Guraferda woreda communication

Guraferda woreda  communication ቢፍቱ ጉራፈርዳ

የጉራፈረዳ ወረዳ  የሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮግራም የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸምን ገመገመ‎‎የጉራፈረዳ ወረዳ የሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮግራም የ2018 በጀት ዓመት የተግባራትና የካፒታል በጀት አፈ...
02/09/2026

የጉራፈረዳ ወረዳ የሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮግራም የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸምን ገመገመ

‎የጉራፈረዳ ወረዳ የሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮግራም የ2018 በጀት ዓመት የተግባራትና የካፒታል በጀት አፈጻጸም የፌደራል እና የክልል አካላት በተገኙበት ገምግሞ የቀጣይ አቅጣጫ አስቀምጧል።

የጉራፈረዳ ወረዳ አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተመስጌን ጨምዴሳ እንደገለፁት በወረዳችን ሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮግራም የማህበረሰቡን ችግር ከመቀነስም ባለፈ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት አልሞ እየሰራ ያለ መሆኑን ጠቅሰዉ ፕሮግራሙ ትኩረት ለሚሹ የህብረተሰብ ክፍሎች የሚሰራ በመሆኑ በ2019 የተሻለ ውጤት ለማምጣት ተቀናጅተን እንሰራለን ብለዋል።

‎በመድረኩ የሰቆጣ ቃል ኪደን ፕሮግራም በጤና፣ በግብርና፣ በሴቶችና ህጻናት ፣ በውሃ ፣ በእንስሳትና በሌሎችም ዘርፍ በ2018 በጀት ዓመት የተግባራት አፈጻጸም ሪፖርት የጉራፈረዳ ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት የእናቶችና የህፃናት የስራ ሂደት አስተባባሪ አቶ ታሪኩ ተስፋዬ በዝርዝር አቅርበው ውይይት ተደርጎበታል።

ከፌደራል ጤና ሚኒስተር ‎እና ከክልል ጤና ቢሮ የመጡ ባለድርሻ አካላት እንደገለፁት በወረዳው በሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮግራም በጀት ዓመት የተከናወኑ የልማት ስራዎች መሬት ላይ የሚታዩ፣በጥራትና በፍጥነት የተከወኑ መሆናቸው የሚበረታታ መሆኑን ገልፀው ቀጣይ ዘላቂ ሃብት እንዲሆኑ ተቋማት ኃላፊነታቸው ሊወጡ እንደሚገባ ተናግረዋል::

ለሰቆጣ ፕሮግራም የተበጀተን በጀት ለታለመለት አላማ በማዋል ተግባራትን በተያዘለት የጊዜ ገደብ ለማጠናቀቅ በመቀናጀትና በመናበብ መስራት እንደሚያስፈልግ አቅጣጫ ተቀምጧል።

የፕሮግራሙ አላማ ለማሳካት እየተሰሩ ያሉ የግንዛቤ ማስጨበጫና የካፒታል ስራዎች አቀናጅተን በመምራት በአዕምሮና በአካል የዳበረ ትውልድ መፍጠር የሁላችንም ተግባርና ኃላፊነት በመሆኑ ለቀጣይ ለ2019 በጀት አመት ለበለጠ ውጤት እንሰራለን በማለት የመድረኩ ተሳታፊዎች ተናግረዋል።

‎ የፍትህ ሥራ ውጤታማ ለማድረግ የቅንጅት ሥራን ማጠናከር ይገባል። አቶ ቢኒያም ባቡየቤንች ሸኮ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ከስር  የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤቶች  እና ከዞን ባለድርሻ አካላት ጋ...
02/09/2026

‎ የፍትህ ሥራ ውጤታማ ለማድረግ የቅንጅት ሥራን ማጠናከር ይገባል። አቶ ቢኒያም ባቡ

የቤንች ሸኮ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ከስር የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤቶች እና ከዞን ባለድርሻ አካላት ጋር የ2018 በጀት ዓመት አፈፃፀምእና በ2019 ጠቋሚ ዕቅድ ላይ በቢፍቱ ከተማ የምክክር መድረክ አካሂዷል።

