Habru Woreda Government Communication Affairs Office

Habru Woreda Government Communication Affairs Office Habru Woreda Government Communication Affairs
የሀብሩ ወረዳ መንግስት ኮሙዩኒኬ

"ኢትዮጵያ እየመረጠች ነው !!!"በሰሜን ወሎ ዞን ሀብሩ ወረዳ መራጮች በሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች ድምጽ እየሰጡ ነው።   ሀብሩ ኮሙኒኬሽን፦ ግንቦት 24/2018 ዓ.ም
01/06/2026

"ኢትዮጵያ እየመረጠች ነው !!!"

በሰሜን ወሎ ዞን ሀብሩ ወረዳ መራጮች በሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች ድምጽ እየሰጡ ነው።

ሀብሩ ኮሙኒኬሽን፦ ግንቦት 24/2018 ዓ.ም

7ኛውን ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ ሰላማዊና ስኬታማ ሁኖ እንዲጠናቀቅ የጸጥታ ኀይሉ  በቂ ዝግጅትና ስምሪት ማድረጉን የሀብሩ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት አስታወቀ። ‎‎ ግንቦት 22/2018 ዓ.ም(ሀብሩ...
30/05/2026

7ኛውን ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ ሰላማዊና ስኬታማ ሁኖ እንዲጠናቀቅ የጸጥታ ኀይሉ በቂ ዝግጅትና ስምሪት ማድረጉን የሀብሩ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት አስታወቀ።


‎ ግንቦት 22/2018 ዓ.ም(ሀብሩ ወረዳ ኮሙኒኬሽን)

‎በሰሜን ወሎ ዞን የሀብሩ ወረዳ አስተዳደር ሰባተኛውን ሀገራዊ እና ክልላዊ ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊና ስኬታማ ሁኖ እንዲጠናቀቅ የፀጥታ መዋቅሩ ከመቼውም ጌዜ በተሻለ ሁኔታ ሰፊ ዝግጅት ማድረጉን የወረዳው ፖሊስ ጽ/ቤት አስታውቋል።

‎የሀብሩ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት ሀላፊ ኢንስፔክተር መሃሪ ደጉ እንደገለጹት የወረዳው የጸጥታ ሀይላችን ፖሊስ እና ከሰላም አስከባሪ ከሀገር መከላከያ ሠራዊት ጋር በመቀናጀት ምርጫውን በስኬት ለማካሄድ በቂ ዝግግጅት ማድረጉንና ስምሪት መውሰዱን ገልፀዋል።

ሀገራዊ ‎ምርጫው ሰላምዊ ዲሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የጸጥታ መዋቅራችን በጥሩ ቁመና ላይ ይገኛል ያሉት ፖሊስ ሃላፊው ህዝባችን ይሆነኛል ወይም ይበጀኛል የሚለውን ፓርቲ ያለምንም ስጋት ነፃ ሁኖ በመምረጥ ሀገራዊ ሀላፊነቱን ሊወጣ ይገባል ሲሉ አሳስበዋል ።

•~•~•
•~•~•
ለወቅታዊ ፣ ትክክለኛና አዳዲስ መረጃዎች የተቋማችንን የማህበራዊ ገፆች ይወዳጁ።
ዩቲዩብ:https://www.youtube.com/
ፌስቡክ:https://www.facebook.com/share/19dpbXvN69/
ቲክቶክ:http://tiktok.com/.communcatio
ቴሌግራም:https://t.me/+J-1GwMayZ2Y4YzVk
ትዊተር:https://x.com/Habrucomncation

ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. የድምፅ መስጫ ቀንን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫየኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የ7ኛው ጠቅ...
27/05/2026

ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. የድምፅ መስጫ ቀንን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ አሰጣጥ እንዲከናወን መወሠኑ ይታወቃል።

በዚህም መሠረት በመራጭነት የተመዘገቡ ዜጎች ሁሉ በዕለቱ ድምፃቸውን ለመስጠት ይችሉ ዘንድ እና የደምፅ አሰጣጥ ሂደቱ ያለምንም የፀጥታ ችግር ይከናወን ዘንድ ቦርዱ የሚከተሉት ተግባራዊ እንዲሆኑ የምርጫ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና ሥነ-ምግባር ዐዋጅ 1162/ 2011 አንቀጽ 161 የመተባበር ግዴታ መሠረት ለመንግሥታዊ እና ለማንኛውም መንግሥታዊ ላልሆኑ ተቋማት ያሳውቃል።

