Bench Sheko Zone Communication

Bench Sheko Zone Communication Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Bench Sheko Zone Communication, Government Organization, Mizan Aman, Mizan Teferi.

ነገ ግንቦት 24/2018 ዓ.ም ለሚካሄደው ሰባተኛው አጠቃላይ ምርጫ በጉራፈርዳ ወረደ ባሉ የምርጫ ጣቢያዎች የድምፅ መስጫ  ቦታዎችን ጨምሮ ሌሎች  ዝግጅቶች ተደርገዋል -የየምርጫ ጣቢያ ሀላፊ...
31/05/2026

ነገ ግንቦት 24/2018 ዓ.ም ለሚካሄደው ሰባተኛው አጠቃላይ ምርጫ በጉራፈርዳ ወረደ ባሉ የምርጫ ጣቢያዎች የድምፅ መስጫ ቦታዎችን ጨምሮ ሌሎች ዝግጅቶች ተደርገዋል -የየምርጫ ጣቢያ ሀላፊዎች።

በሸኮ ምርጫ ክልል ውስጥ የሚገኘው የጉራፈርዳ ወረዳ 29 የሸኮ መደበኛ እና 22 የሸኮ ልዩ በድምሩ 51 የምርጫ ጣቢዎች አሉ።

በወረዳው ነገ ለሚካሄደው የድምፅ መስጫ ፅለት በየምርጫ ጣቢያዎች በቂ ዝግጅቶች መደረጋቸውን ያነጋገርናቸው የምርጫ ጣቢያ ሀላፊዎች ገልፀውልናል።

ሚስጥራዊ የድምፅ መስጫ ቦታዎችን ጨምሮ የፖለቲካ ፓርቲ ታዛቢዎች ቦታዎች መዘጋጀታቸውን የኩጀ ከተማ ቀበሌ የምርጫ ጣቢያ ሀላፊ ማናዬ ጌታሁን ገልፀዋል።

ሀላፊው አክለውም መራጮች በድምፅ አሰጣጣጥ ሂደት እንዳይደናገሩ ስለድምፅ አሰጣጡ ሂደት የሚገልፁ ፖስተሮች በሚታይ ቦታ መለጠፉን ተናግረዋል።

በሴጋ ምርጫ ጣቢያ መደበኛና የሸኮ ልዩ የምርጫ ጣቢያዎች መኖራቸውን የነገሩን ደግሞ የጣበያው ሀላፊ ጅሬኛ ኒጉሳ ናቸው።

ሃላፊ ሆነው በሚመሩት የምርጫ ጣቢያው ለነገው ድምፅ መስጫ ቀን በጣቢያው አስፈለጊው ዝግጅቶች መጠናቁን ተናግረዋል።

የጮዲት ቀበሌ ምርጫ ጣቢያ ሀላፊ አየነ በቀለ በበኩላቸው ለመራጮች መጠለያና ማረፊያ ቦታ ከማዘጋጀት ጀምሮ የሚስጥር ድምፅ መስጫ ቦታዎች ፣ የፖለቲካ ፓርቲ ታዘቢዎች ማረፊያዎችን በማዘጋጀት ለነገው ድምፅ አሰጣጥ ምቹ ሆኔታዎች መከናወናቸውን ገልፀዋል ሲል ቤሸቴ ዘግቧል።

በሼይ ቤንች የምርጫ ክልል በ87 የምርጫ ጣቢያዎች ሙሉ የምርጫ ቁሳቁስ የማጓጓዝና የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ተጠናቀዋል ፦ አቶ ሀብታሙ አበበበሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች ነገ ከማለዳው 12:00 ጀም...
31/05/2026

በሼይ ቤንች የምርጫ ክልል በ87 የምርጫ ጣቢያዎች ሙሉ የምርጫ ቁሳቁስ የማጓጓዝና የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ተጠናቀዋል ፦ አቶ ሀብታሙ አበበ

በሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች ነገ ከማለዳው 12:00 ጀምሮ ድምጽ የመሰጠት ስራ እንደሚጀመርም ተገልጿል።

የሼይ ቤንች የምርጫ ክልል አስተባባሪ አቶ ሀብታሙ አበበ ከቤንች ሸኮ ቴሌቪዥን ድርጅት ጋር በነበራቸው ቆይታ በምርጫ ክልሉ በቅርቡ በሰሜን ቤንች ወረዳ የተጨመረ ጣቢያን ጨምሮ 87 የምርጫ ጣቢያዎች እንደሚገኙ ገልጸዋል።