የቤንች ሸኮ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ቢኒያም ባቡ እንደገለፁት የፍትህን ሥራ ውጤታማነት ለማረጋገጥ የቅንጅት ሥራዎችን ማጠናከር ይገባል ብለዋል።

ባህላዊ ፍርድ ቤቶች በአዋጅ የተቋቋሙ እንጂ ከተሰጣቸው ኃላፊነትና ወሰን የሚወጡትን አለመሆኑን ተናግረዋል።

በስር መዋቅሮች ላይ የተዘዋዋሪ ችሎት እና ምድብ ችሎት ሥራዎች ጠቅላላ የቀረበ ወንጀል 453 ፍታብሔር 1093 በድምሩ 1546 መዝገብ ቀርቦ በወንጀል ፣ 311 በፍታብሔር 809 በድምሩ 1324 መዝገብ ውሳኔ አገኝቷል።

‎ በሙስና መዝገብ 31ቀርቦ 29 ሲወሰን 2 መዝገብ ወደ ቀጣይ በጀት ዓመት ተላልፏል።

በበጀት ዓመቱ ውስጥ የሴቶችና ህፃናት ጥቃትና መብት ጥሰት 290 መዝገብ ቀርቦ 270 መዝገብ የተወሰነ መሆን 20 መዝገብ ወደ ቀጣይ በጀት ዓመት ተላልፏል።

የቤንች ሸኮ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ሻምበል ቡሽ እንደተናገሩት ባህላዊ እና ማህበራዊ ፍርድ ቤቶችን ድጋፍና ክትትል በማጠናከር ከተሰጠቸው ኃላፊነት ውጪ የሚሰሩ ከሆነ ወደ ህጋዊነት እንዲመጡ ማድረግ ይገባል ብለዋል ።

በስር መዋቅሮች በተደረገ ድጋፍና ክትትል የታዩ ጥንካሬና መሻሻል ያለባቸውን ነጥቦች በዞኑ ከፍተኛ ፍርድቤት ዳኛ በአቶ እዮብ ሀይሉ በዝርዝር ቀርቧል።

የምክክር መድረኩ ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት ከባህላዊ ፍርድቤት አንፃር ወጥ የሆነ ነገር አለመኖሩ ሊታረም እንደሚገባ ጠቁመዋል።

በምክክር መድረኩም በ2018 በጀት ዓመት የተሻለ አፈፃፀም ላስመዘገቡ ጉራፈርዳ ወረዳ፣ ሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር እና ሼይቤንች ፤ ወረዳ ፣ ከዳኞች ፣ከረዳት ዳኞች፣ ከአስተዳደር ዘርፍ ፣ከጋራ አገልግሎት የተሻለ አፈፃፀም ላስመዘገቡ የእውቅና ሰርተፊኬትና የማበረታቻ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።

በጉራፈረዳ ወረዳ  አመራሮች ማጠቃለያ የግምገማና ምዘና መድረክ መካሄድ ጀመረ:የጉራፈረዳ ወረዳ ከድል ማግስት ጠንካራ መንግስት" በሚል የ2018 በጀት ዓመት ማጠቃለያ የአመራር ግምገማና ምዘና...
02/09/2026

በጉራፈረዳ ወረዳ አመራሮች ማጠቃለያ የግምገማና ምዘና መድረክ መካሄድ ጀመረ:

የጉራፈረዳ ወረዳ ከድል ማግስት ጠንካራ መንግስት" በሚል የ2018 በጀት ዓመት ማጠቃለያ የአመራር ግምገማና ምዘና መድረክ መካሄድ ጀምሯል።

የቤንች ሸኮ ዞን ስራና ክህሎት መምሪያ ምክትል ኃላፊ አቶ ታምራት ከተማ እንደገለፁት መድረኩ ዋና አላማ በአመራሩ ዉስጥ በተግባራት አፈፃፀም የሚታዩ ጉድለቶችን ፈትሾ የማጥራት ስራ የሚሰራበት መሆኑን ገልፀው በጥንካሬ የታዩትን ይበልጥ ለማጎልበት፣ ጉድለቶችን ለማረምና በአመራሩ መካከል የአስተሳሰብና የተግባር አንድነት ለመፍጠር ተነሳሽነት ለመፍጠር ያለመ መድረክ እንደሆነ ተናግረዋል።

