Habru Woreda Government Communication Affairs Office

Habru Woreda Government Communication Affairs Office Habru Woreda Government Communication Affairs
የሀብሩ ወረዳ መንግስት ኮሙዩኒኬ

ዜና እረፍትነሀሴ 25/2018 /ሀብሩ ኮሙዩኒኬሽን የሀብሩ ወረዳ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጽ/ቤት ባልደረባ የነበሩት ወ/ሮ ወርቅዋ ጌታቸው ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ትላንት ነሀ...
31/08/2026

ዜና እረፍት

ነሀሴ 25/2018 /ሀብሩ ኮሙዩኒኬሽን

የሀብሩ ወረዳ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጽ/ቤት ባልደረባ የነበሩት ወ/ሮ ወርቅዋ ጌታቸው ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ትላንት ነሀሴ 24/12/2018 ዓ,ም ከዚህ አለም በሞት ተለይተዋል ።

ወ/ሮ ወርቅዋ ጌታቸው በሰሜን ወሎ ዞን ሀብሩ ወረዳ አስተዳደር 01 መርጦ ቀበሌ ከአባታቸው አቶ ጌታቸው ካሳዬ ዘገዬና ከእናታቸው ወ/ሮ እማዋይ ተበጄ ይማም መስከረም 14 ,1969ዓ,ም ነበር የተወለዱት።

ወ/ሮ ወርቅዋ የ1ኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በመርጦ አንደኛ ደረጃ ት/ቤት፣የ2ኛ ደረጃቸውን በወልደያ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተከታትለዋል ። በመቀጠልም በ1999ዓ,ም በአልፋ ዩኒቨርስቲ ኮሎጅ በማኔጅመንት የትምህርት ዘርፍ ድፕሎማቸውን እንዲሁም በ2010ዓ,ም ደግሞ በህዝብ አስተዳደር የመጀመሪያ ድግሪዋን አግኝታለች ።

ወ/ሮ ወርቅዋ ከ1999-2001 ዓ,ም በመርሳ ግብርና ኮሌጅ ፣ከ2002-2007ዓ,ም በሀብሩ ወረዳ ፍትህ ጽ/ቤት፣ከ2008 ጀምሮ ትላንት ህይወቷ እስካለፈበት ጊዜ በሀብሩ ወረዳ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጽ/ቤት ባለሙያ በመሆን ለ 22 አመታት የወረዳችንን ህዝብ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ አገልግለዋል ።

ወ/ሮ ወርቅዋ የአንድ ወንድ ልጅ እናት ነበሩ።

ወ/ሮ ወርቅዋ ለነበራቸው መልካም አገልግሎት በሀብሩ ወረዳ አስተዳደር ስም ታላቅ ምስጋና እያቀረብን የቀብር ስነስራታቸው በመርሳ ፈለገ አክሊል ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን በዛሬው እለት ከቀኑ 6:00 ጀምሮ የሚፈፀም ይሆናል። ለመላው ወዳጅ ቤተሰቧና ለስራ ባልደረባቸው መፅናናትን እንዲሰጥልን እንመኛለን ።

•~•~•
•~•~•
ለወቅታዊ ፣ ትክክለኛና አዳዲስ መረጃዎች የተቋማችንን የማህበራዊ ገፆች ይወዳጁ።
ዩቲዩብ:https://www.youtube.com/
ፌስቡክ:https://www.facebook.com/share/19dpbXvN69/
ቲክቶክ:http://tiktok.com/.communcatio
ቴሌግራም:https://t.me/+J-1GwMayZ2Y4YzVk
ትዊተር:https://x.com/Habrucomncation

29/08/2026

የሰሜን ወሎ ዞን ትምህርት መምሪያ በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና 17 ተማሪዎች ከ500 በላይ በማምጣት ከፍተኛ ውጤት ማስመዝገባቸውን አሳወቀ።

