Bench Sheko Zone Communication

Bench Sheko Zone Communication Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Bench Sheko Zone Communication, Government Organization, Mizan Aman, Mizan Teferi.

የሃይማኖት ተቋማት የሕብረተሰቡን የሞራል ልዕልና እና የጋራ አብሮነትን ጠብቆ ለማቆየት ያላቸውን ሚና ማጠናከር አለባቸው -ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ የሃይማኖት ተቋማት የሕብረተሰቡን የሞራል ...
01/09/2026

የሃይማኖት ተቋማት የሕብረተሰቡን የሞራል ልዕልና እና የጋራ አብሮነትን ጠብቆ ለማቆየት ያላቸውን ሚና ማጠናከር አለባቸው -ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ

የሃይማኖት ተቋማት የሕብረተሰቡን የሞራል ልዕልና፣ የሰላም እሴቶች እና የጋራ አብሮነትን ጠብቆ ለማቆየት ያላቸውን ሚና አጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ገለጹ።

የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ 15ኛ ዓመት የምሥረታ በዓልና 18ኛው መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ እየተካሄደ ነው።

የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በዚሁ ወቅት ጉባኤው አያሌ የኢትዮጵያ ታሪክ፣ የሕዝቦቿ አብሮነት እና የጋራ መሻታችን የምንዘክርበትና የምንመክርበት ታሪካዊ መድረክ ነው ብለዋል።

ጉባዔው ላለፉት 15 ዓመታት የእምነት ተቋማት በትብብር እና በኅብረት ለኢትዮጵያ የዕድገት ጉዞ ከፍ ያለ ፋይዳ እና መሠረት ያለው መሆኑን ያስመሰከሩበት መሆኑንም ተናግረዋል።

የዕውቀት፣ የጥበብ፣ የማስተዋል እና የአብሮነት መገለጫ ይሰምር ዘንድ 15 ዓመታትን መሻገሩ ጉባዔውን ልዩ እንደሚያደርገው ጠቁመዋል።

ኢትዮጵያ ተከታታይ ትውልዶች በሐሳባቸው፣በጉልበታቸው እና በጸሎታቸው የገነቧት ታላቅ ሀገር መሆኗን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ መሠረት ለእምነታችን ያለን ጽናት፣ ለሰው ልጅ ያለን ከበሬታ እና ለብዙኅነታችንና አንድነታችን የምንሰጠው ከፍ ያለ አክብሮት ነው ብለዋል።

ከኢትዮጵያ ምሰሶዎች እና ማገሮች መካከል ደግሞ ለዘመናት የሕዝቡን ሞራልና ስብዕና ሲቀርጹ የኖሩት የእምነት ተቋማት መሆናቸውን አመልክተዋል።

የሃይማኖት አባቶች የሕዝቡ የሞራልና የሥነ-ምግባር ዋና ጠባቂ መሆናቸውን ገልጸው፤ በተለይም ታዳጊዎች እና ወጣቶች በውጭ የተውሶ ሐሳቦችና ደራሽ ወጎች እንዳይወሰዱ ትምህርት መለገስ እንዳለባቸው ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ እና የሕዝቧ ጽናት በጠንካራ መሠረት ላይ እንዲታነጽ ከፍ ያለ ሚናቸውን አጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።

አልፎ አልፎ ከኢትዮጵያዊ ባህል፣ ሥነ-ምግባር፣ ሕሊና እና ጨዋነት ውጭ የሆኑ ቅጥፈት፣ እብለት፣ ሌብነት፣ ውስልትና፣ ጭካኔ እና ለሰው ልጅ ሕይወት ደንታ ቢስነት ጎልተው እንዳይታዩ በርትቶ መከላከል እና ማስተማር እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

በዚህ የጥፋት መንገድ የሚመላለሱትን በመገሰጽ፣ ስሜታቸውን ተቆጣጥረው ይሄዱ ዘንድ ማረም እና የሚበጁ ዜጎችን ማውጣት ተቀዳሚ ተግባራቸው ሊሆን እንደሚገባም አመልክተዋል።