በፓርቲና በመንግስት የተከናወኑ ተግባራትን በመፈተሽ አመራሩን ለቀጣይ ተልዕኮ ዝግጁነት መፍጠር እንዲያስችል እንደሆነ ገልጸዋል።

የቤንች ሸኮ ዞን ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት መምሪያ ምክትል ኃላፊ አቶ ሰለሞን ገረመው አመራሩ የመንግስትና የፓርቲ ተግባራትን በዲስፕሊን ከመምራት ጀምሮ የአመለካከትና የመፈፀም ደረጃ የተቀራረበና የተናበበ በማድረግ በየዘርፉ ውጤታማ ስራ ለመስራትና የብልጽግና ጉዞ መጠናከር እንዲሁም በመልካም አስተዳደርና በልማት ስራዎች የህዝቡ ተጠቃሚነት መረጋገጥ ሊሠራ ይገባል ብለዋል።

በበጀት ዓመቱ በፓርቲና በመንግስት የተከናወኑ የተግባራት አፈፃፀም ሪፖርትን የጉራፈረዳ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ የፖለቲካና የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ የሴፍ ታምሩ ያቀረቡ ነው ።

ግምገማውም ለተከታታይ ሶስት ቀናት የሚቆይ ሲሆን በመድረኩ አጠቃላይ የወረዳው አመራሮች ተገኝተዋል።

የጳጉሜን ቀናት የኢትዮጵያ ስኬቶች እና ፈተናዎችን አልፎ የመሻገር አቅም በሚያሳይ ሁኔታ ይከበራል የጳጉሜን ቀናት የኢትዮጵያ ስኬቶች እና ፈተናዎችን አልፎ የመሻገር አቅም በሚያሳይ ሁኔታ እን...
02/09/2026

የጳጉሜን ቀናት የኢትዮጵያ ስኬቶች እና ፈተናዎችን አልፎ የመሻገር አቅም በሚያሳይ ሁኔታ ይከበራል

የጳጉሜን ቀናት የኢትዮጵያ ስኬቶች እና ፈተናዎችን አልፎ የመሻገር አቅም በሚያሳይ ሁኔታ እንደሚከበር የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ከበደ ዴሲሳ አስታወቁ።

ሚኒስትር ዴኤታው የ2018 ዓ.ም የአዲስ ዓመት ዋዜማ አምስቱ የጳጉሜን ወር ቀናት አከባበር ዝግጅትና ስያሜን አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል።

የጳጉሜን ቀናት ባለፉት ዓመታት የተመዘገቡ ትላልቅ ሀገራዊ ስኬቶች እና እመርታዊ ውጤቶች የሚታወሱበትና ህዝቡ እንዲያቃቸው የሚደረግበት መሆኑን አመልክተዋል።

ውስብስብ ፈተናዎችን አልፎ የመሻገር አቅምን ማጠናከር እና ለስኬት ያበቁ ተሞክሮዎችን የሚቀመርበት መሆኑን ተናግረዋል።

የ2018 ዓ.ም አዲስ ዓመት ዋዜማ አምስቱ የጳጉሜን ቀናት በሀገር አቀፍ ደረጃ በተለያየ ዝግጅትና ስያሜ ለማክበር የቅድመ ዝግጅት ስራዎች መከናወናቸውን ጠቅሰዋል።

ጳጉሜን 1 (የእመርታ ቀን)፣ ጳጉሜን 2 (የማንሰራራት ቀን)፣ ጳጉሜን 3 (የጽናት ቀን)፣ ጳጉሜን 4 (የኅብር ቀን) እንዲሁም ጳጉሜን 5 (የነገ ቀን) በሚሉ ስያሜዎች እንደሚከበር አመልክተዋል።

ቀናቱም በሀገር አቀፍ ደረጃ በሁሉም ክልሎች፣ ከተማ አስተዳደሮች፣ በመላ ዓለማት የሚገኙ የኢትዮጵያ ኤምባሲዎችና ኮሚኒቲ አባላት እንደሚከበሩ ነው የጠቆሙት።