ነሀሴ- 23/2018 ዓ.ም

የሰሜን ወሎ ዞን ትምህርት መምሪያ የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ተፈታኞች መካከል 17 ተማሪዎች ከ500 እስከ 567.44 ከፍተኛ ውጤት ማስመዝገባቸውን የሰሜን ወሎ ዞን ትምህርት መምሪያ ሀላፊ አቶ ሰጠ ታደሰ ገልጸዋል።

ይህ ውጤት እንዲመዘገብ ጥረት ያደረጉ መምህራን፣ ተማሪዎች፣ የተማሪ ወላጆች፣ ሱፐርቫይዘሮችና የአስተዳደር ሰራተኞች እንዲሁም የትምህርት ቤተሰቦች ምስጋና አቅርበዋል።

አንድ ሀገር መበለፅግ የሚችለው በትምህርት ብቻ ሰለሆነ ሁሉም ዜጋ ትምህርት ላይ የራሱን ድርሻ ሊወጣ እንደሚገባ አቶ ሰጠ አሳስበዋል።

በቀጣይም ተማሪዎች የተሻለ ውጤት እንዲያስመዘግቡ በየደረጃው የሚገኙ የትምህርት አመራሮች፣ ባለሙያዎች እና አጋር አካላት በቅንጅትና በትብብር እንዲሰሩ ጥሪ ቀርቧል።

የአማራ ክልል ከፍተኛ እና መካከለኛ አመራሮች የ2018 በጀት ዓመት የፓርቲ እና የመንግስት ሥራዎች ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ትውውቅ መድረክ እየተካሄደ ነው። መድ...
29/08/2026

የአማራ ክልል ከፍተኛ እና መካከለኛ አመራሮች የ2018 በጀት ዓመት የፓርቲ እና የመንግስት ሥራዎች ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ትውውቅ መድረክ እየተካሄደ ነው።

መድረኩን በመክፈቻ ንግግር ያስጀመሩት የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር አቶ አረጋ ከበደ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ፈተናዎችን በጽናት በመሻገር በሁሉም ሴክተሮች አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸውን ተናግርዋል።

ክልሉ የገጠሙትን ፈተናዎች ተሻግሮ በኢኮኖሚ እና በልዩ ልዩ የልማት መስኮች ተወዳዳሪ እንዲሆን በሁሉም ዘርፍ የተሻለ ውጤት መመዝገቡን የገለፁት ርእሰ መሥተዳድሩ በሰው ሃብት ልማት፣ በተቋም ግንባታ፣ በቴክኖሎጂ ልማት፣ ሠላምና ደኅንነትን በማረጋገጥ በኩል የተመዘገቡ ስኬቶችን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባም አስረድተዋል።

ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ አክለውም የ25 ዓመት አሻጋሪ የልማት እና የ5 ዓመት ስትራቴጂካዊ ዕቅዶችን ለመተግበር የተደረገው ጥረት የሚደነቅ መሆኑን ገልጸው የተቋማት፣ የአመራሩ እና የባለሙያው የመፈጸም አቅም ማደግ ለሕዝባችን ኢኮኖሚያዊ ብልጽግና ወሳኝ መሆኑንም አስረድተዋል።

የጋራ ግንዛቤ ለጋራ ስኬት መሠረት ነው ያሉት ርእሰ መሥተዳድሩ ከታለመው ርዕይ ለመድረስ ተቋማት ተቀናጅተው መሥራት እንዳለባቸውም አሳስበዋል።

በመርሐ ግብሩ የአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ይርጋ ሲሳይ የ2018 በጀት ዓመት የፓርቲና የፖለቲካ ስራዎችን አፈጻጸም እና የቀጣይ ዕቅድ እያቀረቡ ሲሆን የክልሉ የ2019 በጀት ዓመት የፖለቲካ ስራዎች ዕቅድ እንዲሁም የአሻጋሪ ዕድገት እና ዘላቂ ልማት ዕቅድ ትውውቅ እንደሚደረግም የተያዘው መርሐ ግብር ያመላክታል።

