Southwest Revenue Bureau

Southwest Revenue Bureau የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት የገቢዎች ቢሮ ይፋዊ የፌስ ቡክ ገፅ ነዉ፡፡

በቤሮ ወረዳ ከ 210 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ባለፉት 11 ወራት መሰብሰቡን  የወረዳው ገቢዎች ጽ/ቤት አስታውቋል ።  ሰኔ 06/2018 ዓ/ም (የደምኢህክመ ገቢዎች ቢሮ ) በምዕራብ ኦሞ ዞን...
13/06/2026

በቤሮ ወረዳ ከ 210 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ባለፉት 11 ወራት መሰብሰቡን የወረዳው ገቢዎች ጽ/ቤት አስታውቋል ።

ሰኔ 06/2018 ዓ/ም (የደምኢህክመ ገቢዎች ቢሮ )
በምዕራብ ኦሞ ዞን የቤሮ ወረዳ ገቢዎች ጽ/ቤት በበጀት አመቱ ባለፉት 11 ወራት የተከናወኑ የገቢ አሰባሰብ ስራዎች አፈፃፀም እና የቀሪ ወራት የትኩረት አቅጣጫዎች ዙሪያ አስመልክቶ የወረዳው ገቢዎች ጽ/ቤት ኃላፊ መግለጫ ሰጥተዋል ።

የቤሮ ወረዳ ገቢዎች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ በአምላኩ ትዕዛዙ እንደገለፁት በበጀት አመቱ ባለፉት 11 ወራት በመደበኛና ማዘጋጃ ቤት ገቢ ብር 234,463,879 ለመሰበሰብ ታቅዶ የተሰራ ሲሆን ብር 210,727,736 መሰብሰብ የተቻለ ሲሆን የዕቅዱን 90 % ማሳካት እንደተቻለ ገልፀዋል ።

ኃላፊው አያይዘው እንደገለጹት የበጀት አመቱ ዕቅድ በከፍተኛ መጠን ማደጉ ከዕቅድ በላይ እንዳናሳካ ያደረገ ቢሆንም አፈጻጸሙ ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ከ100% በላይ ዕድገት ተመዝግቧል፡፡

ለተመዘገበው ስኬት በሁሉንም ዘርፍ በተደረገው ርብርብ እና ከባለድርሻ አካላቶች ጋር በቅንጅት በመሰራቱ እንደሆነ አቶ በአምላኩ ገልፀዋል ።

በመጨረሻም በቀሪ ወራት በተጀመረው ትኩረት ከፍተኛ ርብርብ በማድረግ የበጀት አመቱን ዕቅድ ለማሳካት እንደሚሰራ ኃላፊው ገልፀዋል ።
ዘገባው የምዕራብ ኦሞ ዞን የመንግስት ኮምንኬሽን ነው

የኤክሳይዝ ታክስ በሚከፈልባቸው ዕቃዎች ላይ ስለሚደረግ ቁጥጥር ምን ያህል ያውቃሉ?ሰኔ 06/2018 (የደምኢህክመ ገቢዎች ቢሮ)የኤክሳይዝ ታክስ በሚከፈልባቸው ዕቃዎች ላይ ቁጥጥር የሚደረገው ...
13/06/2026

የኤክሳይዝ ታክስ በሚከፈልባቸው ዕቃዎች ላይ ስለሚደረግ ቁጥጥር ምን ያህል ያውቃሉ?

ሰኔ 06/2018 (የደምኢህክመ ገቢዎች ቢሮ)

የኤክሳይዝ ታክስ በሚከፈልባቸው ዕቃዎች ላይ ቁጥጥር የሚደረገው

•ፈቃድ በተሰጠው አምራች ፋብሪካ ውስጥ የሚገኙ የኤክሳይዝ ታክስ የሚከፈልባቸው ዕቃዎች በታክስ ባለሥልጣኑ የኤክሳይዝ ታክስ ቁጥጥር ይደረግባቸዋል፡፡