አዲሱ ዓመት ኢትዮጵያ የጀመረችው የማንሰራራትና የእመርታ ጉዞ ይበልጥ አጠናክራ የምቀጥልበት ነው ብለዋል።

ሚኒስትር ዴኤታው አዲሱ ዓመት የብልጽግና፣ የትብብር እና የትስስር እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል። ኢዜአ

የቤንች ሸኮ ዞን ከፍተኛ  ፍርድቤት  የ2018 ዓ/ም  አፈፃፀም እና የ2019 በጀት አመት ጠቋሚ እቅድ በተመለከተ  ምክክር መድረክ  በጉራፈርዳ  ወረዳ በቢፍቱ ማካሄድ ጀምሯል።የቤንች ሸኮ ...
02/09/2026

የቤንች ሸኮ ዞን ከፍተኛ ፍርድቤት የ2018 ዓ/ም አፈፃፀም እና የ2019 በጀት አመት ጠቋሚ እቅድ በተመለከተ ምክክር መድረክ በጉራፈርዳ ወረዳ በቢፍቱ ማካሄድ ጀምሯል።

የቤንች ሸኮ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት በስሩ ከሚገኙ 6 ወረዳና 4 ከተማ አስተዳደር የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት እና ከዞን ባለድርሻ አካላት ጋር 2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም ምክክር እና 2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ምክክር መድረክ እያካሄደ ነው።

የምክክር መድረኩን በንግግር የከፈቱት የቢፍቱ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ኦሚስ ካሲካራ 6ቱ ወረዳና 4ቱ ከተማ አስተዳደር የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት እና ከዞን ባለድርሻ አካላት የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም ምክክር እና 2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ምክክር ጉባኤ መድረክ በቢፍቱ ከተማ አስተዳደር መካሄድ ለቀጣይ ተግባር ልምድ ልውውጥ የምንወስድበት መሆን አለበት በማለት ተናግረዋል።

የቤንች ሸኮ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ቢኒያም ባቡ ፍርድቤቶች የየራሳቸው አወቃቀር አደረጃጀትና ስልጣን ያላቸው መሆኑን ገልፀው በ2018 በጀት ዓመት 7562 መዝገቦች ቀርበው 6979 መዝገቦች ውሳኔ እንደተሰጠና 583 መዝገብ ወደ ቀጣይ በጀት ዓመት የተላለፈ መሆኑን ገልፀዋል።

የ2018 በጀት ዓመት ሪፖርት የቤንች ሸኮ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ቢኒያም ባቡ እያቀረቡ ሲሆን ቀጣይ አስተያየት ይሰጥበታል።

የቤንች ሸኮ ዞን ከፍተኛ  ፍርድ ቤት  የ2018  አፈፃፀም እና የ2019 ጠቋሚ እቅድ ዙሪያ ምክክር መድረክ  በጉራፈርዳ  ወረዳ በቢፍቱ ከተማ  አስተዳደር ለማካሄድ የአዳራሽ ዝግጅት  ጨርሶ...
02/09/2026

የቤንች ሸኮ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የ2018 አፈፃፀም እና የ2019 ጠቋሚ እቅድ ዙሪያ ምክክር መድረክ በጉራፈርዳ ወረዳ በቢፍቱ ከተማ አስተዳደር ለማካሄድ የአዳራሽ ዝግጅት ጨርሶ እንግዶችን እየጠበቀ ነዉ

በጉራፈረዳ ወረዳ የ2019 በጀት አመት የአስፈፃሚ ተቋማት  ጠቋሚ ዕቅድ ግምገማና በ2019 ዓ/ም በጀት ረቂቅ ዙሪያ የጋራ ውይይት መድረክ ተካሄዴ።በጉራፈረዳ ወረዳ የ2019 በጀት አመት የአ...
01/09/2026

በጉራፈረዳ ወረዳ የ2019 በጀት አመት የአስፈፃሚ ተቋማት ጠቋሚ ዕቅድ ግምገማና በ2019 ዓ/ም በጀት ረቂቅ ዙሪያ የጋራ ውይይት መድረክ ተካሄዴ።

በጉራፈረዳ ወረዳ የ2019 በጀት አመት የአስፈፃሚ ተቋማት ጠቋሚ ዕቅድ ግምገማና በ2019 በጀት ረቂቅ በጀት ዙሪያ የጋራ ውይይት መድረክ በማካሄድ የትኩረት አቅጣጫ ተቀምጧል።