የደም ልገሳ ሕይወትን ለማዳን የሚያስችል የሰብአዊነት ተግባር መሆኑ ተገለፀ።ፍላቂት: ነሐሴ 22/2018 ዓ.ም(መቄት ኮሙኒኬሽን)በሰሜን ወሎ ዞን የመቄት ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት ከወልደያ ደ...
28/08/2026

የደም ልገሳ ሕይወትን ለማዳን የሚያስችል የሰብአዊነት ተግባር መሆኑ ተገለፀ።

ፍላቂት: ነሐሴ 22/2018 ዓ.ም(መቄት ኮሙኒኬሽን)በሰሜን ወሎ ዞን የመቄት ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት ከወልደያ ደም ባንክ ጋር በመተባበር በክረምት ወራት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የደም ልገሳ መርሃ ግብር በፍላቂት ጤና ጣቢያ አካሂዷል።

በደም ልገሳ መርሀ ግብሩ ላይ የመቄት ወረዳ እና የፍላቂት ገረገራ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ሰራተኞች ተሳትፈዋል።

በደም ልገሳው የተሳተፉ የመንግስት ሰራተኞች በሰጡት አስተያየት የደም ልገሳ ሕይወትን ለማዳን የሚያስችል የሰብአዊነት ተግባር መሆኑን ገልፀዋል።

የህብረተሰቡን የእርስ በርስ ትስስር እና የትብብር መንፈስ የሚያጠናክረው ይህ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በደም እጥረት ምክንያት የሚከሰቱ የሞት አደጋዎችን ለመቀነስ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለውም ተናግረዋል።

የጤና ባለሙያዎች በበኩላቸው ደም ልገሳ በሕክምና ሂደት ውስጥ ሊተካ የማይችል ሲሆን ለአደጋ ተጎጂዎች፣ ለቀዶ ጥገና ታካሚዎች፣ ለእናቶችና ለተለያዩ የጤና ችግኝ ያጋጠማቸው ሰዎች ሕይወትን ለማዳን ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።

ባለሙያዎች ማህበረሰቡ የደም ልገሳን እንደ ልማድ በመውሰድ በየጊዜው ደም እንዲለግስ ጠይቀዋል። በተለይም በደም እጥረት የተነሳ የታካሚዎች ሕክምና እንዳይስተጓጎል ማህበረሰቡ የሚችለውን ድጋፍ ማድረግ እንዳለበት አሳስበዋል።

ዛሬ የተጀመረው ይህ የደም ልገሳ መርሃ ግብርም በነገው እለትም የሚቀጥል በመሆኑ ህብረተሰቡም ደም በመለገስ ሕይወትን እንዲያድን የመቄት ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት ጥሪ አቅርቧል።

በመርሳ ከተማ ከተሽከርካሪ ባለንብረቶች ጋር ውይይት ተካሄደነሐሴ 22/2018 ዓ.ም  መርሳየውጫዊ የወረራ ስጋትን እና የውስጣዊ የፅንፈኝነት አደጋን በመቀልበስ ዘላቂ ሰላምንና ልማትን እናረጋ...
28/08/2026

በመርሳ ከተማ ከተሽከርካሪ ባለንብረቶች ጋር ውይይት ተካሄደ

ነሐሴ 22/2018 ዓ.ም መርሳ
የውጫዊ የወረራ ስጋትን እና የውስጣዊ የፅንፈኝነት አደጋን በመቀልበስ ዘላቂ ሰላምንና ልማትን እናረጋግጣለን በሚል መሪ ቃል በመርሳ ከተማ ከተሽከርካሪ ባለንብረቶች ጋር የውይይት መድረክ ተካሄደ።

መድረኩን የመርሳ ከተማ አስተዳደር የብልፅግና ፓርቲ የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ የሆኑት አቶ በሪሁን አበበ በመምራት በሰላም በልማትና በከተማዋ እንቅስቃሴ ውስጥ የተሽከርካሪ ባለንብረቶች ያላቸውን ሚና አስመልክቶ ሰፊ ማብራሪያ ተሰጥቷል።

