13/06/2026
በቤሮ ወረዳ ከ 210 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ባለፉት 11 ወራት መሰብሰቡን የወረዳው ገቢዎች ጽ/ቤት አስታውቋል ።
ሰኔ 06/2018 ዓ/ም (የደምኢህክመ ገቢዎች ቢሮ )
በምዕራብ ኦሞ ዞን የቤሮ ወረዳ ገቢዎች ጽ/ቤት በበጀት አመቱ ባለፉት 11 ወራት የተከናወኑ የገቢ አሰባሰብ ስራዎች አፈፃፀም እና የቀሪ ወራት የትኩረት አቅጣጫዎች ዙሪያ አስመልክቶ የወረዳው ገቢዎች ጽ/ቤት ኃላፊ መግለጫ ሰጥተዋል ።
የቤሮ ወረዳ ገቢዎች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ በአምላኩ ትዕዛዙ እንደገለፁት በበጀት አመቱ ባለፉት 11 ወራት በመደበኛና ማዘጋጃ ቤት ገቢ ብር 234,463,879 ለመሰበሰብ ታቅዶ የተሰራ ሲሆን ብር 210,727,736 መሰብሰብ የተቻለ ሲሆን የዕቅዱን 90 % ማሳካት እንደተቻለ ገልፀዋል ።
ኃላፊው አያይዘው እንደገለጹት የበጀት አመቱ ዕቅድ በከፍተኛ መጠን ማደጉ ከዕቅድ በላይ እንዳናሳካ ያደረገ ቢሆንም አፈጻጸሙ ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ከ100% በላይ ዕድገት ተመዝግቧል፡፡
ለተመዘገበው ስኬት በሁሉንም ዘርፍ በተደረገው ርብርብ እና ከባለድርሻ አካላቶች ጋር በቅንጅት በመሰራቱ እንደሆነ አቶ በአምላኩ ገልፀዋል ።
በመጨረሻም በቀሪ ወራት በተጀመረው ትኩረት ከፍተኛ ርብርብ በማድረግ የበጀት አመቱን ዕቅድ ለማሳካት እንደሚሰራ ኃላፊው ገልፀዋል ።
ዘገባው የምዕራብ ኦሞ ዞን የመንግስት ኮምንኬሽን ነው