•የኤክሳይዝ ታክስ በሚከፈልባቸው ዕቃዎች ላይ የኤክሳይዝ ታክስ ቁጥጥር የሚደረገው ከሚከተሉት በቀደመው ጊዜ ይሆናል፡፡

ሀ) ፈቃድ በተሰጠው አምራች ፋብሪካ ውስጥ የሚገኙ ዕቃዎች በኢትዮጵያ ውስጥ ጥቅም ላይ እንዲውሉ ከፋብሪካው እስከሚወጡ፣

ለ) ዕቃዎቹ ከኢትዮጵያ ውጪ እስከሚላኩ፣ ወይም

ሐ) ዕቃዎቹ ከአገልግሎት ውጪ እስከሚደረጉ ወይም እስከሚወገዱ ድረስ፣

•ዕቃዎች በኤክሳይዝ ታክስ ቁጥጥር ስር እስካሉ ድረስ፣

ሀ) በታክስ ባለሥልጣኑ ሥልጣን የተሰጠው የባለሥልጣኑ ሠራተኛ በማናቸውም ጊዜ ዕቃዎቹን መመርመር ይችላል፣

ለ) በታክሱ ባለሥልጣን ከተፈቀደለት ሰው በስተቀር ማናቸውም ሰው ዕቃዎቹን ከፋብሪካ ማውጣት ወይም በማናቸውም ሌላ መንገድ ዕቃዎቹን የሚመለከት ማናቸውንም ተግባር መፈፀም አይችልም፡፡

ዕቃዎች በኤክሳይዝ ታክስ ቁጥጥር ስር ባሉበት ጊዜ የታክሱ ባለሥልጣን የዕቃው ባለቤት ዕቃዎቹን ለታክሱ ባለሥልጣን እንዲያስረክብ ሊጠይቅ ይችላል፡፡ የታክሱ ባለሥልጣን ዕቃዎቹን ከተረከበ በኋላ ዕቃዎቹ በታክሱ ባለሥልጣን በሚሰጥ መመሪያ መሠረት በባለቤቱ ወጪ ሊሸጡ ወይም ከአገልግሎት ውጪ እንዲሆኑ ሊደረግ ወይም ሊወገዱ ይችላል፡፡

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ  ሰኔ 5/2018 ዓ.ም (የደምኢህክመ ገቢዎች ቢሮ)የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን ...
12/06/2026

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

ሰኔ 5/2018 ዓ.ም (የደምኢህክመ ገቢዎች ቢሮ)

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018 ዓ.ም ባደረገው ክትትል 969.4 ሚሊዮን ብር የገቢ የኮንትሮባንድ እቃዎች እና 20.5 ሚሊዮን ብር የወጭ፤ በድምሩ 989.99 ሚሊዮን ብር ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ እቃዎች በተለያዩ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች ተይዘዋል፡፡

በቁጥጥር ስር ከዋሉት የኮንትሮባንድ እቃዎች መካከል አዳዲስ እና ልባሽ ጨርቆች፣ ኤሌክትሮኒክስ፣ የግንባታ እቃዎች፣ ቡና፣ ጥራጥሬ፣ የተሽከርካሪ መለዋወጫ፣ የመዋቢያ እቃዎች፣ ጫት፣ አደንዛዥ እጾች፣ መድኃኒት፣ ማዕድናት፣ የቁም እንስሳት እና የውጭ ሀገር ገንዘቦች ይገኙበታል፡፡

በተጠቀሰው የጊዜ ገደብ የገቢ እና የወጭ ኮንትሮባንድን በመቆጣጠር አዋሽ፣ ጅግጅጋ እና ሞያሌ ጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች ቀዳሚውን ስፍራ ሲይዙ በቅደም ተከተላቸውም 675 ሚሊዮን፣ 102 ሚሊዮን እና 78 ሚሊዮን ብር ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ እቃዎችን መያዝ ችለዋል፡፡

የኮንትሮባንድ ዕቃዎቹ በጉምሩክ ኮሚሽን ሰራተኞች፣ በፌደራል ፖሊስ፣ በክልል ፖሊስ አባላትና ህብረተሰቡ ባደረጉት የጋራ ጥረት በፍተሻ፣ በጥቆማ እና በበረራ የተያዙ ሲሆን የኮንትሮባንድ እቃዎቹን ሲያዘዋውሩ የተገኙ 16 ተጠርጣሪዎች እና 21 ተሽከርካሪዎችም በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡

የጉምሩክ ኮሚሽን በዚህ የህግ ማስከበር ስራ ላይ ለተሳተፉ የኮሚሽኑ ሰራተኞች እና አመራሮች፣ የክልልና የፌደራል ፖሊስ አባላት እንዲሁም ለመላው ህዝባችን ምስጋናውን ያደርሳል፡፡

የኮንትሮባንድ እና ህገወጥ ንግድ የአፈጻጸም ስልቱ ተለዋዋጭ በመሆኑ ድርጊቱን ለመግታትና በሀገር ኢኮኖሚ የሚያሳድረውን ተጽእኖ ለመከላከል ጉምሩክ ኮሚሽን ብቻ የሚያደርገው እንቅስቃሴ በቂ ባለመሆኑ ሁሉም ባላድርሻ አካላትና ህብረተሰቡ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ የጉምሩክ ኮሚሽን ጥሪውን ያቀርባል፡፡

ዘገባው ጉምሩክ ኮሚሽን ነው።

በበጀት አመቱ 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8.7 ቢሊየን ዶላር ገቢ ተገኘሰኔ 04/2018 (የደምኢህክመ ገቢዎች ቢሮ)በ2018 በጀት ዓመት 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8.7 ቢሊየን ዶላር ገቢ መገኘቱ...
11/06/2026

በበጀት አመቱ 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8.7 ቢሊየን ዶላር ገቢ ተገኘ

ሰኔ 04/2018 (የደምኢህክመ ገቢዎች ቢሮ)

በ2018 በጀት ዓመት 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8.7 ቢሊየን ዶላር ገቢ መገኘቱን የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሺዴ ገለጹ።

ከባለፈው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ38.9 በመቶ እድገት ማሳየቱንም አክለው ተናግረዋል።

ይህ የተገለጸው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሔደው 25ኛ መደበኛ ስብሰባ የፌዴራል መንግስት የ2019 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት ለምክር ቤቱ ቀርቦ ውይይት በተደረገበት ወቅት ነው።

የመካከለኛው ምስራቅ ቀውስ ጫናዎችን በመቋቋም የተገኘው 8.7 ቢሊየን ዶላር ገቢ የበጀት አመቱ ሲጠናቀቅ 10.5 ቢሊየን ዶላር እንደሚመዘገብ መገመቱን ሚኒስትሩ ለምክር ቤቱ ባቀረቡት የበጀት መግለጫ ገልጸዋል፡፡

በተጨማሪም የፌዴራል መንግስት የ2019 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት ውሳኔ ቁጥር 24/2018 ሆኖ ለፕላን በጀት እና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ መመራቱን የምክር ቤቱ መረጃ ያመላክታል፡፡
ዘገባው የAMN ነው

የማህበረሰቡን መልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስ ገቢን አሟጦ መሰብሰብ ወሳኝ መሆኑ ተገለፀ።ሰኔ 04/2018 (የደምኢህክመ ገቢዎች ቢሮ)የዋቻ ከተማ አስ/ር ገቢ ፅ/ቤት ከባለድርሻ አካላ...
11/06/2026

የማህበረሰቡን መልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስ ገቢን አሟጦ መሰብሰብ ወሳኝ መሆኑ ተገለፀ።

ሰኔ 04/2018 (የደምኢህክመ ገቢዎች ቢሮ)

የዋቻ ከተማ አስ/ር ገቢ ፅ/ቤት ከባለድርሻ አካላት ጋር የ11 ወራት ገቢ አፈጻጸም ግምገማና የቀሪ ቀናት ስራ አቅጣጫ ላይ ተወያይቷል።

ወይይቱን የመሩት የከተማ አስ/ር ምክ/ከንቲባና ገቢ ፅ/ቤት ሃላፊ አቶ ማቲዎስ ጋኖ የ11 ወራት አፈጻጸም ያቀረቡ ስሆን የዓመቱ ገቢ ዕቅድ 180,026,640ብር ክንውን በጥቅሉ 133,544,728ብር 74.2% መሰብሰቡን ገልፀው በመደበኛ ዕቅድ 141,656,345 ክንውን 108,006,340ብር 76.3% በማዘጋጃ ቤታዊ ገቢ ዕቅድ 38,370,302 ክንውን 25,538,388ብር 66.6% መከናወኑን አብራርተዋል።