የእምነት መሪዎች በጨለማ ውስጥ ብርሃንን የሚፈነጥቁ መቅረዞች፣ በተስፋ መቁረጥ ማዕበል ውስጥ እንደ ጽኑ አለት የቆሙ የብርታት ምንጮች እና በተከፋፈሉ ልቦች ውስጥ የመመካከር፣ የመተባበር፣ የይቅርታ እና የእርቅ "ሐዋርያት" እና "ሱሃቦች" ናችሁ ብለዋል።

በተለያዩ መድረኮች ለዘመናት የገነባነው መተሳሰብ፣ መደጋፍ እና መከባበር ለመናድ የሚታትሩ እንዲሁም መከፋፈልን እንደ ታላቅ ስኬት የሚቆጥሩ ድምጾች የተበራከቱበት ጊዜ መሆኑን ጠቁመዋል።

በቅርቡ ኢትዮጵያ ባካሄደችው ሀገራዊ የምክክር መድረክ የእምነት ተወካዮች ድርሻ ልክ እንደሌሎቹ ሁሉ ከፍ ያለ እንደነበር መመልከታቸውን ተናግረዋል።

የሃይማኖት አባቶች የሂደቱ ተሳታፊዎች ብቻ ሳይሆኑ፣ ሀገራዊ ስክነትን ለመላበስ በሚደረገው ጥረት ሁሉ የላቀ ሚና እንደነበራቸው ተናግረዋል።

መመካከር በእውነት፣ በይቅር ባይነት እና በጋራ መግባባት ላይ እንዲጸና፣ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ሐሳቡን እንዲያጋራ፣ እንዲሁም ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም እና እድገት መሠረት ይጣል ዘንድ ታሪካዊ ኃላፊነት መወጣታቸውን አንስተዋል።

ሀገራዊ ዕድገትና ልማትን ማገዝ እንዲሁም በንቃት መሳተፍ የፖለቲካ ጉዳይ ብቻ አለመሆኑን ገልጸው፤ ከዘመኑ ዓለም አቀፋዊ ዕድገት ጋር እኩል መራመድ እና እድገትን ማላቅ አስፈላጊ መሆኑን አመልክተዋል።

መንግሥት የእምነት ተቋማት ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም፣ ለማህበራዊ ውህደትና ለአጠቃላይ ዕድገት የሚያደርጉትን ላቅ ያለ አስተዋጽኦ በጥልቅ እንደሚረዳ እና የጎላ እውቅናና ከበሬታ እንደሚሰጥ ገልጸዋል።
(ኢዜአ
በሚከተለዉ የሚዲያ አማራጮች ይከታተሉን
‎📌Tiktok
‎tiktok.com/
‎📌Telegram
https://t.me/benchshekozonecommunication

‎📌 Youtube
https://youtube.com/?si=PUe2-AlSQHCpY1_r

‎📌 WhatsApp
https://chat.whatsapp.com/IDBp91eytBbL0m0u2rSiSU

በሚዛን መሰረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ኮምፓሽን ፕሮጀክት ለደሀ ደሀ ተማሪዎችና ወላጆች የአዲስ አመት መዋያ ከ1.8 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ በማድረግ  የምግብ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ።ፕሮጀክቱ...
01/09/2026

በሚዛን መሰረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ኮምፓሽን ፕሮጀክት ለደሀ ደሀ ተማሪዎችና ወላጆች የአዲስ አመት መዋያ ከ1.8 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ በማድረግ የምግብ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ።

ፕሮጀክቱ ለ216 የደሀ ደሀ ተማሪዎችን ጨምሮ ከ2ሺ በላይ ቤተሰቦችን ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑም ተገልጿል።