ከመራጮች ምዝገባ ጀምሮ ሰላማዊ የስራ እንቅስቃሴ ላይ እንገኛለን ያሉት አስተባባሪው ለሀገራዊ ምርጫው በ87ቱም የምርጫ ጣቢያዎች የምርጫ ቁሳቁስ የማጓጓዝና የቅድመ ምርጫ ስራዎች መጠናቀቃቸውን ገልጸዋል።

ምርጫው ነገ ከማለዳው 12:00 ጀምሮ በሁሉም ጣቢያዎች እንደሚከናወን አስተባባሪው ገልጸዋል ሲል ቤሸቴ ዘግቧል።

በሼይ ቤንች የምርጫ ክልል በ87 የምርጫ ጣቢያዎች ሙሉ የምርጫ ቁሳቁስ የማጓጓዝና የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ተጠናቀዋል ፦ አቶ ሀብታሙ አበበበሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች ነገ ከማለዳው 12:00 ጀም...
31/05/2026

በሼይ ቤንች የምርጫ ክልል በ87 የምርጫ ጣቢያዎች ሙሉ የምርጫ ቁሳቁስ የማጓጓዝና የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ተጠናቀዋል ፦ አቶ ሀብታሙ አበበ

በሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች ነገ ከማለዳው 12:00 ጀምሮ ድምጽ የመሰጠት ስራ እንደሚጀመርም ተገልጿል።

የሼይ ቤንች የምርጫ ክልል አስተባባሪ አቶ ሀብታሙ አበበ ከቤንች ሸኮ ቴሌቪዥን ድርጅት ጋር በነበራቸው ቆይታ በምርጫ ክልሉ በቅርቡ በሰሜን ቤንች ወረዳ የተጨመረ ጣቢያን ጨምሮ 87 የምርጫ ጣቢያዎች እንደሚገኙ ገልጸዋል።

ከመራጮች ምዝገባ ጀምሮ ሰላማዊ የስራ እንቅስቃሴ ላይ እንገኛለን ያሉት አስተባባሪው ለሀገራዊ ምርጫው በ87ቱም የምርጫ ጣቢያዎች የምርጫ ቁሳቁስ የማጓጓዝና የቅድመ ምርጫ ስራዎች መጠናቀቃቸውን ገልጸዋል።

ምርጫው ነገ ከማለዳው 12:00 ጀምሮ በሁሉም ጣቢያዎች እንደሚከናወን አስተባባሪው ገልጸዋል።
ቤሸቴ
በሚከተለዉ የሚዲያ አማራጮች ይከታተሉን
‎📌Tiktok
‎tiktok.com/
‎📌Telegram
https://t.me/benchshekozonecommunication

‎📌 Youtube
https://youtube.com/?si=PUe2-AlSQHCpY1_r

‎📌 WhatsApp
https://chat.whatsapp.com/IDBp91eytBbL0m0u2rSiSU

ድምጽ ለመስጠት …..ነገ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም በሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምጽ መስጠት ሂደት በሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች ከማለዳው 12፡00 ጀምሮ ይካሄዳል፡፡ኢትዮጵያ ትመርጣለ...
31/05/2026

ድምጽ ለመስጠት …..

ነገ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም በሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምጽ መስጠት ሂደት በሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች ከማለዳው 12፡00 ጀምሮ ይካሄዳል፡፡

ኢትዮጵያ ትመርጣለች!

ለ7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ለመራጭነት መዘጋጀታቸውን የሲዝ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ።የፓርቲዎችን የምርጫ ቅስቀሳ በሚዲያዎች መከታታላቸው የሚመርጡትን ፓርቲ በውል እንዲያውቁ እንዳገዛቸውም ገ...
31/05/2026

ለ7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ለመራጭነት መዘጋጀታቸውን የሲዝ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ።

የፓርቲዎችን የምርጫ ቅስቀሳ በሚዲያዎች መከታታላቸው የሚመርጡትን ፓርቲ በውል እንዲያውቁ እንዳገዛቸውም ገልጸዋል።

ከነጋገርናቸው የሲዝ ከተማ ነዋሪዎች ውስጥ አቶ ኪዳኔ ዲጊቶ ፣ ወይዘሮ አሰገደችና ወይዘሮ ቹቹ ወንድሙ እንደተናገሩት 7ኛውን ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።