ከአምና አፈጻጸም አንፃር ከ51 ሚሊየን ብር በላይ ብልጫ ያለው ቢሆንም ከበጀት አመት አፈጻጸም አንጻር ቀሪ የገቢ ምንጮችን ለይቶ አሟጦ መሰብሰብ የግድ መሆኑን ጠቅሰው ማህበረሰቡ የሚያነሳውን የተለያዩ መሠረተ ልማት ጥያቄዎችን መመለስ ይቻል ዘንድ ገቢን አሟጦ መሰብሰብ ወሳኝ እንደሆነ ገልፀዋል።

በተያያዘም ትኩረት መደረግ ያለባቸው ጉዳዮች የደረሰኝ አቆራረጥ ክትትል ችግር፣ በየሩብ ዓመት መሰብሰብ ያለበትን 1/4ኛን ገቢ አሟጦ መሰብስብ፣ የግል ድርጅቶች ስራ ግብር ክትትል ማድረግ፣ የጣሪያና ግድግዳ፣ የሊዝ ውዝፍ፣ መሬት መጠቀሚያና ሌሎች ውዝፍ ዕዳዎችን አሟጦ መሰብሰብ፣ የጥረት ገቢን ቀንና ማታ በተጠናከረ ሁኔታ ተቀናጅቶ በመስራት በቀሪ አጭር ቀናት ዕቅድ ለማሳካት መረባረብ ያስፈልጋል ብለዋል።

በስተመጨረሻም የቀጣይ ቀናት ስራ ዕቅድና የስራ አቅጣጫ በዝርዝር ቀርቦ ውይይቱ ተቋጭቷል።

በመድረኩም የብል/ፓር/አደረጃጀት ዘርፍ ሃላፊ አቶ ሰብለስላሴ ሃ/ማርያምን ጨምሮ ከንቲባ ጽ/ቤት ሃላፊ፣ የእንደ/ንግ/ሃላፊዎችና ባለሙያዎች፣ማዘጋጃ ስራ አስኪያጅና ማኔጅመንት፣የገቢ ባለሙያዎች፣ትራስፖርት ማኔጅመንት፣ግብርና ማኔጅመንት ፋይ/ስ ማኔጅመንት የመድረኩ ተሳታፊ ናቸው።

መረጃው የዋቻ ከተማ የመንግስት ኮምንኬሽን ጽ/ቤቱ ነው !

የመሠረተ ልማት ጥያቄዎችን በዘላቂነት ለመመለስ ገቢን በአግባቡ መሰብሰብ ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ።ሰኔ ዐ3/2018 (የደምኢህክመ ገቢዎች ቢሮ)የአዉራዳ ከተማ አስ/ር ገቢዎች ዩኒት ባለፉት 11 ወ...
10/06/2026

የመሠረተ ልማት ጥያቄዎችን በዘላቂነት ለመመለስ ገቢን በአግባቡ መሰብሰብ ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ።

ሰኔ ዐ3/2018 (የደምኢህክመ ገቢዎች ቢሮ)

የአዉራዳ ከተማ አስ/ር ገቢዎች ዩኒት ባለፉት 11 ወራት በተከናወኑ የገቢ አሰባሰብ ተግባራትና በቀጣይ ቀሪ ግዜያት በሚተገበሩ የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ሰፊ ውይይት አካሂዷል።

በመድረኩ ላይ የተገኙት የአዉራዳ ከተማ አስ/ር ከንቲባ አቶ ታረቀኝ ኃይሌ የመሠረተ ልማት ጥያቄዎችን በዘላቂነት ለመመለስ ገቢን በአግባቡ መሰብሰብ ወሳኝ መሆኑን ገልጿል።

በከተማዉ የተለያዩ የመሠረተ ልማት ጥያቄዎች መኖራቸውን አንስተው የሕብረተሰቡን ጥያቄዎች በአግባቡ ለመመለስ የገቢ አሰባሰብ ላይ ሁሉም አካላት በትኩረት መሥራት እንዳለባቸው አሳስበዋል።

