13/03/2026
ምዕራብ ኦሞ ዞን ፕላንና ልማት መምሪያ
የምህራብ ኦሞ ዞን ፕላንና ልማት መምሪያ በዞኑ ከሚገኙ መምሪዎች አንዱ ሲሆን በሰባት(7) የወረዳ ፕላንና ልማት ጽ/ቤቶች የተዋቀረና በሶስት(3) የከተማ አስተዳደር ፕላንና ልማት ጽ/ቤቶች የተዋቀረ ሲሆን በዞኑ በድምሩ አስር(10) መዋቅሮች ሲኖሩት የፕላን ልማት ጽ/ቤት የተዋቀረባቸው በሰባቱ(7) ወረዳዎች ሲሆን የከተማ አስተዳደር ፕላንና ልማት ጽ/ቤቶች መዋቅር ሲስተካከል እንደሚዋቀሩ ያለዉ መረጃ ያመላክታል፡፡
በዞኑ ያሉ የወረዳ ፕላንና ልማት ጽ/ቤት
በዞኑ ያሉ የከተማ አስተዳደሮች የፕላን ልማት ፅ/ቤት
1. መኤኒት ጎልዲያ ወረዳ ፕላንና ልማት ጽ/ቤት
2. ጋችት ወረዳ ፕላንና ልማት ጽ/ቤት
3. መኤኒት ሻሻ ወረዳ ፕላንና ልማት ጽ/ቤት
4. ጎሪ ጌሻ ወረዳ ፕላንና ልማት ጽ/ቤት
5. ማጂ ወረዳ ፕላንና ልማት ጽ/ቤት
6. ሡሪ ወረዳ ፕላንና ልማት ጽ/ቤት
7. ቤሮ ወረዳ ፕላንና ልማት ጽ/ቤት
1. ባቹማ ከተማ አስተዳደር
2. ጀሙ ከተማ አስተዳደር
3. ማጂ ቱም ከተማ አስተዳደር ናቸው፡፡

አቶ ዘሪሁን ወርቁ
የምህራብ ኦሞ ዞን ፕላንና ልማት መምሪያ ኃላፊ
Background Of West Omo Zone
Location and Area
ምዕራብ ኦሞ ዞን በደ/ምዕራብ ኢትዮጲያ ሕዝቦች ክልላዊ መንግሥት ከሚገኙ ዞኖች በሚያዝያ 23/2011 ዓ.ም በአድስ መልክ መመስረቱ ይታወቃል፡፡ ዞኑ በሀገሪቱ በደቡብ ምዕራብ አቅጣጫ ከአዲስ አበባ 671 ኪ/ሜትርና ከክልሉ ርዕሰ ከተማ ቦንጋ 200 ኪ/ሜ ርቀት ላይ ይገኛል። ዞኑ በሰሜንና በሰሜን ምስራቅ ከከፋ ዞን፣ በሰሜን ምዕራብ ከቤንች ሸኮ ዞን፣ በደቡብ ምሥራቅ ከደቡብ ኦሞ ዞን፣ በደቡብ ምዕራብ ከጋምቤላ ክልልና በደቡብ ከደቡብ ሱዳን ሪፖብሊክ ጋር ይዋሰናል።
ዞኑ 3 ክፍለ ከተማዎችና በ7 ወረዳዎች በ114 ቀበሌ አስተዳደር የተከፋፈለ ሲሆን የቆዳ ስፋቱ 1,458,400 ሄ/ር እንደሚሆንና በ1ስኩዌር ኪሎ ሜትር በአማካይ 20.6 ህዝብ እንደሚኖር ይገመታል።
ዞኑ የሚገኝበት በስተምስራቅ /Latitude/ 6.6384755 እና በስተ ምዕራብ /Longitude/ 35.7817109 ይገኛል፡፡
Population size and distribution
የ1999 ዓ.ም የህዝብና ቤቶች ቆጠራ ውጤትን መሰረት በማድረግና በዞኑ ካሉ ወረዳዎች የህዝብ ቁጥር መረጃ በመሰብሰብ በተገኘው መረጃ በ2017 ዓ.ም የዞኑ ህዝብ ብዛት ወ 163,542 ሴ 174,236 ድ 337,778 በዞን ማዕከል ፣ በከተማ አስተዳደርና በ7ቱ ወረዳዎች የሚገኙ አራቱ /4/ ነባር ብሄረሰቦች ማለትም የመኤኒት፣የዲዚ፣የሱርማና ዚልማሞ ብሔረሰቦችንና በሰፈራ ጣቢያዎች ተካቶ ያሉ የአማራ፤ የከምባታና የሲዳማ ብሔረሰቦችን ያካተተና በተጨማሪም በዞኑ ዉስጥ ባሉ ወረዳ ከተማዎች በንግድና በመንግስታዊ ስራ የተሰማሩ ሌሎች ኢትዮጵያዊ ብሔረሰቦች ይገኛሉ፡፡
በዞኑ ዉስጥ በዋናነት የመኤኒት፣ የዲዚ፣የሱርማና የዚልማሞ ብሔረሰቦች የሚኖሩ ሲሆን ከነባሩ ህዝብ ጋር በኢትዮጵያ ዉስጥ የሚገኙ ሌሎች ብሄር ብሔረሰቦች በአንድነት ተሳስበዉና ተፈቃቅደዉ ተከባብረዉ የሚኖሩበት ዞን ነዉ ፡፡ አብዛኛዉ ህዝብ የሚተዳደረዉ በከፊል አርብቶ አደርነት፤ በግብርና እና በማዕድን ምርት የሚተዳደር ህዝብን ጨምሮ የያዘ ነዉ፡፡
የህዝብ አሰፋፈሩ በመኖሪያ አካባቢ በገጠር 294,179 (87.09%) እና በከተማ 43,599 (12.9