በሚዛን መሰረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን የኢቲ - 3002 የህጻናትና ወጣቶች ልማት ፕሮጀክት ዳይሬክተር አቶ ተሾመ ዘገየ እንደገለጹት ቤተክርስቲያኗ ከኮምፓሽን ፕሮጀክት በምታገኘው የገንዘብ ድጋፍ በመደበኛ ተግባር 216 የደሀ ደሀ ቤተሰብ ተማሪዎችን የምግብ ፣ የአልባሳትና የትምህርት ቁሳቁስ ወጪን በመሸፈን እየሰራች ትገኛለች ብለዋል።

የዛሬው ድጋፍ አዲስ አመትን ከክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት ጋር በማስተሳሰር ተማሪዎችና ቤተሰቦቻቸው በዓሉን በደስታ እንዲያሳልፉ 1 ሚሊየን 813ሺ ብር ወጪ በማድረግ ጤፍ ፣ ዘይት ፣ አልባሳት ፣ ደብተር ፣ እስክሪብቶ ፣ እርሳስና ሳሙና ድጋፍ መደረጉን ገልጸዋል።

ቤተክርስቲያኗ ከፕሮጀክቱ ጋር በመተባበር የእምነት ፣ የብሔርና የቀለም ልዩነት ሳታደርግ የደሀ ደሀ ቤተሰብ ተማሪዎችን በዘላቂነት ለመደገፍ እየሰራች መሆኑን የጠቆሙት አቶ ተሾመ በቀጣይ ሳምንት የዚሁ ድጋፍ አካል የሆነው የአልባሳት ስርጭት እንደሚደረግም ገልጸዋል።

አሁን ላይ ተማሪዎችን ጨምሮ ከ2ሺ በላይ የተማሪ ቤተሰቦችን አቅፎ ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝም ጠቁመዋል።

የሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር ሴቶች ህጻናትና ማህበራዊ ጉዳይ ጽህፈት ቤት ባለሙያ ወይዘሮ ደብሪቱ ሀይሉ እንደገለጹት ፕሮጀክቱ 216 ህጻናትና ቤተሰቦቻቸውን ከኢኮኖሚ ተጋላጭነት ለማላቀቅ ላለፉት 5 አመታት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

በከተማ አስተዳደሩ በዚህ ተግባር ውስጥ የተሰማሩ 3 ፕሮጀክቶች መኖራቸውን ገልጸው ከመደበኛ የመማር ማስተማር ስራ ባሻገር በምግብ ድጋፍ በማድረግ ትልቁን የከተማ አስተዳደር የህጻናትን ተጋላጭነት በመቀነስ ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ይገኛሉ ብለዋል።

በዕለቱ ድጋፍ ከተደረገላቸው መካከል ወይዘሮ ሀና ገዛኸኝና ወርቅነሽ ቆጭቶ እንደተናገሩት ፕሮጀክቱ ላለፉት 5 አመታት የልጆቻቸውን የትምህርት ቁሳቁስና አልሚ ምግቦችን ድጋፍ እያደረገላቸው መቆየቱን ገልጸዋል። አመት በዓላትን ምክንያት በማድረግ ከልጆቻችን ጋር በደስታ እንድናሳልፍ ተጨማሪ የምግብ ቁሳቁስና የአልባሳት ድጋፍ እያደረገላቸው እንደሚገኝም ጠቁመዋል ሲል ቤንች ሸኮ ቴሌቪዥን ነው።

በሚከተለዉ የሚዲያ አማራጮች ይከታተሉ
‎📌Tiktok
‎tiktok.com/
‎📌Telegram
https://t.me/benchshekozonecommunication

‎📌 Youtube
https://youtube.com/?si=PUe2-AlSQHCpY1_r

‎📌 WhatsApp
https://chat.whatsapp.com/IDBp91eytBbL0m0u2rSiSU

የ2018 አጠቃላይ የፀጥታ ስራዎችን በጥልቀት የመገምገምና ለ2019 በጀት ዓመት የቀድሞ ዝግጅት‎ስራዎች ላይ ውይይት ተካሄደ።‎ የፀጥታ ስራዎችን ‎በጥልቅ በመገምገም ለ2019 በጀት ዓመት የ...
01/09/2026