ምርጫ የዲሞክራሲያነት መገለጫ ነው ያሉት ነዋሪዎቹ ነገ በማለዳ የምርጫ ካርድ በወሰዱበት የምርጫ ጣቢያ በመገኘት ይመራናል የምንለውን መንግስት ለመምረጥ ዝግጁ ነን ብለዋል።

ወጣት ፍጹም ሀብታሙና አዳነ ኡዲያብ በበኩላቸው በሀገራዊ ምርጫው በሰላም ፣ በልማት ፣ በዲሞክራሲ እና በአጠቃላይ ለሀገር ለውጥ ያመጣል የምንለውን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል ብለዋል።

እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ሰው በመረጠለት ሳይሆን በወሰደው ካርድ ለቀጣይ አምስት አመታት የሚመራውን መንግስት ሊመርጥ ይገባል ሲሉም ገልጸዋል።
ቤ ሼ ቴ

በሰሜን ቤንች ወረዳ በሁሉም ምርጫ ጣቢያ የቅድሚያ ዝግጅት ስራዎች ተጠናቋል በሰሜን ቤንች ወረዳ ስር በሚገኙ ሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች፣ የድምፅ መስጫ ቦታዎች የቅድመ ዝግጅት የተጠናቀቀ ሲሆን ...
31/05/2026

በሰሜን ቤንች ወረዳ በሁሉም ምርጫ ጣቢያ የቅድሚያ ዝግጅት ስራዎች ተጠናቋል

በሰሜን ቤንች ወረዳ ስር በሚገኙ ሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች፣ የድምፅ መስጫ ቦታዎች የቅድመ ዝግጅት የተጠናቀቀ ሲሆን በወረዳው በ21ዱም ቀበሌ 38 ምርጫ ጣቢያ እንዳወረዳን 38ሺ 975 መራጮች የሚበጃቸውን ፓርቲ ለመምረጥ ዝግጁ መሆናቸው ታውቋል።

ለድምፅ አሰጣጡ ሂደት የሚያስፈልጉ የቴክኒክና የሎጂስቲክስ ዝግጅቶች የተጠናቀቀ መሆናቸው ማረጋገጥ ተችሏል።

ነገ ግንቦት 24/2018 ዓ.ም ለሚካሄደው ሰባተኛው አጠቃላይ ምርጫ በጉራፈርዳ ወረደ ባሉ የምርጫ ጣቢያዎች የድምፅ መስጫ  ቦታዎችን ጨምሮ ሌሎች  ዝግጅቶች ተደርገዋል -የየምርጫ ጣቢያ ሀላፊ...
31/05/2026

ነገ ግንቦት 24/2018 ዓ.ም ለሚካሄደው ሰባተኛው አጠቃላይ ምርጫ በጉራፈርዳ ወረደ ባሉ የምርጫ ጣቢያዎች የድምፅ መስጫ ቦታዎችን ጨምሮ ሌሎች ዝግጅቶች ተደርገዋል -የየምርጫ ጣቢያ ሀላፊዎች።

በሸኮ ምርጫ ክልል ውስጥ የሚገኘው የጉራፈርዳ ወረዳ 29 የሸኮ መደበኛ እና 22 የሸኮ ልዩ በድምሩ 51 የምርጫ ጣቢዎች አሉ።

በወረዳው ነገ ለሚካሄደው የድምፅ መስጫ ፅለት በየምርጫ ጣቢያዎች በቂ ዝግጅቶች መደረጋቸውን ያነጋገርናቸው የምርጫ ጣቢያ ሀላፊዎች ገልፀውልናል።

ሚስጥራዊ የድምፅ መስጫ ቦታዎችን ጨምሮ የፖለቲካ ፓርቲ ታዛቢዎች ቦታዎች መዘጋጀታቸውን የኩጀ ከተማ ቀበሌ የምርጫ ጣቢያ ሀላፊ ማናዬ ጌታሁን ገልፀዋል።