በዚህም መሠረት:-

- ዜጎች ዕለቱን ለድምፅ መስጫ ብቻ መጠቀማቸው ስለሚያስፈልግ የፌዴራል እና የክልል መንግሥታዊ ተቋማት ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ሥራ ዝግ እንዲያደርጉ፣

- ዜጎች ዕለቱን ለድምፅ መስጫ ብቻ መጠቀማቸው ስለሚያስፈልግ በፌዴራል እና በክልሎች የሚገኙ ማንኛውም መንግሥታዊ ያልሆኑ እና የግል ተቋማት በተመሳሳይ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ዝግ እንዲያደርጉ እያሳወቀ፤

- የአስቸኳይ ጊዜ አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማት፣ ሆስፒታሎች፣ የዕለት ተዕለት አገልግሎት ሰጪዎችም (ሆቴሎች፣ ሬስቶራንቶች፣ የትራንስፓርት አገልግሎት) በዝግ ቀናት የሚያደርጉትን አገልግሎት በተመሳሳይ የሚያከናውኑ ሲሆን፤ የመተባበር ግዴታው እነዚህን ተቋማት እንቅስቃሴ መዘጋት አያስገድድም።

- የትራንስፓርት አገልግሎት በተለመደው መንገድ የሚቀጥል ቢሆንም፤ ዜጎች ድምፅ ከመስጠት ውጪ ከፍተኛ እንቅስቃሴን የሚፈልጉ ሁነቶችን እና ዕቅዶችን እንዳይይዙ እና እንቅስቃሴያቸውን ድምፅ ለመስጠት ብቻ እንዲያደርጉ ቦርዱ ያበረታታል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
ግንቦት 19 ቀን 2018 ዓ.ም.

 !   ግንቦት 19/2018 ዓ/ም (ሀብሩ)በትምህርት ተደራሽነትና ጥራት ላይ ታሪካዊ ለውጥ ማስመዝገቡን የሀብሩ ወረዳ ትምህርት ጽህፈት ቤት አስታወቀ። ጽህፈት ቤቱ ባለፉት አምስት ዓመታት ከ...
27/05/2026

!

ግንቦት 19/2018 ዓ/ም (ሀብሩ)

በትምህርት ተደራሽነትና ጥራት ላይ ታሪካዊ ለውጥ ማስመዝገቡን የሀብሩ ወረዳ ትምህርት ጽህፈት ቤት አስታወቀ። ጽህፈት ቤቱ ባለፉት አምስት ዓመታት ከ227 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ዘርፈ-ብዙ የመሠረተ-ልማት ግንባታዎችን በስኬት ማጠናቀቁን ገልጿል።

በሰሜን ወሎ ዞን የሀብሩ ወረዳ ትምህርት ጽህፈት ቤት ባለፉት አምስት ዓመታት በትምህርት ተደራሽነት፣ ጥራትና በሴት ተማሪዎች ስነ-ተዋልዶ ንጽህና አጠባበቅ ላይ ያተኮሩ ታላላቅ የፕሮጀክት ስራዎችን በስኬት ማጠናቀቁን አስታውቋል።

የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ መንገሻ ደረጀ የባለፉት አምስት ዓመታት አጠቃላይ የግንባታ ሪፖርትን መሠረት በማድረግ እንደገለጹት፤ በወረዳው በአጠቃላይ 22 ፕሮጀክቶች ሙሉ በሙሉ ተጠናቀው ለአገልግሎት የበቁ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅትም በአንድ ግዙፍ ፕሮጀክት ላይ ንቁ የግንባታ ስራ እየተከናወነ ይገኛል።

ኃላፊው አክለውም ለትምህርት መሠረተ-ልማት ማስፋፊያ ከተመደበው ጠቅላላ በጀት ውስጥ 139 ሚሊዮን 522 ሺህ 674 ከ80 ሳንቲም በላይ የሚሆነው ሙሉ በሙሉ ለተጠናቀቁት 22 ፕሮጀክቶች ውል የተከፈለ ሲሆን፣ ተጨማሪ 88 ሚሊዮን ብር በሂደት ላይ ለሚገኘው ለአጆ ሜዳ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ ተመድቦ ስራው እየተከናወነ እንደሚገኝ ታውቋል።

