31/05/2026
ነገ ግንቦት 24/2018 ዓ.ም ለሚካሄደው ሰባተኛው አጠቃላይ ምርጫ በጉራፈርዳ ወረደ ባሉ የምርጫ ጣቢያዎች የድምፅ መስጫ ቦታዎችን ጨምሮ ሌሎች ዝግጅቶች ተደርገዋል -የየምርጫ ጣቢያ ሀላፊዎች።
በሸኮ ምርጫ ክልል ውስጥ የሚገኘው የጉራፈርዳ ወረዳ 29 የሸኮ መደበኛ እና 22 የሸኮ ልዩ በድምሩ 51 የምርጫ ጣቢዎች አሉ።
በወረዳው ነገ ለሚካሄደው የድምፅ መስጫ ፅለት በየምርጫ ጣቢያዎች በቂ ዝግጅቶች መደረጋቸውን ያነጋገርናቸው የምርጫ ጣቢያ ሀላፊዎች ገልፀውልናል።
ሚስጥራዊ የድምፅ መስጫ ቦታዎችን ጨምሮ የፖለቲካ ፓርቲ ታዛቢዎች ቦታዎች መዘጋጀታቸውን የኩጀ ከተማ ቀበሌ የምርጫ ጣቢያ ሀላፊ ማናዬ ጌታሁን ገልፀዋል።
ሀላፊው አክለውም መራጮች በድምፅ አሰጣጣጥ ሂደት እንዳይደናገሩ ስለድምፅ አሰጣጡ ሂደት የሚገልፁ ፖስተሮች በሚታይ ቦታ መለጠፉን ተናግረዋል።
በሴጋ ምርጫ ጣቢያ መደበኛና የሸኮ ልዩ የምርጫ ጣቢያዎች መኖራቸውን የነገሩን ደግሞ የጣበያው ሀላፊ ጅሬኛ ኒጉሳ ናቸው።
ሃላፊ ሆነው በሚመሩት የምርጫ ጣቢያው ለነገው ድምፅ መስጫ ቀን በጣቢያው አስፈለጊው ዝግጅቶች መጠናቁን ተናግረዋል።
የጮዲት ቀበሌ ምርጫ ጣቢያ ሀላፊ አየነ በቀለ በበኩላቸው ለመራጮች መጠለያና ማረፊያ ቦታ ከማዘጋጀት ጀምሮ የሚስጥር ድምፅ መስጫ ቦታዎች ፣ የፖለቲካ ፓርቲ ታዘቢዎች ማረፊያዎችን በማዘጋጀት ለነገው ድምፅ አሰጣጥ ምቹ ሆኔታዎች መከናወናቸውን ገልፀዋል ሲል ቤሸቴ ዘግቧል።