አቶ በሪሁን በአካባቢው የተፈጠሩ የሰላምና የፀጥታ ችግሮችን በጋራ ለመፍታት ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የየራሱን ኃላፊነት እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል። በተለይም ተሽከርካሪዎች ለሕገወጥ እና ለጎጂ ተግባራት እንዳይውሉ ባለንብረቶች ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አሳስበዋል።

በመድረኩ የተሳተፉ ባለንብረቶችም በአካባቢያቸው ሰላምን ለማስፈንና ሕግን ለማስከበር ከመንግሥት ጎን እንደሚቆሙ ገልጸዋል። በተጨማሪም ሕገወጥ ንግድን ለመከላከል ተገቢው የሕግ እርምጃ እንዲወሰድ ጠይቀዋል።

መድረኩንበጋራ በመሆን የመሩት የመርሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ ያሲን መሐመድ፣የመርሳ ከተማዋ አስተዳደር የብልፅግና ፓርቲ የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ የሆኑት አቶ በሪሁን አበበ እና ኮሎኔል ሚፍታህ ሙሀመድ በጋራ መርተውታል።

አቶ ያሲን መሐመድ በበኩላቸው በአካባቢው የሚፈጠሩ የፀጥታ ችግሮችን በተናጠል ሳይሆን በጋራ በመሥራት መፍታት እንደሚገባ ገልጸዋል።

ኮሎኔል ሚፍታህ ሙሀመድ በመጨረሻም ተሽከርካሪዎችን ለሕገወጥ ተግባራት እንዲውሉ የሚያደርጉ አካላትን በመቃወም ባለንብረቶች ከእንዲህ ዓይነት ተግባር እንዲቆጠቡ ጠይቀዋል።

ዘገባው:-የመርሳ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ነው

ከ88 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የአጆ ሜዳ ትምህርት ቤት ተመረቀ፤በሰሜን ወሎ ዞን ሀብሩ ወረዳ ከ88 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የአጆ ሜዳ አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት...
27/08/2026

ከ88 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የአጆ ሜዳ ትምህርት ቤት ተመረቀ፤

በሰሜን ወሎ ዞን ሀብሩ ወረዳ ከ88 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የአጆ ሜዳ አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተመርቋል።

የትምህርት ቤቱ ግንባታ ተጠናቆ ርክክብ የተደረገ ሲሆን፣ ትምህርት ቤቱ ከ1,000 በላይ ተማሪዎችን ማስተናገድ የሚችልና ደረጃውን የጠበቀ መሠረተ ልማት እንዳለው ተገልጿል።

የሰሜን ወሎ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ ታምራት ንጋቱ፤ ልማቶች እውን የሚሆኑት በአካባቢው ሰላም ሲሰፍንና ለልማት የሚተባበር ማኅበረሰብ ሲኖር መሆኑን ገልጸው፣ ግንባታው በደረጃው መሠረት ተጠናቆ ለአገልግሎት መዘጋጀቱን ገልጸዋል።

ትምህርት ቤቱ ለ2019 ዓ.ም. የትምህርት ዘመን ማስጀመሪያ የሚያስፈልጉ ግብዓቶች እንደተሟሉለት የገለጹት አቶ ታምራት፣ ተቋሙ የተሟላ አገልግሎት እንዲሰጥ የመብራት፣ የውሃና የአጥር ሥራዎችን ከማኅበረሰቡና ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ ጥረት እንደሚደረግ አስታውቀዋል።

የወልድያ ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ዱባለ አብራሬ በበኩላቸው፤ አዲሱ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ምቹ በሆነ አካባቢ ተምረው እንዲያድጉ ከማስቻሉም በላይ በአካባቢው የሚገኙ ተፈናቃይ ተማሪዎችን አካቶ ለማስተማር ጉልህ ሚና እንዳለው ገልጸዋል።

