Ze.bazen24

Ze.bazen24 Tok

I think this is the fact history.
02/03/2026

I think this is the fact history.

የዓድዋዉ ምንሊክ...!

‎ከዓድዋ በፊት በየአካባቢው ያሉትን ሹሞች እና ሕዝቦች ማስገበር ነበረበት። በመላም በዱላም ያንን አደረገ። ያንን ባደረገ ማግስት ነጭ ወራሪ መጣ። ምንሊክ ለእርምጃ አልተጣደፈም። ተቻኩሎ ሳይፍ አልመዘዘም። ደካማ መስሎ ቀን ጠበቀ። ጦርነትን መጀመር ያለብህ እንደምታሸንፍ እርግጠኛ ስትሆን ነው የሚለውን መርሕ በልቡ አኖረ። በዲፕሎማሲ ጉዳዩን ለመፍታት ጣረ። ወደብ ላይ በጣሊያን መንግስት ተይዞ የታገቱበትን ሁለት ሚሊየን ጥይት አስለቀቀ። ወደ ሞስኮ መልዕክተኞችን ልኮ ከንጉስ ኒኮላይ በ10 ሺህ የሚቆጠር ጠብመንጃ አገኘ።

‎በወቅቱ ለጣሊያን ያደረውን የዋጉን ዋቅሹም ብሩን አስሮ የዋግ ሹምነትን ለዋቅሹም ልጅ ሰጠ። ከትግራይ ከጣሊያን ጋር ለመተባበር ሲሰሩ የነበሩትን ራስ መንገሻንም ከጣሊያን ጋር አጋጭቶ እንዲዋጉ አደረገ። ራስ መንገሻ በጣሊያን ከተሸነፉ በኃላ አሉላ አባነጋን ይዞ ወደ አዲሳባ መጥቶ ይቅርታ ጠየቁ። ምኒልክ እዚህም ጋ ጥበብ የተሞላበት ስልት ተጠቀሙ። ወደ ግዞት አልላካቸዉም። አስሮ አላሰቃያቸዉም። የነገዉን ትልቁን ምስል ተመለከተና ሹሞ ሸልሞ ሸኛቸዉ።

‎የቁርጡ ቀን ደረሰ። የክተት አዋጅ ታወጀ። የክተት አዋጁ በዓለም ላይ አጭሩ የጦርነት ጥሪ ነው። ያልተንዛዛ ፣ እጥር ምጥን ያለ የክተት አዋጅ ነው። የት፣መቼ፣ እንዴት...የሚሉትን ጥያቄዎች የመለሰ የማያሻማ ግልፅ አዋጅ ነው። አዋጁ ዛሬም ድረስ ትልልቅ የጦርነት ትምህርት ቤቶች ውስጥ ጭምር የማስተማሪያ ሰነድ ሆኖ እያገለገለ ይገኛል።

‎ሕዝቡም የተባለውን አደረገ። ቀንበሩን ሰቅሎ፣ ስንቁን ቋጥሮ ወደ ወረ ኢሉ ተመመ። ከዛ ወዲህ ያለው ታሪክ ነው። የመሪ ጥበብ፣ ቀናኢ ሕዝብ፣ ልባም አዋጊ፣ ሞትን የናቀ ተዋጊ ባንድ ልብ አድሮ ባንድ ልብ ተፋለሙ።

‎አይደፈሬ የተባለው የአምባላጌዉ ምሽግ በገበየሁ ተሰበረ። የመቀሌው እንዳየሱስ ጦርነት በጣይቱ ስልትና ብልሐት ወራሪው ተረታ። በዓድዋ'ም የበሻ አውአሎም የስለላ ጥበብ፣ የአሉላ ጀግንነት፣ የባልቻ ገድል፣ የራስ መኮንን ፈረሰኞች አይበገሬነት ተጣምሮ በዓለም ታሪክ አዲስ ትርክት አኖሩ። ያቺን የነፃነት ሰንደቅ በዓድዋ ተራራ ላይ ሰቀሉ። ጥቁር ነጭን ረታ! በቃ ይህ የገድሎች ሁሉ ገድል የድሎች ሁሉ ድል ሆነ...