የ2018 አጠቃላይ የፀጥታ ስራዎችን በጥልቀት የመገምገምና ለ2019 በጀት ዓመት የቀድሞ ዝግጅት
‎ስራዎች ላይ ውይይት ተካሄደ።

የፀጥታ ስራዎችን ‎በጥልቅ በመገምገም ለ2019 በጀት ዓመት የቀድሞ ‎ዝግጅት ስራዎች ላይ ውይይት ተካሂዷል።
‎‎መድረኩን የመሩት የሸኮ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ‎ፀጥታ ክላስተር አስተባባሪ አቶ አሊ ሾጪ የ2018 ዓ.ም
‎የፀጥታ ስራዎች በደካማና በጠንካራ ጎን በመገምገም ‎ለ2019 የተሻለና አመርቂ የሆነ ሰላምን ለማስፈን ከወዲሁ ስራ መጀመራቸውን ገልፀዋል።

‎የፓሊስና የፀጥታ አካላት ዋናኛው ስራቸው የሕዝብን ‎ደንነት መጠበቅ ሲሆን በከተማው አብዛኛው ችግር
‎ለመፍጠር የሚፈልጉ ወጣቶች ስለሆኑ የፀጥታ አካላቶች እንደ 2018 ዓ.ም ሳይሆን በ2019 ዓ.ም
‎በጀት ዓመት አብሶ በወጣቶችና በከተማው ችግርን‎ ለመፍጠር የሚፈልጉ አካላት ላይ በአዲስ ሀይልና
‎በአዲስ መንፈስ እንደሚሰሩ ተገልጿል።

‎ማህበረሰቡ በአብዛኛው የህግን ዳኝነት በመተው ‎የባህላዊ ዳኝነት በቶሎ ይፈርድልኛል በማለት ከአከባቢው ማህበረሰብ ባለፈ የመንግስት ባለስልጣናትን በማስፈራራት ወደ ቶሞ በመሄድ ‎ከህግ የበላይነት የባህል ፍርዶችን በመከተል ላይ ስለሆኑ መንግስት እነዚህን አይነት አካላቶችን ለህግ የማቅረብ ስራዎችን መስራት እንዳለበት ተጠቁሟል።

‎በተጨማሪ በመድረኩ አስተያየት የሰጡት የሸኮ ከተማ ‎አስተዳደር የፓሊስ አዛዥ ም/ኢ አደም ዮናስ በከተማው
‎ሰሞኑን የተነሱ ያሉት ወጣት አፈሳ ተጀምሯል በሚል ‎እየተነሱ ያሉ ስህተትና ከእውነት የራቁ ወሬ መሆኑን ተናግረው ለ2019 አዲሱ አመት በዓል በሰላም እንዲያልፍ የቀድሞ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ም/ኢ ገልፀዋል።
የወረዳው ኮሚኒኬሽን እንደዘገበው
በሚከተለዉ የሚዲያ አማራጮች ይከታተሉን
‎📌Tiktok
‎tiktok.com/
‎📌Telegram
https://t.me/benchshekozonecommunication

‎📌 Youtube
https://youtube.com/?si=PUe2-AlSQHCpY1_r

‎📌 WhatsApp
https://chat.whatsapp.com/IDBp91eytBbL0m0u2rSiSU







የሲዝ ከተማ ምክር ቤት 1ኛ ዙር 6ኛ ዓመት የስራ ዘመን 14ኛ መደበኛ ጉባዔውን ማካሄደ ጀመረ።ምክር ቤቱ ለተከታታይ ሁለት ቀናት በሚያካሂደው ጉባዔ የአስፈፃሚ ተቋማትን የ2018 በጀት አመት...
01/09/2026