ይህ በወረዳው ታሪክ በትምህርት ዘርፍ የተመዘገበ ከፍተኛው መዋዕለ-ንዋይ መሆኑም ተገልጿል።

ጽህፈት ቤቱ ባከናወናቸው የግንባታ ስራዎች ውስጥ የተለያዩ የትምህርት ደረጃዎችንና የተማሪዎችን ሁለንተናዊ ፍላጎት ያማከሉ ዘርፈ-ብዙ ስራዎች ተካተዋል። ከእነዚህም መካከል በመልካ ጨፌየ የተገነባው ዘመናዊ የአጸደ-ሕጻናት መማሪያና መጸዳጃ ቤት በ5 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር ወጪ የተከናወነ ሲሆን፤ በኮለቦbox፣ ቡርቃ፣ ጌታው ቀየ እና አሊመንታ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ባለ አራት መማሪያ ክፍል ብሎኮች ተገንብተው ተጠናቀዋል።

በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በኩልም በመርሳ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የላቦራቶሪ ብሎኮች፣ የኮምፒውተር ክፍሎች እና ተጨማሪ የመማሪያ ክፍሎችን ያካተቱ ሁለት ግዙፍ ፕሮጀክቶች በ21 ነጥብ 9 ሚሊዮን እና በ35 ነጥብ 2 ሚሊዮን ብር ወጪ ተገንብተው ለአገልግሎት ክፍት ሆነዋል።

በተጨማሪም በትምህርት ቤቶች የሴት ተማሪዎችን መቅረት ለማስቀረት በተሰራው ስራ በዱሌ ጨፌየ፣ በዙፋን አቦ እና በአሊመንታ ዘመናዊ የመጸዳጃ እና የሴቶች ንጽህና መጠበቂያ ክፍሎች በከፍተኛ በጀት የተገነቡ ሲሆን፤ በዙፋን አቦ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ንጹህ የመጠጥ ውሃ መስመር መዘርጋቱ ተጠቅሷል።

ይህንን ታሪካዊ ስኬት ለማስመዝገብ የመንግስት በጀት ብቻ ሳይሆን የሀገር ውስጥና ዓለም አቀፍ ተራድኦ ድርጅቶች ሚና ከፍተኛ እንደነበር ሪፖርቱ ያመላክታል። የአማራ ልማት ማህበር (አልማ)፣ ዩኒሴፍ፣ ወርልድ ቪዥን፣ ዩ-ኤን-ዲ-ፒ እና ዋን ወሽ ፕሮግራም ከወረዳው አስተዳደር ጋር በቅንጅት በመስራት ለበጀቱ መገኘት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክተዋል።

ጽህፈት ቤቱ በአሁኑ ወቅት የትኩረት ማዕከል አድርጎ እየሰራበት የሚገኘውና 88 ሚሊዮን ብር የተመደበለት የአጆ ሜዳ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታም ተጠናቋል ብለዋል። ይህ ፕሮጀክት ሲጠናቀቅ በአካባቢው ለሚገኙ በብዙ ሺህ ለሚቆጠሩ ህጻናት ምቹ የመማሪያ አካባቢን እንደሚፈጥር ይጠበቃል።

በመጨረሻም የሀብሩ ወረዳ ትምህርት ጽህፈት ቤት የምህንድስና ዘርፍ ባወጣው መግለጫ፤ እነዚህ የተገነቡ የትምህርት ተቋማት የትውልድ መቅረጫ በመሆናቸው ህብረተሰቡና ተማሪዎች የባለቤትነት ስሜት ተሰምቷቸው ጥበቃና እንክብካቤ እንዲያደርጉላቸው ጥሪ አቅርቧል።

በሰሜን ወሎ ዞን ግዳን ወረዳ በተለያዩ ቀበሌዎች የተገነቡ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ተመረቁ ግንቦት 18/2018 ዓ.ም (የግዳን ወረዳ ኮሙኒኬሽን) በወረዳው የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚ...
27/05/2026

በሰሜን ወሎ ዞን ግዳን ወረዳ በተለያዩ ቀበሌዎች የተገነቡ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ተመረቁ

ግንቦት 18/2018 ዓ.ም (የግዳን ወረዳ ኮሙኒኬሽን)

በወረዳው የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በከፍተኛ በጀት የተገነቡ የተለያዩ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች በከፍተኛ አመራሮች ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት ሆነዋል።