‎ ከዚህ ሁሉ ድል ጀርባ ግን ያ ንጉስ አለ!
(ጥላሁን ያሚ)

 አንበሳ ባንክ ለደምበኞቹ መልካም ዜና ይዞ መቷል። እንደሚታወቀው ባንኩ ለብዙ ግዜ ያህል የዲጂታል ችግር የነበረው መሆኑን የሚታወቅ ሲሆን አሁን ግን የነበረውን ችግር እስከወድያኛው ሊሸኘው ...
24/02/2026


አንበሳ ባንክ ለደምበኞቹ መልካም ዜና ይዞ መቷል። እንደሚታወቀው ባንኩ ለብዙ ግዜ ያህል የዲጂታል ችግር የነበረው መሆኑን የሚታወቅ ሲሆን አሁን ግን የነበረውን ችግር እስከወድያኛው ሊሸኘው ስራው ጨርሶ ይገኛል። ከእንግዲህ በኋላ አስቸገረኝ፣እምቢ አለኝ፣አይሰራም፣ደረሰኝ አያሳየኝም ማለት ቀረ ወጪ ተደርጎበት ስራው ጨርሶ አገልግሎቱ መስጠት ጀምረዋል አንበሳ ሞባይል ባንክ በማለት ስሙ ይፋ አድርገዋል።
በአቅራቢያዎ ወደ ሚገኘው የአንበሳ ባንክ ቅርንጫፍ ጎራ ብለው Active ያድርጉ። ደህንነቱ የተጠበቀ አገልግሎቱ ቀልጣፋ የሆነው Apps ስራው ጀምረዋል
❇የሚሰጣቸው አገልግሎት
✔ትራንስፈር ወደ ቴሌብር እና ሳፋሪ(M-PESA)
✔ትራንስፈስ ወደ ሌሎች ባንኮች
✔የውሃና መብራት ክፍያዎች
✔የትምህርት ቤቶች(school pay)
✔የአየር መንገድ ትኬቶች
✔የዲኤስቲቪ ክፍያዎች
✔የአየር ሰዓት ከፈለጉም
✔ካርድ አልባ(cardless)
ይሄ ሁሉ ባሉበት ሁነው የሚተገብሩበት በ ነው

!

አንበሳ ባንክ Anbesa bank
እንጀምረው! Let's go for it!

ይክእል ኣዶናይኣዶናይ ልበልና ብምክንያት እዩ ድካምና ተሳኪዕልና
29/11/2025

ይክእል ኣዶናይ
ኣዶናይ ልበልና ብምክንያት እዩ
ድካምና ተሳኪዕልና

07/11/2025

Lion International Bank Reports 1.8 Billion Birr Pre-Tax Profit

Nov 1, 2025

Lion International Bank (LIB) reported a pre-tax profit of 1.8 billion birr for the 2024/25 fiscal year during its 21st Annual General Meeting held today at the Sheraton Addis. The figure represents a substantial 94% increase from the previous year, underscoring the bank's robust performance amid economic challenges.

The meeting, attended by shareholders and board members, revealed that the bank's strategic focus on digital transformation and branch expansion contributed significantly to these results. LIB's total assets grew by 25% to reach 54 billion birr, while customer deposits saw a 23% increase to 44 billion birr. The bank's expanding customer base now stands at 2.4 million account holders, reflecting growing public trust in the institution.

LIB strengthened its capital position with paid-up capital increasing by 21% to 3.7 billion birr, while total capital and reserves Reached 6.5 billion Birr. The bank expanded its physical presence by adding 35 new branches, bringing its total network to 341 outlets across Ethiopia.

In a March 2025 report, stakeholders mentioned intentions to boost the bank's capital to 10 billion birr over the coming years.

The bank's strategic growth was further reinforced by its recent merger with Geez Bank, approved in August 2025, which will help meet capital requirements and expand its market reach. LIB also launched the "Anbesa Excellence Award 2025" to recognize top-performing regions, districts, and branches, reinforcing its commitment to operational excellence and service quality.

ጭቅላት ሲኖርህ ለህዝብህ እንደዚህ ታስባለክ
17/07/2025

ጭቅላት ሲኖርህ ለህዝብህ እንደዚህ ታስባለክ

" መኖር ከማይችል ሰው ግብር አትሰበስብም ፤ በልቶ ከማያድር ሰው ግብር አትሰበስብም ! "
- አቶ ካሳሁን ፎሎ

እንደ ሀገር ግብር መሰብሰብ አለበት ልማትም መቀጠል አለበት ፤ የሰው ህይወትም መቀጠል አለበት ፤ ሰው እየተራበ መስራት አይችልም ምርታማ መሆን አይችልም ! "

የኢትዮጵያ የሰራተኛ ማህበራት ኮንፌደሬሽን ዋና ፕሬዘዳንት አቶ ካሳሁን ፎሎ ስለ ገቢ ግብር አዋጁ ምን አሉ ?

