21/08/2026
ከመንግስት ካዝና ሊወጣ የሚገባውን 25,361, 824 ብር በላይ ማትረፍ መቻሉን ተገለጸ
በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር ስር በወጣቶች እና ሴቶች ክንፍ አስተባባሪነት የተከናወኑ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባራት አፈፃፀም ግምገማ ተካሄደ
በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር ስር የሰላም ሚኒስቴር ከቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ ወጣቶች እና ሴቶች ክንፍ ጋር በመቀናጀት ያከናወናቸው የ2018/19 ዓ.ም የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባራት ግምገማ ተካሄዷል።
በግምገማ መድረኩ ላይ የተገኙት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የወጣቶች ክንፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ወጣት ሰይድ ኢብራሂም የቤንች ሸኮ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ሚዲያ እና ኮሚዩኒኬሽን ዘርፍ ኃላፊ አቶ ተስፋዬ ዶሻ በጋራ በመሆን መድረኩን መርተውታል::
የበጎ ፈቃድ አገልግሎቱ የአቅመ ደካሞችን ቤቶች በመገንባት፣ ደም በመለገስ፣ የትምህርት ቁሳቁሶችን በማሰባሰብ፣ የአካባቢ ፅዳት በማከናወንና የወጣቶችን ትስስር በማጠናከር ረገድ በቀጣይነት በትኩረት መሥራት እንደሚገባ ተገልጿል።
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የወጣቶች ክንፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ወጣት ሰይድ ኢብራሂም በበኩላቸው በዚህ ክረምት በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር የተሰሩት ስራዎች የሚደነቅ መሆኑን በመግለጽ ወጣቱን በማሳተፍ ተግባራቱን በማስቀጠል ማህበረሰቡን ተጠቃሚ ማድረግ እንደሚገባም አስገንዝበዋል
በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በ14 የሥራ መስኮች ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኙ ተጠቁሟል በተለይም የደም ልገሳ፣ የአካባቢ ፅዳት፣ የችግኝ ተከላ፣ የትራፊክ ደህንነት አገልግሎት ድጋፍ፣ የትምህርት ቁሳቁስ ማሰባሰብና ለተማሪዎች የማጠናከሪያ ትምህርት መስጠት ዋነኞቹ መሆናቸውን አስገንዝበዋል።
በሪፖርቱም በጠቅላላ በዚህ ክረምት ወንድ 10,955ወጣቶችን ለማሳተፍ ብሎም ሴት 10,954 ድ 21,909 ታቅዶ ክንውን 11,785 ሴ 10,269 ድ 22,054 አፈጻጸም 100% በማሳካት ከመንግስት ካዝና ሊወጣ የሚገባውን 25,361, 824 ብር በላይ ማትረፍ መቻሉን እና አፈጻጸሙ ከ 96% በላይ መሳካቱን በሪፖርቱ ላይ ተመላክቷል
በቀረበው ሪፖርት ላይ ጠለቅ ያለ ውይይት ከተደረገበት በኃላ ደካማ እና ጠንካራ ጎኖች ተነስተውበታል በተነሱ ጠንካራ ጎኖች ላይ በጥንካሬ ማስቀጠል እንደሚገባ ተነስቶ በደካማ የተነሱ ነጥቦችን በቀጣይ በጥንካሬ በመቀየር ሊሰራበት እንደሚገባ ተነስቷል
በመድረኩም የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የወጣቶች ክንፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ወጣት ሰይድ ኢብራሂም
የቤንች ሸኮ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ሚዲያ እና ኮሚዩኒኬሽን ዘርፍ ኃላፊ አቶ ተስፋዬ ዶሻ ጨምሮ ሌሎች የሰላም ሚኒስተር ተወካይ የዞን እና የከተማ ወጣት ኃላፊ ተገኝተውበታል
Mizan Aman city Admin prosperity party