ሀላፊው አክለውም መራጮች በድምፅ አሰጣጣጥ ሂደት እንዳይደናገሩ ስለድምፅ አሰጣጡ ሂደት የሚገልፁ ፖስተሮች በሚታይ ቦታ መለጠፉን ተናግረዋል።

በሴጋ ምርጫ ጣቢያ መደበኛና የሸኮ ልዩ የምርጫ ጣቢያዎች መኖራቸውን የነገሩን ደግሞ የጣበያው ሀላፊ ጅሬኛ ኒጉሳ ናቸው።

ሃላፊ ሆነው በሚመሩት የምርጫ ጣቢያው ለነገው ድምፅ መስጫ ቀን በጣቢያው አስፈለጊው ዝግጅቶች መጠናቁን ተናግረዋል።

የጮዲት ቀበሌ ምርጫ ጣቢያ ሀላፊ አየነ በቀለ በበኩላቸው ለመራጮች መጠለያና ማረፊያ ቦታ ከማዘጋጀት ጀምሮ የሚስጥር ድምፅ መስጫ ቦታዎች ፣ የፖለቲካ ፓርቲ ታዘቢዎች ማረፊያዎችን በማዘጋጀት ለነገው ድምፅ አሰጣጥ ምቹ ሆኔታዎች መከናወናቸውን ገልፀዋል።ቤንች ሸኮ ቴሌቭዥን ዘግቧል።

"በነገው እለት ለሚካሄደው ምርጫ ድምጻችንን ለመስጠት ተዘጋጅተናል :-የጉራፈረዳ ወረዳና የቢፍቱ ከተማ  ነዋሪዎች በነገው እለት የሚካሄደውን 7ተኛው  አጠቃላይ ሀገራዊ ምርጫን ተከትሎ መራጮች...
31/05/2026

"በነገው እለት ለሚካሄደው ምርጫ ድምጻችንን ለመስጠት ተዘጋጅተናል :-የጉራፈረዳ ወረዳና የቢፍቱ ከተማ ነዋሪዎች

በነገው እለት የሚካሄደውን 7ተኛው አጠቃላይ ሀገራዊ ምርጫን ተከትሎ መራጮች 12:00 ስአት ጀምሮ የምርጫ ድምጻቸውን ለመስጠት በዝግጅት ላይ መሆናቸውን የጉራፈረዳ ወረዳና የቢፍቱ ከተማ ነዋሪዎች ገልጸዋል።

ነዋሪዎች እንደገለፁት ካርድ ያወጣ ማንኛውም የኅብረተሰብ ክፍል ግንቦት 24 ወደ ምርጫ ጣቢያ መሄድ እና ለሀገር የሚበጀውን መምረጥ ሀገር አለኝ ከሚል ዜጋ የሚጠበቅ እንደሆነም ገልጸዋል።

ሀገራችን ኢትዮጵያ ነገ ከለሊቱ 12:00ሰዓት ጀምሮ የምታደርገው 7ተኛ አጠቃላይ ሀገራዊ ምርጫም ያለምንም ችግር ፍጹም ሰላማዊ ሆኖ ተጀምሮ እንዲጠናቀቅ እንፈልጋለንም በማለት ለዚህም ኀላፊነታችን እንወጣለን በማለት ተናግረዋል ሲል የወረዳው ኮሚኒኬሽን ዘግቧል።

ለመራጮች ድምፅ መስጫ የሚያገለግሉ ቁሳቁሶች ተሟልተዋል:-የሚዛን አማን ምርጫ ጣቢያ አስተባባሪዎችበ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ዜጎች ድምፅ እንዲሰጡ የሚያስችሏቸው ቁሳቁሶች መሟላታቸውን በሚዛን-አማን...
31/05/2026

ለመራጮች ድምፅ መስጫ የሚያገለግሉ ቁሳቁሶች ተሟልተዋል:-የሚዛን አማን ምርጫ ጣቢያ አስተባባሪዎች

በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ዜጎች ድምፅ እንዲሰጡ የሚያስችሏቸው ቁሳቁሶች መሟላታቸውን በሚዛን-አማን ከተማ ከሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች መካከል ጋቸብ ውሽቅን፣ኮሶኮል፣ዋና ማዘጋጃ፣ሾንጋ ምርጫ ሀ እንዲሁም ኮመታ ሀ ምርጫ ጣቢያ አስተባባሪዎች ተናግረዋል።