" የደመወዝ ገቢ ግብር ከዚህ በፊት መነሻው 600 ብር ነው፤ አሁን በረቂቁ የቀረበው 2,000 ሆኖ ነው።

በመሰረቱ 600 በሆነበት ሰዓት አንደኛ ገንዘብ የመግዛት አቅሙ ትልቅ በመሆኑ ፣ 1 ዶላርም 20 ብር ነበር ያኔ የዛሬ 10 ዓመት አካባቢ ነው ይሄ ነገር የተሻሻለው ፤ ሁለተኛ የመንግሥት ሰራተኞች መነሻ ደመወዝ 600 ነበር ያኔ 600 ለአንድ ሰው ለአንድ ወር ቢያንስ ምግብ መብላት ብቻ ይበቃዋል በሚል ታሳቢ አማካይ ተወስዶ ነው 600 የተባለው።

አሁን ግን 300% ፣ 200% ጨመርን (ማለትም 2000 ብር አደረግን) እሱ አይደለም ዋናው መነሻው ስንት ነው አሁን ? በአጭሩ ፤ እንኳን የኑሮ ውድነቱን ታሳቢ ያደረገ መንግሥት እራሱ ሰራተኛው በ600 ብር ሊያኖረው አይችልም ፤ የኑሮ ውድነቱ ከሚታሰበው በላይ በተለይም በሪፎርሙ መንግሥት በይፋ ያረጋገጠው ታችኛው የሰራተኛ ክፍል ጎድቶታል፤ ' ሊቋቋመው አይችልም ' በሚል መነሻ ደመወዙን ከፍ አድርጓል ፤ መነሻ ደመወዝን ከፍ ሲያደርግ ይሄን ታሳቢ አድርጓል።

አሁንም ቢሆን እነዚህ ሰዎች መኖር ከማይችል ሰው ግብር አትሰበስብም ፤ በልቶ ከማያድር ሰው ግብር አትሰበስብም። በቀን 2.15 ዶላር የሚያገኝ ሰው ድሃ ነው ከዚያ በታች የሚያገኝ በሙሉ ድሃ ነው ፤ እኛ ደግሞ እዛ ሁሉ አልደረስንም።

እኛ እያቀረብን ያለነው ሃሳብ 8,324 መነሻ ይሁን ነው። እንኳን የኛ ሀሳብ የመንግሥት እራሱ ያስቀመጠው መነሻ ላይ እንኳን አልደረሰም።

ሌላው በፊት የግብር ምጣኔው ከ0 ጀምሮ 10% ፣ 15% ፣ 20% ፣ 25% ፣ 30% ፣ 35% ይቀጥል ነበር አሁን 10%ን ከመሃል አወጡና ከ0 ጀምረው ቀጥታ 15% ነው የገቡት። አሁን ቀጥታ ከ15 ከከፍተኛው ነው ሲጀምር የጀመሩት። ይሄ ትክክል አይደለም።

35% ከየት ጀመረ 14,100 በላይ የሚያገኝ ሰው 35% ግብር ይከፍላል ፤ 35% ከሰራተኛ በአሁኑ የኑሮ ውድነት 15% በእያንዳንዱ በምግብ ዋጋም፣ በሚገዛው እቃም 15% ይጨምራል ይሄ ሲደመር 50% ይመጣል፤ 7% የጡረታ አለ ጡረታ የሚያገኘው ከ60 ዓመት በኃላ አሁን ግን 57% ከደመወዙ ላይ ይሄዳል በቀረችው 43% ፦
- ልጆች ያስተምራል
- ምግብ ይበላል
- ልብስ ይገዛል
- ቤት ይከራያል ምንድነው የሚያደርገው ?