በፕሮግራሙ የህብር ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ እንድሁም በግዳን ምርጫ ክልል የብልፅግና ፓርቲ የክልል ምክርቤት ዕጩ ተወዳዳሪ የተከበሩ አቶ ጋሻው አስማሜ፣ የሰሜን ወሎ ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ኃላፊ እና የዞኑ ምክትል አስተዳዳሪ እንዲሁም በግዳን ምርጫ ክልል የብልፅግና ፓርቲ የክልል ምክር ቤት ዕጩ ተወዳዳሪ አቶ ታምራት ንጋቱ፣ የሰሜን ወሎ ዞን አካባቢና ደን ተጠሪ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ባንቴ ምስጋናው፣ የግዳን ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አማኑኤል አያሌው፣ የወረዳ አስተባባሪ ኮሚቴ እና የወረዳው አመራሮች ተገኝተዋል።

ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሃገር!!

ከአንድ መቶ ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባው  የመገናኛ ወንዝ ድልድይ ተመርቀ። መርሳ ፦ ግንቦት 19/2018 ዓ.ም በሰሜን ወሎ ዞን መርሳ ከተማ አንድ መቶ ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ...
27/05/2026

ከአንድ መቶ ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባው የመገናኛ ወንዝ ድልድይ ተመርቀ።

መርሳ ፦ ግንቦት 19/2018 ዓ.ም

በሰሜን ወሎ ዞን መርሳ ከተማ አንድ መቶ ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባው 60 ሜትር ርዝመት ያለው የመገናኛ ወንዝ ድልድይ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ተደርጓል።

በአማራ ክልል መንገድ የትራንስፖርትና ሉጂስቲክስ ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ጋሻው አወቀ እንደገለጹት ድልድዩ በአካባቢው ማህበረሰብ ለዘመናት ሲነሳ የቆየውን የመሠረተ ልማት ጥያቄ ከመፍታት ባሻገር የከተማዋን ትራንስፖርት፣ ንግድ፣ ማህበራዊ ትስስር፣ ኮሪደር ልማት እና የከተማውን ዋመ ንገድ በእጅጉ የሚያሳልጥ መሆኑን ተናግረዋል።

እንደ ዶ/ር ጋሻው ገለጻ የድልድዩ ግንባታ ፕሮጀክት በክልሉ መንግስት እና በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ትብብር የተከናወነ ሲሆን ግንባታውን የክልሉ የልማት ድርጅት ህብር ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን በፍጥነት እና ጥራት ተገንብቷል ብለዋል።

የአካባቢው አስተዳደርና ማህበረሰብ ለፕሮጀክቱ ያደረጉት ድጋፍ እና ትብብር የሚደነቅ ሲሆን ድልድዩ ለአገር አቋራጭ የህዝብ ትራንስፖርት፣ መንገደኞች ደህንነትና ለኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ይኖረዋል ሲሉ ዶ/ር ጋሻው ገልጸዋል።

የምረቃ ስነስርዓቱ የተካሄደው የክልልና የዞን ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣እጩ የምርጫ ተወዳዳሪዎችና ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት ነው።

1ሺ 447ኛው አመተ ሂጅራ የኢድ- አልደሃ /አረፋ/ በአል በሰሜን ወሎዋ መርሳ ከተማ በደማቅ ሁኔታ ተከበረ።    መርሳ ፦ ግንቦት 18/2018 ዓ.ም 1ሺ 447ኛው አመተ ሂጅራ የኢድ አልአደ...
27/05/2026

1ሺ 447ኛው አመተ ሂጅራ የኢድ- አልደሃ /አረፋ/ በአል በሰሜን ወሎዋ መርሳ ከተማ በደማቅ ሁኔታ ተከበረ።

መርሳ ፦ ግንቦት 18/2018 ዓ.ም

1ሺ 447ኛው አመተ ሂጅራ የኢድ አልአደሃ /አረፋ/ በአል በሰሜን ወሎዋ መርሳ ከተማ በደማቅ ሁኔታ ተከበረ። በአሉን ህዝበ ሙስሊሙ በአንድነት በመውጣት በስግደት ስነ ስርዓት አክብሮታል።