ትምህርት ቤቱ ከትውልድ ትውልድ በጥራት እንዲተላለፍ ማኅበረሰቡ ሊጠብቀውና ሊንከባከበው እንደሚገባም አሳስበዋል። ያልተጠናቀቁ ቀሪ ሥራዎችንና መሟላት የሚገባቸውን ጉዳዮች ለማጠናቀቅም ጥረት እንደሚደረግ ገልጸዋል።

የሰሜን ወሎ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ሰጠ ታደሰ፤ ትምህርት ቤቱ ቀደም ሲል በተለያዩ ምክንያቶች ከሚጠበቀው ደረጃ በታች እንደነበር ገልጸው፣ አሁን ግን ከ1,000 በላይ ተማሪዎችን ማስተናገድ የሚችል ደረጃውን የጠበቀ ግንባታ ተጠናቆ መረከቡን ተናግረዋል።

ግንባታው በፌዴራል ከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር አማካይነት ከዓለም ባንክ በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ የተከናወነ ሲሆን፣ ለፕሮጀክቱ 88 ሚሊዮን 28 ሺህ 108 ብር ወጪ መደረጉን አቶ ሰጠ ገልጸዋል።

ትምህርት ቤቱ 9 ብሎኮችን ያካተተ ሲሆን፣ ግንባታው በጥራት ተከናውኖ በአምስት ወራት ውስጥ ተጠናቆ ለአገልግሎት መዘጋጀቱ ተገልጿል።

በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የተገኙ ተሳታፊዎች በበኩላቸው፤ ትምህርት ቤቱ መገንባቱ ልጆች በምቹ አካባቢ ተምረው በእውቀትና በአመለካከት የተሻሉ ዜጎች እንዲሆኑ እንደሚያግዝ ገልጸዋል። ቀሪ ሥራዎችም በአጭር ጊዜ እንዲጠናቀቁና ትምህርት ቤቱ በአግባቡ እንዲጠበቅና እንዲንከባከብ ጠይቀዋል።

መረጃው የሰሜን ወሎ ዞን ኮሙዩኒኬሽን ነው።

በ2018 ዓ/ም በሰሜን ወሎ ዞን ሀብሩ ወረዳ  ሀገር አቀፍ የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት የመልቀቂያ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎችን የወረዳው ት/ጽ/ቤት አሳታውቋል።መር...
27/08/2026

በ2018 ዓ/ም በሰሜን ወሎ ዞን ሀብሩ ወረዳ ሀገር አቀፍ የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት የመልቀቂያ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎችን የወረዳው ት/ጽ/ቤት አሳታውቋል።

መርሳ ፦ ነሀሴ 21/2018 ዓ.ም/ሀብሩ ኮሙዩኒኬሽን

በሰሜን ወሎ ዞን ሀብሩ ወረዳ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን አጠናቀው ሀገር አቀፍ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የመልቀቂያ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል
1ኛ. ተማሪ ጌታሁን መኩሪያው አራጌ 537/600 ከመርሳ 2ኛ ደረጃና መሰናዶ ት/ቤት

2ኛ.ተማሪ ሙሀመድ እንድሪያስ አስረሴ 503/600 ማምጣት ከመርሳ 2ኛ ደረጃና መሰናዶ

3ኛ. ዘይኑ አህመድ ተሾመ ሲሆን ያስመዘገበው ውጤት 502.91 ከስሪንቃ ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ት/ቤት በመሆን ከፍተኛ ውጤት ማስመዝባቸውን የሀብሩ ወረዳ ት/ጽህፈት ቤት የላከው መረጃ ያመላክታል ።

የሀብሩ ወረዳ ት/ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ መንገሻ ደረጄ እንደገለፁት በዚህ አመት ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች ትልቅ ምስጋና አቅርበው ሌሎች ከኃላ የሚመጡ ልጆች የእነሱን ፈለግ በመከተል ከዚህ በላይ ውጤት ለማስመዝገብ ጠንክረው እንዲያጠኑ ሲሉ አሳስበዋል ።