የሲዝ ከተማ ምክር ቤት 1ኛ ዙር 6ኛ ዓመት የስራ ዘመን 14ኛ መደበኛ ጉባዔውን ማካሄደ ጀመረ።

ምክር ቤቱ ለተከታታይ ሁለት ቀናት በሚያካሂደው ጉባዔ የአስፈፃሚ ተቋማትን የ2018 በጀት አመት ሪፖርት በመገምገም የቀጣይ አቅጣጫዎችን እንደሚያስቀምጥም ይጠበቃል።

የሲዝ ከተማ ምክር ቤት የ2018 በጀት አመት የስራ ሪፖርት የሚቀርብና የከተማ አስተዳደሩ የ2019 በጀትም ቀርቦ በምክር ቤት እንደሚፀድቅ ይጠበቃል።መረጃው የከተማ አስተዳደሩ ኮምንኬሽን ነው።

በሚከተለዉ የሚዲያ አማራጮች ይከታተሉን
📌Tiktok
tiktok.com/
📌Telegram
https://t.me/benchshekozonecommunication

📌 Youtube
https://youtube.com/?si=PUe2-AlSQHCpY1_r

📌 WhatsApp
https://chat.whatsapp.com/IDBp91eytBbL0m0u2rSiSU

የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን ለዘላቂ ሰላምና ልማት የጎላ አበርክቶ አለው - አፈጉባኤ አገኘሁ ተሻገርየኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል ለዘላቂ ሰላምና ልማት እንዲሁም...
01/09/2026

የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን ለዘላቂ ሰላምና ልማት የጎላ አበርክቶ አለው - አፈጉባኤ አገኘሁ ተሻገር

የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል ለዘላቂ ሰላምና ልማት እንዲሁም የሕዝቦችን ትስስር ለማጠናከር የጎላ አበርክቶ ይኖረዋል አሉ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈጉባኤ አገኘሁ ተሻገር፡፡

የ21ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል አስተባባሪ ዐቢይ ኮሚቴ በበዓሉ መሪ ዕቅድ ላይ የውይይት መድረክ እያካሄደ ይገኛል፡፡

አፈጉባኤ አገኘሁ ተሻገር በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በዓሉ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ልምዳቸውን፣ ተሞክሯቸውን፣ ባህላቸውን እንዲለዋወጡ፣ ዲሞክራሲያዊ አንድነታቸውን እንዲያጠናክሩ እድል የሚፈጥር ነው፡፡

ለዘላቂ ሰላም፣ ልማትና ኢኮኖሚ እድገት እንዲሠሩና በሕዝቦች መካከል አንድነትና ትስስር እንዲኖር በማድረግ በኩል የጎላ አበርክቶ እንደሚኖረውም አመልክተዋል፡፡

በበዓሉ ጉልህ የሆኑ ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ውጤቶች እንዲመዘገቡ ከወዲሁ በትኩረት ይሠራል ነው ያሉት፡፡

መጪው በዓል 7ኛውን ሀገራዊ ምርጫና ሀገራዊ ምክክር ጨምሮ የሀገራችንን ቀጣይ መንገድ የጠረጉና ወደ አዲስ ተስፋና ምዕራፍ ያሸጋገሩ ሀገራዊ ሁነቶች በተከናወኑበት ማግስት የሚከበር በዓል እንደመሆኑ የተለየ ትርጉም ይኖረዋል ብለዋል፡፡
21ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል በኦሮሚያ ክልል የገዳ ስርዓትን ጨምሮ የበርካታ ታሪካዊና ባህላዊ መስህቦች ባለቤት፣ ሕዝቦች ተከባብረው በሚኖሩባትና የብዝሃነት ማሳያ በሆነችው ጅማ ከተማ ይከበራል፡፡

በዓሉ ከልማት፣ ከዲሞክራሲ ግንባታ ጋር ቀጥታ ግንኙነት ባላቸው ታላላቅ ሀገራዊ ሁነቶች ታጅቦ እንደሚከበር መናገራቸውን ከምክር ቤቱ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