የጉራፈረዳ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታጋይ ኤሊያስ የግምገማው ዋና አላማ ሁሉም ተቋማት አንድ እቅድ አንድ ሪፖርት መሰረት በማድረግ ተግባራትን በእቅድ መሰረት ለመፈፀም እና በዉስንነት የታቀዱ እንድሁም የተንዛዙ እቅዶችን ለማስተካከል ያለመ ግምገማ እንደሆነ ገልፀዋል።

በግምገማውም የአስፈጻሚ ተቋማት ጠቋሚ እቅድ በኢኮኖሚ፣በማህበራዊ እና በአስተዳደር ዘርፍ ዝርዝር ተግባራት የጉራፈረዳ ወረዳ ፕላን ጽ/ቤት ኃላፊ በአቶ እንዳለመው እድሜ እና የ2019 በጀት ዓመት የበጀት ረቂቅን የፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዮሐንስ መከራ ቀርቦ ተገምግም አቅጣጫ ተቀምጧል።

በመድረኩም የጉራፈረዳ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኦይሳ አለሙ እቅዱን ለመፈፀም በመቀናጀት ትኩረት የሚሹ ተግባራትን በመለየት በተለይም የህዝብን የልማት ፍላጎቶች ለማሟላት ገቢ አሰባሰብ ላይ አቅምን አሟጦ መስራት እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።

የጉራፈረዳ ወረዳ ም/አስተዳዳሪና የግብርና አካባቢ ጥበቃ ህብረት ስራ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መስፍን አስፋው የታቀደው እቅድ አፈጻጸሙ ከተቋማት ግብ አስተሳስሮ ከመሄድ አንጻር የሚስተዋሉ ክፍተቶች በመቅረፍ ህብረተሰቡን ይበልጥ ተጠቃሚ ለማድረግ ባለሙያው በቁርጠኝነት ሊሰራ እንደሚገባ ተናግረዋል።

የመድረኩ ተሳታፊዎች እንዳነሱት በ2019 በጀት አመት የታቀዱ እቅዶችን በተሰጠው ማስተካከያ መሰረት ተቀናጅተን እንተገብራለን በማለት በጀትን ለታለመለት አላማ በማዋል የተጀመሩ የመሰረተ ልማቶችን በማስቀጠል ማህበረሰቡን ተጠቃሚ ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል።

የ2019 በጀት አመት እቅዱ በማሳካት ውጤት ለማስመዝገብ የሁሉም ባለድርሻ አካላት ርብርብ እንደሚጠይቅና ሁሉም ሰራተኞች በሃላፊነት እና በታማኝነት ስሜት መንቀሳቀስ እንደሚያስፈልግ እና የበጀት አጠቃቀም ብቃት በዋናነት ተነስተው ቀጣይ የገቢ አሰባሰቡን በማጠናከር በቁጥር የተሰጠውን ወደ ሀብት ለመቀየር ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባ አቶ ታጋይ ኤሊያስ አሳስበዋል።

በመጨረሻም የ2019 ዓ/ም እቅድና የ2019 በጀት ረቂቅ የተነሱ አስተያየቶችን እንደግብአት በመውሰድ ማስተካከያ መደረግ እንዳለበት ተገልፆል።

ላለፉት 3 ቀናት ሲካሄድ የቆየው የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም ግምገማና የአመራር ምዘና መድረክ ተጠናቀቀ።በቤንች ሸኮ ዞን ላለፉት ሦስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የመንግስትና የፓርቲ ተግባራት...
01/09/2026

ላለፉት 3 ቀናት ሲካሄድ የቆየው የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም ግምገማና የአመራር ምዘና መድረክ ተጠናቀቀ።

በቤንች ሸኮ ዞን ላለፉት ሦስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የመንግስትና የፓርቲ ተግባራት አፈጻጸም ግምገማና የአመራሩ ምዘና መድረክ ተጠናቋል።

በመድረኩ በበጀት ዓመት የተከናወኑ የልማት ፣ የመልካም አስተዳደር ፣ የአገልግሎት አሰጣጥ ፥ የፓርቲ ኢነሸቲቦች እና ህዝብ ተኮር ማህበራዊ የልማት ስራዎች በጥልቀት ተገምግመዋል።