•~•~•
•~•~•
ለወቅታዊ ፣ ትክክለኛና አዳዲስ መረጃዎች የተቋማችንን የማህበራዊ ገፆች ይወዳጁ።
ዩቲዩብ:https://www.youtube.com/
ፌስቡክ:https://www.facebook.com/share/19dpbXvN69/
ቲክቶክ:http://tiktok.com/.communcatio
ቴሌግራም:https://t.me/+J-1GwMayZ2Y4YzVk
ትዊተር:https://x.com/Habrucomncation

በሀብሩ ወረዳ "ውጫዊ የወረራ ስጋትና ውስጣዊ የፅንፈኝነት አደጋን በመቀልበስ ዘላቂ ሰላምና ልማትን እናረጋግጣለን" በሚል መሪ ሀሳብ የመንግስት ሰራተኞች ውይይት ተካሄደ።​መርሳ፡- ነሀሴ 21...
27/08/2026

በሀብሩ ወረዳ "ውጫዊ የወረራ ስጋትና ውስጣዊ የፅንፈኝነት አደጋን በመቀልበስ ዘላቂ ሰላምና ልማትን እናረጋግጣለን" በሚል መሪ ሀሳብ የመንግስት ሰራተኞች ውይይት ተካሄደ።

​መርሳ፡- ነሀሴ 21/2018 ሀብሩ ኮሙዩኒኬሽን

በሰሜን ወሎ ዞን የሀብሩ ወረዳ አስተዳደር ከጠቅላላ የመንግስት ሰራተኞች ጋር «ውጫዊ የወረራ ስጋትና ውስጣዊ የፅንፈኝነት አደጋን በመቀልበስ ዘላቂ ሰላምና ልማትን እናረጋግጣለን» በሚል መሪ ሀሳብ ያዘጋጀውን የውይይት መድረክ አካሂዷል።

የውይይት መነሻ ጽሁፍ በሀብሩ ወረዳ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጽ/ቤት ሀላፊ በሆኑት በአቶ አሰፋ አያሌው የቀረቡ ሲሆን በዋናነት ፅንፈኝነትን ለማዳከም የተሰሩ ስራዎች ፣በክልሉ በተፈጠረው ቀውስ በህዝባችን ለይ የደረሱ ጉዳቶች፣አሁን የተደቀኑ የወረራ ስጋቶች እና የተደቀኑብንን የውስጥ ፅንፈኝነትና የውጭ ወረራ ስጋትን መክተን እንደት ዘላቂ ሰላምንና ልማትን እናረጋግጣለን የሚሉ ሀሳቦች በዝርዝር ቀርበው ሰፊ ውይይት ተካሂዶባቸዋል።

​በመድረኩ የፅንፈኝነትንና የውጭ ስጋቶችን አሉታዊ ተፅዕኖ በመመከት ሰላምን ማስፈን እና የወረዳውን ልማት ማፋጠን በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።

ውይይቱን የመሩት የወረዳው ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ሀላፊ ወ/ሪት ብርቱካን አባቡ እንደገለፁት ​የሰላምና ደህንነት ጉዳይ፡ የአካባቢውን ሰላም ዘላቂ ለማድረግ የፅንፈኝነት አስተሳሰብንና ህገ-ወጥ እንቅስቃሴዎችን ማውገዝ እንዲሁም የወረዳውን ህዝብ ደህንነት የሚፈታተኑ ውጫዊ እና ውስጣዊ ስጋቶችን በጋራ መመከት እንደሚገባ ተናግረዋል ።