ቀጣይ ቅንጅታዊ አሰራርን በማጠናከር በዘላቂነት የህዝባችንን ግብር የመክፈል ባህልን በማሳደግ በትኩረት መሰራት ያስፈልጋል ብለዋል።

በተያዘው ዕቅድ መሠረት በቀሪዎቹ ቀናት ውስጥ አፈጻጸሙን ሙሉ በሙሉ ማሳካት እንደሚገባም አሳስበዋል።

የከተማው አስ/ር የኢኮኖሚ ክላስተር ኃላፊ አቶ ደስታ ፍሰሃ በበጀት ዓመቱ የ11 ወራት አፈጻጸም ሪፖርት ያቀረቡ ስሆን የተለያዩ የገቢ መሰብሰቢያ ምንጮችን በመለየትና በአግባቡ በመጠቀም ከህብረተሰቡ የሚቀርቡ የልማት ጥያቄዎችን መመለስ መቻል አለብን ብለዋል።

የደረሰኝ ክትትልን ማጥበቅና ሕገ-ወጥ የንግድ እንቅስቃሴን መከላከል ላይ በትኩረት መሥራት እንደሚገባ አስረድተዋል።

የልማት ስራዎችን በዘላቂነት ለማስቀጠል የገቢ አቅምን ማሳደግ አማራጭ የሌለው ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል።

ጥንካሬዎችን በበለጠ በማስቀጠል ጉድለቶችን የዕቅዱ አካል በማድረግ በትኩረት እንደሚሰሩም አንስተዋል።

የመድረኩ ተሳታፊዎች በበኩላቸው የህዝቡን የልማት ፍላጎት ለማሟላትና የመንግስትን ግዴታ ወጪዎችን ለመሸፈን የሚጠበቀውን ገቢ ለመሰብሰብ ሚናቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል።

በመድረኩ የከተማ አስ/ር አስተባባሪና አመራሮች ፥የዞን ገቢ መምሪያ ደጋፊ ባለሙያዎች፣የቀጠና አመራሮች እና የዘርፉ ባለሙያዎች ተገኝተዋል።

ዘገባው የአዉራዳ ከተማ የመንግስት ኮምንኬሽን ነው

አዲሱ የግብር ከፋዮች ምደባ በአዲሱ በጀት ዓመት መተግበር ይጀምራልሰኔ 03/2018 (የደምኢህክመ ገቢዎች ቢሮ)አዲሱ የግብር ከፋዮች ምደባ ከአዲሱ በጀት ዓመት ጀምሮ ተግባራዊ ይደረጋል አለ ...
10/06/2026

አዲሱ የግብር ከፋዮች ምደባ በአዲሱ በጀት ዓመት መተግበር ይጀምራል

ሰኔ 03/2018 (የደምኢህክመ ገቢዎች ቢሮ)

አዲሱ የግብር ከፋዮች ምደባ ከአዲሱ በጀት ዓመት ጀምሮ ተግባራዊ ይደረጋል አለ የገቢዎች ሚኒስቴር፡፡

የ2019 በጀት ዓመት የታክስ ከፋዮች የደረጃ ምደባ ኮሚቴ ያከናወናቸውን ተግባራት አስመልክቶ ሪፖርት አቅርቧል፡፡

የገቢዎች ሚኒስትር ዓይናለም ንጉሴ በዚህ ወቅት እንዳሉት ÷ አዲሱ ምደባ ግብር ከፋዮች ተገቢውን አገልግሎት እንዲያገኙ ለማድረግ ያለመ ነው፡፡

የሚኒስቴሩን ተደራሽነት ለማጠናከር እንዲሁም የግብር ከፋዮችን አደረጃጀት ለማስፋት እንደሚያስችልም አመልክተዋል፡፡

የጋራ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የጎላ ሚና እንደሚኖረው ጠቁመው ÷ለተግባራዊነቱ የሚመለከታቸው አካላት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል፡፡

ምደባው ዓለም አቀፋዊ ተሞክሮዎችን መሠረት አድርጎ የተከናወነ ሲሆን÷ ለግብር ከፋዮች ተገቢውን አገልግሎት በመስጠት የሚሰበሰበውን ገቢ ለማሳደግ ጉልህ ሚና እንደሚኖረው ተጠቁሟል፡፡