በአሉ ሲከበር የተቸገሩ ወገኖችን በመርዳት አንድነትን በማብዛት መሆን እንዳለበ የኃይማኖት አባቶች አሳስበዋል።

የእምነቱ ተከታዮችም የስግደት ስነስርአቱን ሀይማኖታዊ ክዋኔውን ጠብቀው በስኬት አካሂደዋል።

የመርሳ ከተማ አስተዳደርም የጸጥታ አካላትን፣ የትራንስፖርትና መንገድ ደህንነት እንዲሁም የኮሙኒኬሽንና ሚዲያ ግንኙነት አካላትን በአሉን እንዳጅቡና በስኬት እንድጠናቀቅ በቂ ስምሪት በመስጠት ድርሻውን ተወጥቷል፡፡

መርሳ ኮሙኒኬሽን

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች ፣ እንኳን ለ1 ሺ 447ኛው የዒድ አል-አድሃ (ዓረፋ) በዓል በሠላም አደረሳችሁ! እያልኩ መልካም ምኞቴን እገልፃለሁ።አቶ ከድር ሙስጦፋ የሰሜን ወሎ ዞን ...
26/05/2026

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች ፣ እንኳን ለ1 ሺ 447ኛው የዒድ አል-አድሃ (ዓረፋ) በዓል በሠላም አደረሳችሁ! እያልኩ መልካም ምኞቴን እገልፃለሁ።
አቶ ከድር ሙስጦፋ የሰሜን ወሎ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ሃላፊ

ዒድ አል-አድሃ ሙባረክ!

በሕዝበ ሙስሊሙ ዘንድ በልዩ ልዩ ሃይማኖታዊ ስነ ስርዓቶች በድምቀት ከሚከበሩት በዓላት መካከል አንዱ የሆነዉ ፣የዒድ አል-አድሃ (ዓረፋ) በዓል ከሃይማኖታዊ አስተምህሮቶቹ ባሻገር፣ማህበራዊ መስተጋብሮች እንዲነቃቁ፣ የመረዳዳትና የመደጋገፍ እሴቶችና ትዉፊቶች እንዲጠናከሩ መልካም አጋጣሚ ይፈጥራል፤ ተካፍሎ የመብላትን ፣ለተቸገሩ የመድረስን፣ የሌሎችን ችግር ለማቃለል የመነሳሳት ሥነ ልቦናን ከፍ ያደርጋል።

በተለያዩ የዞናችን ወረዳዎች እና ከተማዎች ፣በተለያዩ የሕይወት መስኮች ተሰማርተው የሚገኙ የክልላችን ተወላጆች፣ ወላጆቻቸውን፣ ቤተዘመዶቻቸውን የሚጠይቁበት፣ የሐሴትና የፍቅር መንፈስ የሚጎላበት፣ ልጆች በወላጆቻቸው ምርቃት በረከትን የሚላበሱበት፣ ተስፋቸውም የሚለመልምበት ነው _የዓረፋ በዓል።

ይህን የአብሮነትና የመደጋገፍ እሴት ሕዝበ ሙስሊሙ አጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል።

የዘንድሮው የዒድ አል-አድሃ (ዓረፋ) በዓል እየተከበረ የሚገኘው፣ ሀገራችን _ኢትዮጵያ ሰባተኛውን ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ እያከናወነች በምትገኝበት እና ለድምፅ መስጫው ዕለትም በጣት የሚቆጠሩ ቀናት በቀሩበት ዋዜማ ላይ ነው።
ስለሆነም መላው የዞናችን ሕዝቦች ፣ምርጫው ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩላችሁን ከመወጣት ባሻገር፣ በድምፅ መስጫው ዕለት ማልዳችሁ ድምፅ ለመስጠት ከወዲሁ እንድትዘጋጁ ጥሪ አቀርባለሁ !

መልካም የዒድ አል-አድሃ ( ዓረፋ ) በዓል!
አመሠግናለሁ !

እንኳን ለ1447ኛው አሒ ኢደል አረፋ በዓል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ ‼️የሰሜን ወሎ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አራጌ ይመርልጅን መስዋዕት እስከ ማድረግ የታመነ የአላህ (ሱ.ወ) ፍቅር የታ...
26/05/2026

እንኳን ለ1447ኛው አሒ ኢደል አረፋ በዓል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ ‼️
የሰሜን ወሎ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አራጌ ይመር

ልጅን መስዋዕት እስከ ማድረግ የታመነ የአላህ (ሱ.ወ) ፍቅር የታየበት ኢድ አል አድሃ (አረፋ)
በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ በደማቅ ከሚከበሩ በዓላት መካከል የኢድ አል አድሃ በዓል አንዱ ነው::