ኤፍ ኤም ሲ

የበጎ ፈቃድ አገልገሎት ማህበራዊ እሴቶችንና ህብረብሔራዊ አንድነትን ከማጠናከር ረገድ ጉልህ ሚና እየተጫወተ መሆኑ ተገለፀ‎‎በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የክረምት ወራት በጎ ፈቃድ ...
01/09/2026

የበጎ ፈቃድ አገልገሎት ማህበራዊ እሴቶችንና ህብረብሔራዊ አንድነትን ከማጠናከር ረገድ ጉልህ ሚና እየተጫወተ መሆኑ ተገለፀ

‎በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የክረምት ወራት በጎ ፈቃድ አገልግሎት "በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል ዕሳቤ እየተሰጠ ይገኛል።

‎በክልሉ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊና የክልሉ ክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ቴክኒክ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ግርማ ባሻ እንደገለፁት፤ ተግባሩ ካለው ፋይዳ አኳያ ታይቶ ከክረምት ባለፈ በበጋ ወቅት እየተተገበረ መጥቷል።

‎ከለውጡ ጊዜ ወዲህም የተደራጀ የዕቅድ፣ የስትራቴጂና የፖሊሲ አካል በመሆን የዜጎችን ማህበራዊ እሴትና ህብረብሔራዊ አንድነት እያጠናከረ ነው ብለዋል።

‎ዘንድሮ በ14 የስምሪት መስኮችን 57 የሚሆኑ ዝርዝር ተግባራትን ባካተተ መልኩ እየተከናወነ ሲሆን፤ 1 ነጥብ 5 ሚሊየን በጎ ፈቃደኞችን ከሴቶች፣ ከወጣቶች፣ ከሀይማኖት ተቋማት፣ ከፖለቲካ ፓርቲዎችና ሌሎች ተቋማት አሳትፏል።

‎በዚህም በገንዘብና በአይነት ወደ 1 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር የሚገመት ስራ 2 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚሆኑ ዜጎችን ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ ነው ሲሉ አቶ ግርማ ተናግረዋል።

‎በዋናነት የቤቶች ግንባታና እድሳት ስራን የመርሐ-ግብሩ ማስጀመሪያ በማድረግ ከላይ በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት የጭቃ ቤቶችን የመቀነስ ተግባር እየተከናወነ ነው።

‎በተጨማሪ የችግኝ ተከላ፣ የደም ልገሳ፣ ለአቅመ ደካሞች የፍጆታ እቃ ማሟላት፣ የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ የማድረግ፣ ከጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶች፣ ከህገ-ወጥ እንቅሰቃሴ፣ ከትራፊክ ደህንነትና መሠል ጉዳዮች ጋር ተያይዞ ግንዛቤ የማስጨበጥ ስራዎች ለአብነት የሚጠቀሱ መሆናቸው ተገልጿል።

‎ከሁሉም የሀገሪቱ ክልሎች የተውጣጡ ወሰን ተሻጋሪ በጎ ፈቃደኞችን በኮንታ ዞን በመቀበል ያስተናገዱ ሲሆን፤ በፓርቲው ሴቶችና ወጣቶች ክንፍ በኩል ከክልሉ ባለፈ ወደ ጋንቤላና ኦሮሚያ ክልሎች እንቅስቃሴ ይኖራልም ተብሏል።

‎አብዛኞቹ ስራዎች ከግማሽ በላይ ተከናውነዋል ያሉት አቶ ግርማ፤ ቀጣይነት ሊኖረው ስለሚገባ ሁሉም ዜጋ በጎ ተግባርን ባህል አድርጎ እንዲቀበልና እንዲያጠናክር አሳስበዋል።

‎የክረምት ወራት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ሲጠናቀቅ የበጋ ወቅት ማስጀመሪያ እንደሚኖርም ጥቆማ ሰጥተዋል።
በሚከተለዉ የሚዲያ አማራጮች ይከታተሉን
‎📌Tiktok
‎tiktok.com/
‎📌Telegram
https://t.me/benchshekozonecommunication