አዲሱ የግብር ከፋዮች ምደባ ከአዲሱ በጀት ዓመት ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚደረግም ሚኒስቴሩ ለፋና ዲጂታል ገልጿል፡፡

ኤፍ ኤም ሲ

በግብር በኩል ያለብንን ሀገራዊ ኃላፊነት ለመወጣት ተዘጋጅተናል፦የሚዛን አማን ነዋሪዎችበሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር ከደረጃ “ሀ” ግብር ከፋዮችና ከሂሳብ አዋቂዎች ጋር በ2018/19 በጀት ...
10/06/2026

በግብር በኩል ያለብንን ሀገራዊ ኃላፊነት ለመወጣት ተዘጋጅተናል፦የሚዛን አማን ነዋሪዎች

በሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር ከደረጃ “ሀ” ግብር ከፋዮችና ከሂሳብ አዋቂዎች ጋር በ2018/19 በጀት ዓመት የሂሳብ መዝገብ አያያዝና አቀራረብ ዙሪያ ያተኮረ የጋራ ውይይት ተካሂዷል።

በውይይቱ የተሳተፉት አቶ አብዱ አገኘው፣ አቶ አጥናፉ ግርሻው እና አቶ ኢያሱ ዳውሻብ እንደገለጹት፣ በየአካባቢው የሚገነቡ መንገዶች፣ ትምህርት ቤቶች፣ የጤና ተቋማትና ሌሎች መሠረተ ልማቶች በዜጎች ከሚከፈለው ግብር የሚተገበሩ በመሆናቸው፣ ግብርን በወቅቱ መክፈል ለሀገር ልማት የማይተካ ሚና እንዳለው ገልጸዋል።

ተሳታፊዎቹ የሚከፍሉት ግብር በቀጥታ ወደ ልማት እንደሚመለስ ጠቅሰው፣ ከተያዘው ጊዜ ቀድመው ግብራቸውን በመክፈል የዜግነት ግዴታቸውን እየተወጡ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በተያዘው በጀት ዓመት በሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር ለመጀመሪያ ጊዜ ከ1 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን መስማታቸው እንዳስደሰታቸው የገለጹት ተሳታፊዎቹ፣ ወደፊትም በግብር በኩል ያለባቸውን ሀገራዊ ኃላፊነት በተሟላ ሁኔታ ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።

በከተማ አስተዳደሩ የግብር ሕግ ማስከበር ዳይሬክቶሬት ዳይረክተር አቶ አየነው አሽቴ በበኩላቸው፣ ፍትሃዊ የግብር አሰባሰብ ሥርዓት እንዲጠናከርና ከግብር ከፋዮች የሚነሱ ቅሬታዎች በአግባቡ እንዲፈቱ በትኩረት እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል።

ከነጋዴዎች የሂሳብ አመዘጋገብ ጋር ተያይዘው የሚታዩ ችግሮችን ለመቅረፍም ተገቢ የማሻሻያ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን አስረድተዋል።

የሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና የገቢዎች ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ረዳት ፕሮፌሰር ታገል ወንድሙ በበኩላቸው፣ መንግሥት የሚሰበስበው ግብር ለልማት፣ ለሰላምና ደኅንነት እንዲሁም ለመሠረታዊ የሕዝብ አገልግሎቶች የሚውል መሆኑን ገልጸዋል።

በከተማው በግብር አሰባሰብ ዘርፍ ለተገኘው ከፍተኛ ስኬት የሚዛን አማን ነዋሪዎችን ያመሰገኑት ረዳት ፕሮፌሰር ታገል፣ “ግብር መክፈል የዜግነት ግዴታ ነው” በማለት ማህበረሰቡ የሚጠበቅበትን ግብር በወቅቱ በመክፈል ሀገራዊ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።

በ2018/19 በጀት ዓመት የሂሳብ መዝገብ አያያዝና አቀራረብ ዙሪያ በቀረበው የመወያያ ሰነድ ላይም ተሳታፊዎች ጥልቅ ውይይት በማድረግ ቀጣይ የሥራ አቅጣጫዎችም ተቀምጠዋል።
Hገባው የቤንች ሸኮ ዞን የመንግስት ኮምንኬሽን ነው