ከመንግስታዊ ተልዕኮ ባሻገር የፓርቲ ስራዎች ፣ የፓርቲ አደረጃጀቶችን የማጠናከር ስራዎችን ጨምሮ ሌሎች የአመራሩ ተሳትፎ ስራዎችም በጥልቀት የተገመገሙ ናቸው ።

የአጠቃላይ አመራሩ ምዘና የተካሄደ ሲሆን በዚህም የአመራሩ ቁርጠኝነትና ተነሳሽነት ስራዎች ፣ አጠቃላይ የአመራሩ ተግባር አፈጻጸም ውጤታማነት፣ በአመራሩ ዘንድ የታዩ ጉድለቶች እና ተልዕኮን ከማስፈጸም አኳያ አመራሩ የተወጣውን ሚና መሠረት በማድረግ ጥልቅ አጠቃላይ ግምገማ እና ግለ ግምገማ ተካሂዷል።

በግምገማው በ2018 በጀት ዓመት በርካታ ውጤቶች እንደተመዘገቡ ተመላክቷል።

በሂደቱም የመልካም አስተዳደር ችግሮችና ብልሹ አሰራሮችን በተገቢው መንገድ ምላሽ ያልተሰጣቸው ጉዳዮች በጥልቀት እንደተገመገሙ ተጠቁሟል።

በቀጣይም ፓርቲው እንደዚህ ዓይነት ጉዳዮች እንዳይደገሙ ተገቢውን እና ጥብቅ እርምጃ እንደሚወስድ በማጠቃለያው ተመላክቷል።

ለሦስት ተከታታይ ቀናት በተካሄደው የአፈጻጸም ግምገማና በአመራር ምዘና መድረኩ የመንግስትና የፓርቲ ተግባራት በሚገባ ተገምግሞ በተያዘው በጀት ዓመት የመንግስትና የፓርቲ ተግባራትን በተሻለ መልኩ ለማከናወንና ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ውይይት ተደርጎ አቅጣጫም ተቀምጧል።
ዞን መ/ኮ

የ2018 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል ማጠቃለያ ፈተና ውጤት ትንተና ይፋ ሆነ።​ሚዛን- አማን ፣ ነሐሴ 26፣2018 ዓ.ም (ቤሸቴ)፦ በዞኑ የ2018 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል አጠቃላይ የመንግስትና የግል ትም...
01/09/2026

የ2018 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል ማጠቃለያ ፈተና ውጤት ትንተና ይፋ ሆነ።​

ሚዛን- አማን ፣ ነሐሴ 26፣2018 ዓ.ም (ቤሸቴ)፦ በዞኑ የ2018 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል አጠቃላይ የመንግስትና የግል ትምህርት ቤቶች የፈተና ውጤት ትንተና ይፋ ሆኗል።​

የቤንች ሸኮ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ አገኘሁ ወርቁ እንደገለፁት በ222 ትምህርት ቤቶች 8 ሺህ733 ተማሪዎች የ6ኛ ክፍል ማጠቃለያ ፈተና እንደወሰዱ ጠቁመዋል።

በዘንድሮ ዓመት ከተፈተኑት ከአንድ እስከ ሃያ ቶፕ ተማሪዎች 15ቱ ሴት ሲሆኑ 5ቱ ወንዶች ናቸው ብለዋል።

የማለፊያ መቁረጫ ውጤት 40 ከመቶ መሆኑም ተገልጿል።

አጠቃላይ ከተፈተኑት 8ሺ733 በመቁረጫ ነጥብ ያለፉ በቁጥር 5ሺ 790 በመቶኛ 66.3 መሆኑን ጠቁመዋል።

ከ2017 ዓ/ም አፈፃፀም 5.1 ከመቶ ብልጫ መኖሩን ገልፀው በአማካይ 50 እና በላይ ያመጡት 3ሺ 413 ሲሆን ከአምናው አፈፃፀም በ18.8 ከመቶ ከፍ ብሎ ተመዝግቧል ብለዋል።

