulo1xi7MFoOM1X3-rg
በዌብሳይት http://www.menzgera.gov.et/
በቴሌግራም https://t.me/menzegeracom
ትዊተር https://twitter.com/MenzgeraCom
https://www.youtube.com/watch?v=DskFVQ6Av0M
ቲክ ቶክ www.tiktok.com/

በመ/ሜዳ ምርጫ ክልል መንዝ ጌራ ምድር ወረዳ በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች ጊዜያዊ የድምጽ ውጤት ይፋ እየሆነ ነው፤ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምጽ ቆጠራ ውጤት ተጠናቅቆ በየምርጫ ጣቢያዎቹ ለሕ...
02/06/2026

በመ/ሜዳ ምርጫ ክልል መንዝ ጌራ ምድር ወረዳ በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች ጊዜያዊ የድምጽ ውጤት ይፋ እየሆነ ነው፤

የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምጽ ቆጠራ ውጤት ተጠናቅቆ በየምርጫ ጣቢያዎቹ ለሕዝብ ይፋ መሆን ጀምሯል።

​በመንዝ ጌራ ምድር ወረዳ በሚገኙ የተለያዩ ምርጫ ጣቢያዎች ማኅበረሰቡ የተለጠፈውን የድምጽ ውጤት እየተመለከተ ደስታውን እየገለፀ ነው።

7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ሰላማዊና ፍትሃዊ ሆኖ እንድጠናቀቅ ላደረጉ አካላት ወረዳ አስተዳደሩ ምስጋና አቀረበ፤መ/ሜዳ፤ግንቦት 25/2018(መጌወመኮ)በመ/ሜዳ ምርጫ ክልል መንዝ ጌራ ምድር ...
02/06/2026

7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ሰላማዊና ፍትሃዊ ሆኖ እንድጠናቀቅ ላደረጉ አካላት ወረዳ አስተዳደሩ ምስጋና አቀረበ፤

መ/ሜዳ፤ግንቦት 25/2018(መጌወመኮ)

በመ/ሜዳ ምርጫ ክልል መንዝ ጌራ ምድር ወረዳ በሚገኙ 61 የምርጫ ጣቢያዎች የተካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ነፃ ሰላማዊና ፍትሃዊ ሆኖ ተጠናቋል።

ምርጫው ሰላማዊ ሆኖ እንድጠናቀቅ ሚናቸውን ለተወጡ የወረዳው አመራሮች፣የፀጥታ መዋቅር አመራርና አባላት፣ምርጫ ቦርድ አስተባባሪዎች እና ለጀግናው ወረዳው ህዝብ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማሩ ቸርነት ምስጋና አቅርበዋል።

ዋና አስተዳዳሪው አክለውም ምርጫ የዲሞክራሲ ስርዓት መገለጫ ቢሆንም ይህን ያልተረዱ ኢትዮጵያን ለማፈራረስና ህዝቦቿን ምቾት ለመንሳት ሌት ከቀን የሚሰሩ የውስጥና የውጪ ጠላቶቿን ጫና ተቋቁመን፣በህዝባችን ጽናትና በመሪዎቹ ብርታት የማይቻሉ የሚመስሉ በርካታ ተግባራትን እየፈፀምን ጠላትን በአይኑ እያሳየነው መሆኑ በርካታ ማሳያዎች አሉ፤ለዚህም ጠላት በአንዳንድ ምርጫ ጣቢያዎች አቅራቢያ ጥይት እየተኮሰ ሞትን የማይፈራ፣መብቱን የሚያስከብር፣መሸነፍን የማይወድ፣በጥቅም የማይደለል የሀገር ፍቅር ያለው ህዝብና መሪ መኖሩ ለእኛ የኩራት መገለጫችን ነው፣ምርጫን በሰላምና በጋራ ትብብር እንዳጠናቀቅን ሁሉ ለቀጣይ ሌሎች የልማት ስራዎች ተመሳሳይ ዝግጅት በማድረግ ለህዝባችን ክብር እንሰጣለን ብለዋል።
ተጨማሪ መረጃዎችን ከመንዝ ጌራ ምድር ወረዳ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://www.youtube.com/channel/UC2sGeulo1xi7MFoOM1X3-rg
በዌብሳይት http://www.menzgera.gov.et/
በቴሌግራም https://t.me/menzegeracom
ትዊተር https://twitter.com/MenzgeraCom
https://www.youtube.com/watch?v=DskFVQ6Av0M
ቲክ ቶክ www.tiktok.com/

