Debub Bench Woreda Education Office

Debub Bench Woreda Education Office Debub Bench Woreda Education Office (የደቡብ ቤንች ወረዳ ትምህርት ጽህፈት ?

07/10/2025

የሪሜዲያል መግቢያ ነጥብ ይፋ ሆነ‼️

ትምህርት ሚኒስቴር በ2018 የትምህርት ዘመን የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎችን በተፈጥሮ እና ማህበራዊ ሳይንስ ትምህርት መስኮች ከ49.5% በታች ያስመዘገቡ ነገር ግን ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን የሚያሟሉ ተማሪዎች የRemedial ፕሮግራም ተጠቃሚ መሆናቸውን አሳውቋል።

1. በሁሉም አማራጮች (በግል እና በመንግስት ተቋማት) የ Remedial ፕሮግራም ለመከታተል ተማሪዎች እንደተፈተኑት የትምህርት አይነት ብዛት 33% ከመቶ እና ከዚያ የተቆረጠ መሆኑን።

2. ከላይ በተራ ቁጥር 1 የተገለጸው እንደተጠበቀ ሆኖ በመንግስት ተቋማት (ወጪያቸው በመንግስት ተሸፍኖ) የ Remedial ፕሮግራም የሚከታተሉ ተማሪዎች የመቁረጫ ነጥቡን ያሟሉ ብቻ ይሆናሉ።

የመቁረጫ ነጥብ ፦

➡️ የተፈጥሮ እና የማህበራዊ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች 216

➡️ የተፈጥሮ እና የማህበራዊ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች 204

➡️ ታዳጊ ክልል እና አርብቶ አደር አካባቢ የተፈጥሮ እና ማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ለሁለቱም ጾታ 198

➡️ የማህበራዊ እና የተፈጥሮ ሳይንስ መስማት ለተሳናቸው ተማሪዎች ለሁለቱም ጾታ 198

➡️ ማህበራዊ እና የተፈጥሮ ሳይንስ ዓይነስውራን ተማሪዎች ለሁለቱም ጾታ 165
https://t.me/+uXs4lxNd76QyMThk

01/10/2025

የተሻሻለው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መግቢያ ውጤት…

አዲስ አበባ፣ መስከረም 21፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ትምህርት ሚኒስቴር የ2017 ዓ.ም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መግቢያ ውጤትን ከ300 ወደ 297 ዝቅ አድርጓል፡፡

ሚኒስቴሩ እንደገለጸው ÷ የትምህርትና ስልጠና ፖሊሲ ተማሪዎች ወደቀጣይ የትምህርት ደረጃ ለመዛወር 50 በመቶና ከዚያ በላይ ማምጣት እንዳለባቸው ይደነግጋል።

በዚህ መሰረትም በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና አማካይ ውጤታቸው 49 ነጥብ 50 እስከ 49 ነጥብ 99 በመቶ ያመጡ ተማሪዎች ወደ 50 በመቶ እንዲጠጋጋ መወሰኑን አመልክቷል፡፡

ውሳኔውን ተከትሎም 49 ነጥብ 5 እና በላይ አማካይ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች ዝቅተኛውን 50 በመቶ የማለፊያ ነጥብ እንዳሟሉ ተደርጎ ይወሰዳል፡፡

ስለሆነም 49 ነጥብ 5 እና በላይ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመግባት መማር እንደሚችሉ ሚኒስቴሩ አረጋግጧል፡፡

በመሳፍንት እያዩ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/
Facebook FBC (Fana Broadcasting Corporate S.C.)
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/
Facebook WMCC
TikTok www.tiktok.com/
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/

በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

22/09/2025

የትምህርት ሚኒስቴር መልዕክት!...

በ2017 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ የማለፊያ ውጤት ላመጣችሁ ተማሪዎች በሙሉ፤

በ2017 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ የዩኒቨርስቲ መግቢያ ውጤት ያመጣችሁና ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በወጪ መጋራት (ስኮላርሽፕ) ለመማር ፍላጎት ያላችሁ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫችሁን በየትምህርት ቤታችሁ በተወከሉ መምህራን በኩል እስከ መስከረም 14/2018 ዓ.ም ድረስ ማስተካከል የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

ማሳሰቢያ፡-

1. የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ከ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ጀምሮ በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ተማሪዎችን ስሚቀበል ምርጫችሁ ውስጥ ማካተት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

2.አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ እና አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች ምርጫ ውስጥ የማይካተቱ መሆኑ እናሳውቃለን።

21/09/2025
13/09/2025

መስከረም 03፣2018ዓም
ልዩ የስኮላርሺፕ እድል ለመምህራን ትምህርት!

አንጋፋው እና ስመጥሩ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በትምህርት ዘርፍ የተጀመረውን የትምህርት ጥራት እና ተገቢነት ለማረጋገጥ የሚሰራውን ስራ ለመደገፍ እንደ ወትሮው ሀገራዊ ሀላፊነቱን በመወጣት ላይ ይገኛል። ከዚሁ ጋር በተያየዘ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ2018 የትምህርት ዘመን በመጀመሪያ ዲግሪ ልዩ የስኮላርሽፕ እድል አዘጋጅቷል።

የስኮላርሺፑ ተጠቃሚ ሁሉንም መመዘኛ ያሟሉ እና ዩኒቨርሲቲው ያዘጋጀውን የመግቢያ ፈተና በብቃት ያለፉ መሆን ይጠበቅባቸዋል።

የዚህ ስኮላርሺፕ ተጠቃሚዎች

- በተፈጥሮ እና ኮምፕዩቴሽናል ሳይንስ የትምህርት መስክ በፊዚክስ ፣ በኬምስትሪ ፣ በባዮሎጂ እና በሂሳብ እንዲሁም
- በማህበራዊ ሳይንስ የትምህርት መስክ ፤ በእንግሊዘኛ ፣ በኢኮኖሚክስ ፣ በታሪክ፣ በጂኦግራፊ እና በሌሎችም የመምህርነት ትምህርት የሚከታተሉ ይሆናሉ።

የዚህ ስኮላርሽፕ ተጠቃሚዎች

- ሙሉ ነፃ የትምህርት እድል
- መጠነኛ የኪስ ገንዘብ
- ከአጋር ተቋማት ጋር በሚኖር ትብብር ተጨማሪ የስልጠና እድሎችን የሚያገኙ ይሆናል።

በመሆኑም የዚህ ልዩ እድል ተጠቃሚ መሆን የሚፈልጉና ከምርቃት በኋላ በመምህርነት ለማገልገል የምትሹ ሁሉ ከቅበላ በኋላ ዉል ፈርማችሁ ትምህርታችሁን መከታተል የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን::

#አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፣የተፅዕኖ ፈጣሪዎች ቤት
# አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ይማሩ : ህልሞን ያሳኩ

13/09/2025
08/08/2025

ማስታወቂያ

ትምህርት ሚኒስቴር ባስገነባቸው ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች በ2017 የትምህርት ዘመን 8ኛ ክፍልን ካጠናቀቁ ተማሪዎች መካከል አወዳድሮ ማስተማር ይፈልጋል። በመሆኑም መስፈርቱን የምታሟሉ ተማሪዎች ከነሐሴ 05/2017 እስከ ነሐሴ 15/2017 ድረስ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን ለመመዝገን ይህንን ሊንክ መጠቀም ትችላላችሁ።
https://sbs.moe.gov.et/apply

Address

Debrework(ደብረወርቅ )
Mizan Teferi

Telephone

+251953676949

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Debub Bench Woreda Education Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share