በዞኑ ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡት 1ኛ. ኑሀሚን ዴቪድ ሴት ተማሪ ከአቡነ ተክለሀይማኖት ት/ቤት 100 ከ100 ፣ 2ኛ. ማስተዋል መላኩ ሴት ተማሪ ፅ/ማርያም ት/ቤት 96.9 ፣ 3ኛ.ፓሮሲያ እስጢፋኖስ ወንድ ተማሪ ከአቡነ ተክለሀይማኖት ት/ቤት 96.1 ፣ 4ኛ.ማረያማዊት መልካሙ ሴት ተማሪ ከአቡነ ተክለሀይማኖት ት/ቤት 95.6 ፣ 5ኛ.ሱመያ ሰይድ ሴት አማን-ብርሃን ት/ቤት 95.6 መሆናቸውም ተጠቁሟል።

የዞኑ ኮሚኒኬሽን ዘግቧል

በወረዳው አፈሳ አለ ተብሎ የተናፈሰው የወሬ መረጃ የተሳሳተና ከእውነት የራቀው መረጃ ነው :-አቶ ደረጀ ባሳበ​ጉራፈረዳ ወረዳ  ወጣቶች በግዴታ እየተወሰዱ ነው የሚሉ ወሬዎች ሙሉ በሙሉ መሰረ...
27/08/2026

በወረዳው አፈሳ አለ ተብሎ የተናፈሰው የወሬ መረጃ የተሳሳተና ከእውነት የራቀው መረጃ ነው :-አቶ ደረጀ ባሳ

በ​ጉራፈረዳ ወረዳ ወጣቶች በግዴታ እየተወሰዱ ነው የሚሉ ወሬዎች ሙሉ በሙሉ መሰረተ ቢስ መሆናቸውን የጉራፈረዳ ወረዳ ሰላም ፀጥታ ምልሻ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ደረጀ ባሳ ተናግረዋል።

​ሰሞኑን በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ እየተዘዋወረ ያለው የወጣቶች አፈሳ አለ የሚለው መረጃ ከእውነት የራቀና ሆን ተብሎ ወረዳውን አለመረጋጋት ውስጥ ለመክተት የሚሰራ የሐሰት ወሬ መሆኑን አቶ ደረጀ ባሳ ገልጸዋል።

​አክለውም አቶ ደረጀ ባሳ የሀገር መከላከያ ዩኒቨርሲቲ እንደማንኛውም ዩኒቨርሲቲዎች ወጣቶች በፍላጎታቸው በተለያዩ የትምህርት መስኮች ገብተው የሚሰለጥኑበትና የሙያ ባለቤት የሚሆኑበት ከፍተኛ የትምህርት ተቋም እንጂ፣ ከህግ ውጭ ሰው ታፍሶ የሚወሰድበት ቦታ አይደለም ብለዋል።

​በወረዳው ፍላጎት ያላቸው ወጣቶች የሀገር መከላከያ ሰራዊት አባል በመሆን ሀገራቸውን እንዲጠብቁና በዘርፉ ሰልጥነው የሙያ ባለቤት እንዲሆኑ እንደ ሀገር በወረደው አቅጣጫ መሰረት ምዝገባዎች ሲካሄዱ መቆየታቸውን አቶ ደረጀ ባሳ ገልፀው ሆኖም ይህን ሰላማዊ የመግቢያ ሂደት እንደ አፈሳ በማስመሰል ማህበራዊ ሚዲያ ላይ ማሰራጨት ተቀባይነት የሌለው ተግባር መሆኑን አብራርተዋል።

​ ማህበረሰቡ በተለይም ወጣቶች ከዚህ መሰረተ ቢስ ወሬ ራሳቸውን አግልለው እንደማንኛውም ጊዜ መደበኛ ስራቸውንና እንቅስቃሴያቸውን በተረጋጋ መልኩ ማከናወን እንዳለባቸው እና ህብረተሰቡ የተሳሳቱ መረጃዎችን በማሰራጨት ፈንታ የጸጥታ አካላት ጋር በመተባበር የወረዳውን ሰላም ዘላቂ እንዲሆን የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያበረክት አቶ ደረጀ ባሳ ጥሪ አቅርበዋል።

Address

Biftu
Mizan Teferi

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Guraferda woreda communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Guraferda woreda communication:

Shortcuts

Share