ይሄና ይሄ ብቻ ስላልሆነ ነው ዝም ያልን እንጂ ይሄም ከፍ ብሎ እኮ ይበቃል ማለት አይደለም።

ግን እንደ ሀገር ግብር መሰብሰብ አለበት ልማትም መቀጠል አለበት ፤ የሰው ህይወትም መቀጠል አለበት ፤ ሰው እየተራበ መስራት አይችልም ምርታማ መሆን አይችልም። "

Via:- tikvah ethiopia

ሓውዜን-ዓደይ-ብጥዋፍ ዘታልል ህውሓት ገጢሙኪዋ ካብ ሳልሳይ ጊዜ ደብዳብ የውፃእዮ ህዝብኪ
20/06/2025

ሓውዜን-ዓደይ-ብጥዋፍ ዘታልል ህውሓት ገጢሙኪዋ ካብ ሳልሳይ ጊዜ ደብዳብ የውፃእዮ ህዝብኪ

26/05/2025

ትግራይ ክልል ለብሔራዊ ባንክ ወርቅ በማቅረብ ቀዳሚ እንደሆነ ተገለፀ

ኢትዮጵያ በበጀት ዓመቱ 10 ወራት ውስጥ ከወርቅ 2 ነጥብ 57 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር ገቢ አግኝታለች፡፡

በአጠቃላይ 29 ነጥብ 396 ኪሎ ግራም በላይ ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ ቀርቧል።

እንደ የማዕድን ሚኒስቴር ገለጻ ከክልሎች ለብሔራዊ ባንክ የቀረበው የወርቅ መጠን፦ ትግራይ፤ 12 ሺህ 210 ኪሎ ግራም ፤ ኦሮሚያ፤ 6 ሺህ 910 ኪሎ ግራም ፤ ጋምቤላ፤ 4 ሺህ 590 ኪሎ ግራም

ቤንሻንጉል፤ ጉሙዝ 3 ሺህ 689 ኪሎ ግራም በሌሎች ማዕድናት አመርቂ የሆነ ውጤት እየተመዘበ እንደሚገኝም የማዕድን ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሚሊዮን ማቴዮስ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ ተናግረዋል፡፡
(ኢትዮ ኤፍኤም)

ፍትሒ ፍትሒ ፍትሒ
17/05/2025

ፍትሒ ፍትሒ ፍትሒ

Dr Mehari tadelle እንተመሪሕዋ ትግራይ ትዕሪ ዝብል እምነት ኣለኒ
26/03/2025

Dr Mehari tadelle እንተመሪሕዋ ትግራይ ትዕሪ ዝብል እምነት ኣለኒ

21/03/2025

ሃሰተኛ ሰነዶችን ከተቋሙ ተረጋግጦ የወጣ በማስመሰል የሚያጭበረብሩ ግለሰቦች መኖራቸውን የሰነዶች ማረጋገጫ እና ምዝገባ አገልግሎት አስታወቀ
*****************************

የሰነዶች ማረጋገጫ እና ምዝገባ አገልግሎት እንዳስታወቀው አንዳንድ ህገወጦች በምስሉ ላይ የሚታየውን የአየር መንገድውክልና እና መሰል ሃሰተኛ ሰነዶችን ከተቋሙ ተረጋግጦ የወጣ በማስመሰል ህብረተሰቡን በማጭበርበር የማይገባቸውን ጥቅም ለማግኘት እየሞከሩ መሆኑን ለተቋሙ በደረሰው ጥቆማ መረዳት መቻሉን አስታውቋል።

ተቋሙ እንዲህ አይነቱን የወንጀል ድርጊት እንደማይታገስ እና ተከታትሎ ለህግ እንደሚያቀርብ ያስታወቀ ሲሆን ህብረተሰቡም በእንደዚህ አይነት ሃሰተኛ ሰነድ እንዳይጭበረበርና መሰል አጠራጣሪ ሁኔታ ሲኖር ለፖሊስ ጥቆማ በመስጠት ወንጀል ፈፃሚዎች በህግ ተጠያቂ ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስቧል።

የሰነዶች ማረጋገጫ እና ምዝገባ አገልግሎት የሚመነጩ የውክልና ሰነዶች ባር ኮድ ያላቸው ሲሆኑ ልዩ ውክልና ከሆነ ደግሞ የራሱ የሆነ መለያ ( security feature) እና ኤሌክትሮኒክስ/ደረቅ ማህተም የያዙ በመሆኑ በቀላሉ በሃሰተኛ መንገድ ሊዘጋጁ የማይችሉ መሆናቸውንም ተቋሙ አረጋግጧል።

#ኢቢሲ #እውነታ #ሀሰተኛ

Address

Mekelle

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ze.bazen24 posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share