7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ በስኬት መጠናቀቁን ተከትሎ በሚዛን አማን ከተማ ዘላቂ መሰረተ ልማቶችን ተደራሽ ለማድረግና የታማኝ ግብር ከፋዮችን ሚና ለማሳደግ ያለመ አዲስ የምክክርና የስልጠና...
10/06/2026

7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ በስኬት መጠናቀቁን ተከትሎ በሚዛን አማን ከተማ ዘላቂ መሰረተ ልማቶችን ተደራሽ ለማድረግና የታማኝ ግብር ከፋዮችን ሚና ለማሳደግ ያለመ አዲስ የምክክርና የስልጠና መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።

የሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ጽህፈት ቤት ከደረጃ “ሀ” ግብር ከፋዮች እና ከሂሳብ አዋቂዎች ጋር በበጀት ዓመቱ የሂሳብ መዝገብ አቀራረብና ተያያዥ አሰራሮች ላይ ያተኮረ የጋራ የምክክርና የስልጠና መድረክ ማካሄድ ጀምሯል።

​መድረኩን በንግግር የከፈቱት የከተማ አስተዳደሩ ብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ኃላፊና ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ተስፋዬ ጊስካር ወቅቱ 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በስኬት በተጠናቀቀበት ማግስት የተዘጋጀ በመሆኑ መድረኩን ልዩ እንደሚያደርገው ገልጸዋል።

ከተማዋ አሁን ላይ ለደረሰችበት የልማትና የዕድገት ደረጃ የግብር ከፋዩ ማህበረሰብ ያበረከተው አስተዋፅኦ ከፍተኛ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ተስፋዬ በቀጣይም የንፁህ መጠጥ ውሃ፣ የመብራትና ሌሎችንም ዘርፈ-ብዙ የመሰረተ ልማት ፍላጎቶችን ተደራሽ ለማድረግ ግብርን በታማኝነትና በወቅቱ መክፈል እንደሚገባ አሳስበዋል።

​የከተማ አስተዳደሩ ምክትል ከንቲባና የገቢዎች ጽህፈት ቤት ኃላፊ ረዳት ፕሮፌሰር ታገል ወንድሙ በበኩላቸው ከተማዋ ሚዛን አማን በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ ከ1 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ መቻሏን ይፋ አድርገዋል።

ይህ የተሰበሰበው ገቢም በከተማዋ የተጀመሩ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎችን በስኬት ለማከናወን ትልቅ አቅምና የገንዘብ ጉልበት መፍጠሩን አብራርተዋል።

​የውይይት መድረኩ ​ኢኮኖሚው ከሚያመነጨው ሀብት ጋር የተመጣጠነ ተገቢውን ግብር በወቅቱ በመሰብሰብ ለከተማዋ ዘላቂ ልማት ማዋል፣​የግብር አሰባሰቡን ስርዓት ፍትሃዊ በሆነ መንገድ የጎንዮሽ አዳዲስ ግብር ከፋዮችን ወደ ስርዓቱ ማስገባት፣​ወደ ጽህፈት ቤቱ የሚቀርቡ የሂሳብ መዛግብት በሙሉ በአገሪቱ ስራ ላይ ባሉ ህጎች፣ ደንቦችና መመሪያዎች ላይ ብቻ የተመሰረቱ እንዲሆኑ ማስቻል እንደሆነ ተነግራል።

​በመድረኩ ላይ የስልጠና ሰነድ ያቀረቡት የገቢዎች ጽህፈት ቤት የግብር ህግ ማስከበር ዳይሬክቶሬት አቶ አየነው እሸቴ እንደገለጹት ግብር ከፋዮች ባላቸው ትክክለኛ የንግድ እንቅስቃሴ ልክ ፍትሃዊ ግብር እንዲከፍሉ በማድረግ፣ ራሳቸውን ካልተገባ አስተዳደራዊ ቅጣትና ወለድ እንዲጠብቁ ግንዛቤ መፍጠር ዋነኛው ግብ እንደሆነ ጠቅሰዋል።