02/06/2026

ኢትዮጵያውያን መርጠዋል፤ ኢትዮጵያ አሸንፋለች!

የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

ኢትዮጵያ ከዜጎቿ የፈለገችዉን ኹሉ በፈለገችው ጊዜና ኹኔታ የምታገኝ ሀገር ናት፡፡ ለሀገራቸዉ የተጠየቁትን ሁሉ ለመስጠት ወደኋላ የማይሉ ዜጎች ስላሏት በእጅጉ ኮርታለች፡፡ ከዓድዋ እስከ ሕዳሴ ግድብ፣ ከወገን ለወገን መረዳዳት እስከ አረንጓዴ ዐሻራ የዜጎቿን ተሳትፎ ጠይቃ፣ ከመሻቷ በላይ ተሳትክቶላታል፡፡ ዛሬ የተደገመዉም ይኸው ነው፡፡

ኢትዮጵያ ኢትዮጵያዊ ዴሞክራሲን ማንበር፣ በግልጽና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ መንግሥትን መምረጥ፣ ሕገ መንግሥታዊነትን ፅኑ መሠረት ማስያዝ ትሻለች፡፡ ለዚህ ደግሞ 7ኛዉን ሀገራዊ ምርጫ እንደ ትልቅ አጋጣሚ መጠቀም አስፈልጓት ነበር፡፡

በምላሹም ከ54 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ለመራጭነት ተመዝግበው የዛሬዋን ቀን ሲጠባበቁ ቆይተዋል፡፡ እነሆ የእናት ሀገር ጥሪን በመቀበል ዜጎች በነቂስ ወጥተው ሲመርጡ ውለዋል፤ ሌሊቱንም አጋምሰዋል፡፡ በኢትዮጵያ የምርጫ ታሪክ ዜጎች ለረዥም ሰዓታት ተሰልፈዉ ድምፅ የሰጡበት ልዩ ምርጫም ነው፡፡

ምርጫዉ እንዳይካሄድ ባዳ እና ባንዳ ተቀናጅተዉ ያልቆፈሩት ጉድጓድ፣ ያልደረደሩት እንቅፋት አልነበረም፡፡ ነገር ግን ኢትዮጵያ ለጠራችው ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ የማይቻል ነገር አልነበረምና በስኬት ተጠናቅቋል፡፡ ኢትዮጵያውን በሰላማዊ መንገድ መርጠው ኢትዮጵያ አሸንፋለች፡፡

የኢትዮጵያን የዴሞክራሲያዊ ምርጫ ጥሪ ተቀብሎ ከንጋት እስከ ምሽት በመምረጥ ምላሽ ለሰጠው ሕዝብ፣ ሕገ መንግሥታዊ ሥርዐቱ እንዲጸና እና ዜጎች በሰላም እንዲመርጡ ምቹ ዓውድ ለፈጠሩ የፀጥታ አካላት፣ ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃ በየደቂቃዉ ሲያደርሱ ለነበሩ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት እንዲሁም የምርጫዉን ሂደት ለመሩ፣ ላስተባበሩ እና ለታዘቡ ሁሉ ኢትዮጵያ ታመሰግናለች፡፡

የኢፌዴሪ መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

ግንቦት 25 2018፣አዲስአበባ፣ኢትዮጵያ

Address

Mehal Meda
251

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Menz Gera werda Comunication office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Menz Gera werda Comunication office:

Share