የዋና ማዘጋጃ ምርጫ ጣቢያ አስተባባሪ የሆኑት አቶ ንጉሴ ጎበና ከኮሮጆ ጀምሮ ያሉ ቁሳቁሶች መሟላታቸውንና መራጮች በአየር ንብረት መለዋወጥ እንዳይጉላሉ ድንኳንና ዳስ የማዘጋጀት ተግባራት መከናወናቸውን አሳውቀዋል።

የምርጫ ቁሳቁሶችን መረከባቸውንና ታዛቢዎች እንዲሁም የፖለቲካ ፓርቲዎች ስራቸውን እንዲያሳልጡ ማረፊያ ቦታዎች ዝግጁ መሆናቸውን የገለፁት የሚዛን ኮመታ ሀ ምርጫ ጣቢያ ሰብሳቢ አቶ ሀብታሙ ሁሴን ናቸው።

የምርጫ ሂደቱ ግንቦት 24 ቀን ከጠዋቱ 12 ሰዓት ጀምሮ የሚከናወን ይሆናል ያሉት የሾንጋ ሀ ምርጫ ጣቢያ አስተባባሪ አቶ ደረጀ ታሪኩ በአስተባባሪዎችና አስፈፃሚዎች በኩል የሚጠበቁ የስራ ድርሻዎች መጠናቀቃቸውን አመላክተዋል።

አስተባባሪዎቹ ምርጫው ሰላማዊ በሆነ መንገድ እንዲካሄድ የፀጥታ አካላት ተመድበው ከስጋት ነፃ ቀጠና እንዲፈጠር እየሰሩ ነው ብለዋል ሲል ደቡብ ምዕራብ ሚዲያ ኔትወርክ ዘግቧል።

ነገ ግንቦት 24 በሚካሄደው 7ተኛው ጠቅላላ ምርጫኢትዮጵያ ትመርጣለች።የሚመራቸውና የሚያስተዳድሯቸውን መንግስት ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን በቤንች ሸኮ ዞን ሸኮ ወረዳና በሸኮ ከተማ አስተዳደር የ...
31/05/2026

ነገ ግንቦት 24 በሚካሄደው 7ተኛው ጠቅላላ ምርጫ
ኢትዮጵያ ትመርጣለች።

የሚመራቸውና የሚያስተዳድሯቸውን መንግስት ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን በቤንች ሸኮ ዞን ሸኮ ወረዳና በሸኮ ከተማ አስተዳደር የሚገኙ መራጮች ተናገሩ።

የቤንች ሸኮ ቴሌቭዥን ተዟዘርው ያነጋገራቸው የሸኮ ልዩ ምርጫ ክልል የሸኮ ወረዳና የሸኮ ከተማ አስተዳደር ነዋሪዎች እንደገለፁት ነገ ግንቦት 24 በሚካሄደው 7ተኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚመራቸውና የሚያስተዳድሯቸውን መንግስት ለመምረጥ ካርዳቸውን ይዞ መዘጋጀታቸውን ተናገረዋል።

በሚዲያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የራሳቸውን ፖሊሲዎች አቀርበው ባደረጉት ክርክር ግንዛቤ አገኝተው የሚያስተዳደራቸው ሀገርን ሊያሻግር የሚችል ፓርቲና መንግስትን ለመምረጥ በጉጉት እየተጠባበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን የሰጡት መራጮች ገልፀዋል።

በተለይም በነገው ዕለት ሌሊት 12:00 ሰዓት ተጀምሮ እስከ ምሽት 12:00 ሰዓት ድርስ የሚካሄደው 7ተኛው ጠቅላላ ምርጫ ከራሳቸውም ባለፈ ጎርቤታቸውን፣ አከባቢያቸውና ከስራቸው ያሉት ሰዎችን በማስተባበር የተሰጣቸውን ሰዓት ተጠቅመው አሻራቸውን ማስቀመጥ እንዳለባቸውም መልዕክታቸውን አስተላለፈዋል።

መራጩ ህብረተሰብ በወሰዷቸው ካርድ ድምፃቸውን ሌሊት ከ12 ሰዓት ጀምሮ ሊሰጡ እንደሚገባም መራጮቹ ገልፀዋል ሲል ቤሸቴ ዘግቧል።

Address

Mizan Aman
Mizan Teferi

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Bench Sheko Zone Communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share