በተጨማሪም በደረሰኝ አሰጣጥ፣ በሂሳብ ሰነድ አያያዝና በመዝገብ አቀራረብ ላይ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን ከከፍተኛ ግብር ከፋዮች ጋር በጋራ በመገምገም ዘላቂ መፍትሔ ማስቀመጥ እና በቀጣይ ዓመት የተሻለ አፈፃፀም ማስመዝገብ የስልጠናው ውጤት እንደሚሆን ጠቁመዋል።

​በዚሁ የምክክር መድረክ ላይ የከተማዋ ከፍተኛ የደረጃ "ሀ" ግብር ከፋዮች፣ የንግዱ ማህበረሰብ ተወካዮች እና የሂሳብ አዋቂዎች በንቃት እየተሳተፉ ሲሆን፤ በሂሳብ አቀራረብና በግብር አሰባሰብ ሂደት ላይ ባሉ ጠንካራ ጎኖችና መስተካከል በሚገባቸው ጉድለቶች ዙሪያ ሰፊ ውይይት እየተደረገበት ይገኛል።
ዘገባው የቤንች ሸኮ ዞን የመንግስት ኮምንኬሽን

በ2019 በጀት ዓመት የገቢ አሰባሰብ መሠረቶችን በማስፋት የህዝቡን የልማት ጥያቄ በየደረጃው ምላሽ የመስጠት ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥላል - ወ/ሮ ህይወት አሰግድሰኔ 03/2018 (የደምኢህክመ...
10/06/2026

በ2019 በጀት ዓመት የገቢ አሰባሰብ መሠረቶችን በማስፋት የህዝቡን የልማት ጥያቄ በየደረጃው ምላሽ የመስጠት ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥላል - ወ/ሮ ህይወት አሰግድ

ሰኔ 03/2018 (የደምኢህክመ ገቢዎች ቢሮ)

ቢሮው በ2019 በጀት ዓመት የገቢ አሰባሰብ እቅድ ዙሪያ አየመከረ ነው።

የደምኢህክመ ገቢዎች ቢሮ ከክልሉ ምስረታ ማግስት ጀምሮ ለክልሉ ሁለንተናዊ ልማትና የህዝብ ተጠቃሚነት በየደረጃው ለማረጋገጥ ይቻል ዘንድ ለልማት መሠረት የሚሆነውን የፋይናንስ ወረት ከግብርና ታክስ እንዲገኝ ከፍተኛ ተጨባጭ ስራ ሲያከናውን መቆዬቱ ይታወቃል።

ይህ ተግባር በ2019 በጀት ዓመት ተጠናክሮ ይቀጥል ዘንድ በበጀት ዓመቱ ገቢ ዕቅድ ዙሪያ የቢሮው አመራሮች የፋይናንስ ቢሮ አመራሮችና የፕላን ልማት ቢሮና የገቢዎች ቢሮ ከፍተኛ ባለሙያዎች እየመከሩ ይገኛል።

የቢሮው ኃላፊ ወ/ሮ ህይወት አሰግድ ቢሮው በ2019 በጀት በክልሉ ፍትሃዊ የገቢ አሰባሰብ ሂደት በላቀ አግባብ በማስፈን በፈቃጀኝነት ላይ የተመሠረተ የገቢ አሰባሰብ ስርዓት በመገንባት ለክልሉ ህዝብ ሁለንተናዊ ልማት የሚውል ገቢን በየደረጃው በመሰብሰብ ለህዝብ ልማት የማዋል ተግባር ተጠናክሮ የሚሰራበት ይሆናል ብለዋል።

አቶ ጅብሪል አባጊሳ የቢሮው የልማት ዕቅድ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የ2019 በጀት የገቢ መነሻ ዕቅድ ሰነድ እንዲሁም አቶ መለሰ ኡሮ የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊና የመንግስት ፋይናንስ ዘርፍ ኃላፊ የገቢ ድርሻ በየበጀት ዓመቱ ያለውን ድርሻ ላይ ያተኮረ ሰነድ አቅርበው ውይይት ይደረግበታል።

Address

Mizan Teferi

Telephone

+251900452940

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Southwest Revenue Bureau posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Southwest Revenue Bureau:

Share