በመሆኑም የተከበራችሁ የዞናችን ፣ የክልላችን ፣ የሀገራችን እንድሁም በመላም አለም የምትገኙ ሙስሊም ወገኖቸ ፣ ቤተሰቦቸ ፣ ጓደኞቸ ለዚህ ለተከበረው እና ለተቀደሰው 1447ኛው አሒ ኢደል አዱሀ አረፋ በዓል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ።

ይህን በአል ከወትሮው ለየት የሚያደርገው በዓሉን ባከበርን ማግስት የሚከበረው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ነው።

ሙስሊሙ ማህበረሰብ እንደ ከዚህ ቀደሙ ሰላሙን በማስጠበቅ ፣ የተጀመረውን ልማት በማስጠበቅ በንቃት እና ሀላፊነት በተሞላበት መልኩ ምርጫውን እንድሳተፍ እና ከጎናችን እንድቆም ጥሪየን አቀርባለሁ።

ኢድ ሙባረክ ‼️

የብልጽግና ፓርቲ የድጋፍ ሰልፍ በሰላም መጠናቀቁን የአማራ ክልል ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ። በአማራ ክልል የተደረገው የብልጽግና ፓርቲ የድጋፍ ሰልፍ በሰላም መጠናቀቁን የአማራ ክልል ፖ...
26/05/2026

የብልጽግና ፓርቲ የድጋፍ ሰልፍ በሰላም መጠናቀቁን የአማራ ክልል ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ።

በአማራ ክልል የተደረገው የብልጽግና ፓርቲ የድጋፍ ሰልፍ በሰላም መጠናቀቁን የአማራ ክልል ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል።

ለዚህም የጸጥታ ኀይሉ ቀደም ብሎ ያደረገው ከፍተኛ የሰው ኀይል ስምሪት እና የሎጀስቲክስ ዝግጅት ቀዳሚውን ሚና እንደተጫወተ ነው የተገለጸው። የጸጥታ ኀይሉ የድጋፍ ሰልፉ በሰላም እንዲጠናቀቅ ከማኅበረሰቡ ጋር ተቀናጅቶ ለመሥራት ጥረት ማድረጉ ውጤታማ እንዳደረገውም ተጠቅሷል።

የጸጥታ ኀይሉ በብልጽግና ፓርቲ ድጋፍ ሰልፍ የነበረው የዝግጁነት መንፈስ ቀጣይ ለሚደረገው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫም አስተማማኝ መሠረት የጣለ እንደኾነም ተመላክቷል። ቀጣዩ ምርጫ ፍጹም ሰላማዊ ኾኖ እንዲጠናቀቅ እና ዜጎች ያለምንም ስጋት እና መሳቀቅ በነጻነት ወጥተው የሚፈልጉትን የፖለቲካ ፓርቲ መምረጥ እንዲችሉ የሰላም ጥበቃ ሥራውን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ገልጿል።

ጠቅላይ መምሪያው ሰልፉ ፍጹም ሰላማዊ ኾኖ እንዲጠናቀቅ ግንባር ቀደም ሚና ለተጫወቱ የመከላከያ ሠራዊት አባላት፣ የፌዴራል እና የክልሉ ፖሊስ፣ ሌሎች የሰላም አስከባሪ አካላት እና የጸጥታ ኀይሉን ሥራ በንቃት ላገዙ የማኅበረሰብ ክፍሎች ምሥጋና አቅርቧል።

•~•~•
•~•~•
ለወቅታዊ ፣ ትክክለኛና አዳዲስ መረጃዎች የተቋማችንን የማህበራዊ ገፆች ይወዳጁ።
ዩቲዩብ:https://www.youtube.com/
ፌስቡክ:https://www.facebook.com/share/19dpbXvN69/
ቲክቶክ:http://tiktok.com/.communcatio
ቴሌግራም:https://t.me/+J-1GwMayZ2Y4YzVk
ትዊተር:https://x.com/Habrucomncation

ዘገባው:-የአሚኮ ነው

Address

Mersa

Opening Hours

Monday 09:00 - 17:00
Tuesday 09:00 - 17:00
Wednesday 09:00 - 17:00
Thursday 09:00 - 17:00
Friday 09:00 - 17:00

Telephone

0333330161

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Habru Woreda Government Communication Affairs Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Habru Woreda Government Communication Affairs Office:

Share