​የሀብሩ ወረዳ የሲቪል ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ደሳለ ፈንታው ባስተላለፉት መልዕክት የመንግስት ሰራተኞች የአገልግሎት አሰጣጣቸውን በማሻሻል፣ የህዝቡን ቅሬታ በመቀነስና ከህብረተሰቡ ጎን በመቆም የህግ የበላይነት እንዲከበር ከፊት ተሰላፊ መሆን እንዳለባቸው አስገንዝበዋል ።
​ልማትን ማስቀጠል፡ ዘላቂ ሰላም ሳይኖር የተጀመሩ የልማት ስራዎችን ማሳካት እንደማይቻል በመግለፅ፣ ሰራተኛው በየተሰማራበት ዘርፍ ውጤታማ ስራ በማከናወን የህዝቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንዳለበት ጠቁመዋል።

​የውይይቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው የወረዳውን ሰላምና ደህንነት ለማስጠበቅ፣ ህገ-ወጥነትን ለመታገል እና ለአገልግሎት ፈላጊው ህብረተሰብ ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል።
​በመጨረሻም የመድረኩ አስተባባሪዎች እንደተናገሩት፣ የተጀመሩ የሰላምና የልማት ስራዎች ግባቸውን እንዲመቱ የመንግስት ሰራተኛው ያሳየውን ቁርጠኝነት አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ የቀረበ ሲሆን፤ መድረኩ በቀጣይ የስራ አቅጣጫዎች ስምምነት ላይ በመድረስ ተጠናቋል።

"ሰላም ለሁሉም ሁሉም ለሰላም"

•~•~•
•~•~•
ለወቅታዊ ፣ ትክክለኛና አዳዲስ መረጃዎች የተቋማችንን የማህበራዊ ገፆች ይወዳጁ።
ዩቲዩብ:https://www.youtube.com/
ፌስቡክ:https://www.facebook.com/share/19dpbXvN69/
ቲክቶክ:http://tiktok.com/.communcatio
ቴሌግራም:https://t.me/+J-1GwMayZ2Y4YzVk
ትዊተር:https://x.com/Habrucomncation

የሀብሩ ወረዳ ብልፅ ፓርቲ ቅ /ፅ/ቤት ውጫዊ የወረራ ሰጋት እና ውስጣዊ የፅንፈኝነት አደጋን በመቀልበስ ዘላቂ ሰላምና ልማትን እናረጋግጣለን በሚል መሪ ሀሳብ  ከመንግስት ሰራተኛ አባላት ጋር...
26/08/2026

የሀብሩ ወረዳ ብልፅ ፓርቲ ቅ /ፅ/ቤት ውጫዊ የወረራ ሰጋት እና ውስጣዊ የፅንፈኝነት አደጋን በመቀልበስ ዘላቂ ሰላምና ልማትን እናረጋግጣለን በሚል መሪ ሀሳብ ከመንግስት ሰራተኛ አባላት ጋር ዉይይት አደረገ።

ነሀሴ 20/2018/ሀብሩ ኮሙዩኒኬሽን

በሰሜን ወሎ ዞን በሀብሩ ወረዳ ባለፋት አመታት በክልላችን ብሎም በወረዳችን ተከስቶ የነበረው ቀውስ አንፃራዊ በሆነ መልኩ እየተሻሻለ የመጣ ቢሆንም ይህን ሰላም ለማደናቀፍ የፅፈኘነት አስተሳሰብ ያላቸው ሀይሎች ስላሉ ይህንን ሀሳብ ለማረምና የጋራ መግባባት ለመፍጠር የሚያስችል ውይይት ከመንግስት ሰራተኛ አባላት ጋር ተካሂዷል ።
በውይይቱ የተገኙት የሀብሩ ወረዳ የብልፅግና ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ሀላፊ አቶ ብርሀን ጌትነት በመክፈቻ ንግግራቸው እንዳሉት ሰላም የሌለው ሀገር ልማት የለውም የልማትና የእድገት እውነተኛ ባለቤት ለመሆን የሰላምን ዋጋ ማወቅና መተግበር ያስፈልጋል። ያለሰላም ማህበራዊ መረጋጋትም ሆነ ኢኮኖሚያዊ አምርታ በፋፁም ሊኖር አይችልም ስለዚህ በሰላሙና በልማቱ ዙሪያ የጋራ መግባባት በመፋጠር ሁላችንም የድርሻችንን ለመወጣት ነው ሲሉ የውይይቱን አላማ ገልፀዋል።

የሀብሩ ወረዳ የስራ ክህሎት ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ይበልጣል በላይ በሰነዱ ላይ እንደገለፁት በክልላችን ብሎም በወረዳችን ስር የሰደዱ ችግሮችን ለመፍታትና የህዝባችንን መሰረታዊ ጥያቄዎች ለመመለስ ጥረት ሲደረግ ቆይቷል ይሁን እንጅ በክልላችን ብሎም በወረዳችን ዘለቂ ሰላም እንዳይረጋገጥ በውስጣዊም ሆነ በውጫዊ ያሉት ሀይሎች አላማቸው ሀገራችንን ማፋረስ፣የግዛት አንድነትን ማፋረስ፣የክልላችንን ንብረት ማውደምና መዝረፍ፣ስነልቦናዊ ጉዳት ማድረስ ፣ህይወት ማጥፍት እና ሌሎችም መሆናቸዉን በሰነዱ ገልፀው። አሁንም አመራራቸንም ሆነ ባለሙያው ይህንን በውል ተረድቶ ከአሉቧልታ በመወጣት ዉስጣዊ አንድነታችንን በማጠናከረ፣ነባራዊ ሁኔታዉን በመረዳት ከፀጥታው አካል ጋር በመተባበርና ትክክለኛ መረጃ በመስጠት ዘላቂ ሰለምና ልማት ለማረጋገጥ ሁላችንም የዲርሻችንን እንወጣ ሲሉ በገለፃቸው አስረድተዋል ።

የሀብሩ ወረዳ ፕላንና ልማት ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ደሳለ ወርቁ በማጠቃለያ ንግግራቸው፣ የፓርቲ አባላት የውይይቱን ሀሳቦች በተግባር በመተርጎም ለሰላም፣ ለልማትና ለህዝብ ጥቅም በተቀናጀ መልኩ መስራት እንዳለባቸው ገልጸዋል።
በተለይም የፓርቲ አባላት የአደረጃጀት አቅማቸውን በማጠናከር፣ ከህዝብ ጋር ያላቸውን ቀጥተኛ ትስስር በማጠናከርና የሚነሱ ችግሮችን በውይይትና በጋራ ተሳትፎ በመፍታት ለወረዳው ሰላማዊና ልማታዊ ጉዞ የራሳቸውን ድርሻ እንዲወጡ አሳስበዋል።
አክለውም፣ ውጫዊ የወረራ ስጋትንና ውስጣዊ የጽንፈኝነት አደጋን በመመከት የሀገርን ሰላም ማስጠበቅ፣ የልማት ውጤቶችን ማስፋፋትና የህዝብን ተሳትፎ ማጠናከር የአባላት ቀጣይ ትኩረት መሆን እንዳለበት ጠቁመዋል።

•~•~•
•~•~•
ለወቅታዊ ፣ ትክክለኛና አዳዲስ መረጃዎች የተቋማችንን የማህበራዊ ገፆች ይወዳጁ።
ዩቲዩብ:https://www.youtube.com/
ፌስቡክ:https://www.facebook.com/share/19dpbXvN69/
ቲክቶክ:http://tiktok.com/.communcatio
ቴሌግራም:https://t.me/+J-1GwMayZ2Y4YzVk
ትዊተር:https://x.com/Habrucomncation

Address

Mersa

Opening Hours

Monday 09:00 - 17:00
Tuesday 09:00 - 17:00
Wednesday 09:00 - 17:00
Thursday 09:00 - 17:00
Friday 09:00 - 17:00

Telephone

0333330161

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Habru Woreda Government Communication Affairs Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Habru Woreda Government Communication Affairs Office:

Shortcuts

Share