‎📌 Youtube
https://youtube.com/?si=PUe2-AlSQHCpY1_r

‎📌 WhatsApp
https://chat.whatsapp.com/IDBp91eytBbL0m0u2rSiSU


ወሰን ተሻጋሪ የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት የህዝቦችን መቀራረብ፣ የሀገራዊ አንድነትንና የመተሳሰብ እሴቶችን ያጠናክራል ተባለ"በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መርህ ቃል የተካሄደው የወሰን...
31/08/2026

ወሰን ተሻጋሪ የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት የህዝቦችን መቀራረብ፣ የሀገራዊ አንድነትንና የመተሳሰብ እሴቶችን ያጠናክራል ተባለ

"በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መርህ ቃል የተካሄደው የወሰን ተሻጋሪ የወጣቶች ሀብት ማሰባሰብ መረሀ ግብር በቤንች ሸኮ ዞን ተካሂዷል።

የቤንች ሸኮ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የወሰን ተሻጋሪ ሀብት ማሰባሰብ ከ 380ሺ ብር በላይ የሚገመት ሀብት በመሰብሰብ ለክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት አስረክቧል።

ወሰን ተሻጋሪ የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት የህዝቦችን መቀራረብ፣ የሀገራዊ አንድነትንና የመተሳሰብ እሴቶችን ያጠናክራል ሲሉም የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሰይድ ኢብራሂም ተናግረዋል።

አክለውም በክልላችን የሚገኙ ዞኖች ይህንን የወሰን ተሻጋሪ ተግባር በብቃት እየተገበሩ ያለ ሲሆን ቤንች ሸኮ ዞንም የሚበረታታ ድጋፍ በማድረግ ጉልህ ድርሻ ይወስዳልም ብለዋል።

የወሰን ተሻጋሪ የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት መርሃ ግብር በወጣቶች መካከል የአንድነት ስሜትን፣ የመተሳሰብ ባህልን፣ የሰላም እሴቶችንና የሀገር ፍቅርን በማጠናከር ለትውልድ ግንባታ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከተ መሆኑን አንስተዋል።

በዞኑ በሚገኙ ወረዳዎች እና ከተማ አስተዳደሮች የተሰበሰበው ይህ ሀብት ሲሰበሰብ ወጣት ለወጣት ያለውን ግኑኝነት በማስፋት የመተሳሰብ እሴቶችን ያጠናክርልናል ሲሉ የቤንች ሸኮ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዘማች ኪዳኔ ተናግረዋል።

በዚህ ሀብት ማሰባሰብ የተሳተፉት አስሩን መዋቅር ስድስቱ ወረዳዎች እና አራቱ ከተማ አስተዳደሮች የተሻለ አፈጻጸም በማሳየት በጋራ ማሳካት መቻላቸውን በማንሳት እና ምስጋና በማቅረብ ለክልሉ ከ380ሺ ብር በላይ የሚገመት ቁሳቁስ ማስረከቡን በማንሳት በቀጣይም በጋራ ትልቅ ስራ መስራት እንደሚገባ አንስተዋል።

አክለውም በጎነት ዛሬ ድካም ቢመስልም ነገ ለሀገርና ለህዝብ የሚተርፍ ትልቅ ፍሬ የሚያፈራ እሴት መሆኑን ገልጸው፣ ለዚህ ተልዕኮ መመረጥ እድልና ኃላፊነት መሆኑን ጠቁመዋል።
በሚከተለዉ የሚዲያ አማራጮች ይከታተሉን
📌Tiktok
tiktok.com/
📌Telegram
https://t.me/benchshekozonecommunication

📌 Youtube
https://youtube.com/?si=PUe2-AlSQHCpY1_r

📌 WhatsApp
https://chat.whatsapp.com/IDBp91eytBbL0m0u2rSiSU

የሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር ዋና ማዘጋጃ ቤት የ2018 በጀት ዓመት አፈፃፀም ሪፖርትና የ2019 ዕቅድ ላይ የውይይት መድረክ ተካሄደ።​ የሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር ዋና ማዘጋጃ ቤት የ...
31/08/2026

የሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር ዋና ማዘጋጃ ቤት የ2018 በጀት ዓመት አፈፃፀም ሪፖርትና የ2019 ዕቅድ ላይ የውይይት መድረክ ተካሄደ።

​ የሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር ዋና ማዘጋጃ ቤት የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርትና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ ከተቋሙ ባለሙያዎችና ከባለድርሻ አካላት ጋር የውይይት መድረክ ተካሄደ።

​መድረኩን በንግግር የከፈቱት የሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር ዋና ማዘጋጃ ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ኪዳኔ ንጉሴ የዕቅድ ክለሳ መድረኩ ዋና ዓላማ ባለፈው ዓመት የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራትን ውጤታማነት መገምገም፣ ያጋጠሙ ክፍተቶችን በመለየት ለአዲሱ በጀት ዓመት ስኬት በግብአትነት መጠቀም መሆኑን ገልጸዋል።

ዋና ሥራ አስኪያጁ አክለውም ማዘጋጃ ቤቱ በመሬትና ካዳስተር፣ በመሠረተ ልማት፣ በማዘጋጃ ቤት ገቢ፣ በኮሪደር ልማት፣ በኮንስትራክሽንና ፕላን፣ በከተማ ጽዳትና ውበት፣ በአረንጓዴ ልማት፣ በከተማ ልማታዊ ሴፍትኔት፣ በቄራ አገልግሎት እንዲሁም በሌሎች መዋቅራዊ ዘርፎች ሰፊ ሥራዎችን ማከናወኑና የነበሩ ውስንነቶችን በማረም በቀጣይ የተሻለ ስራ ለመስራት ያለመ መሆኑን ጠቁመዋል።

​በመድረኩ የ2018 በጀት ዓመት አፈፃፀም ሪፖርትን ያቀረቡት የከተማ አስተዳሩ ዋና ማዘጋጃ ቤት ምክትል ሥራ አስኪያጅና የኮንስትራክሽን ዘርፍ ኃላፊ አቶ ወንድሙ አለማየሁ፤ በበጀት ዓመቱ የተከናወኑ የኮሪደር ልማት ሥራዎችን ጨምሮ ሌሎችንም ተግባራት በዝርዝር አቅርበዋል።
በበጀት ዓመቱ ​የቴራዞ ንጣፍ ሥራ 910 ሜትር ርዝመት ያለው የቴራዞ ንጣፍ ሥራ 100 በመቶ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል ያሉት ምክትል ስራ አስኪያጁ ለዚህም ሥራ ጠቅላላ የተጠየቀው በጀት 62,276,869.40 ብር ሲሆን፣ የተከፈለው 57,844,440.18 ብር በመሆን የፋይናንሻል አፈፃፀሙ 93 በመቶ ደርሷል ብለዋል።

በ2018 የበጀት ዓመት ልዩ ትኩረት የተሰጠው ​የስማርት ፖል ተከላ የኮሪደር ልማቱ አካል የሆነው የቴክኖሎጂና የመሠረተ ልማት ማሻሻያ ሥራ ተጠናክሮ መከናወኑ ተመላክቷል።

በዚህም አዲስ የተተከሉ ስማርት ፖሎች 54 ሲሆኑ፣ የተሻሻሉና የታደሱ ስማርት ፖሎች ደግሞ 134 ደርሰዋል የተባለ ሲሆን ለዚህ ማሻሻያ ፕሮጀክት ጠቅላላ በጀት 104,834,542.8 ብር ተመድቦ፣ እስካሁን 62,900,721.98 ብር ክፍያ መፈፀሙና የፕሮጀክቱ ፋይናንሻል አፈፃፀም 60 በመቶ እንዲሁም ፊዚካል አፈፃፀሙ 85 በመቶ ላይ ይገኛል።

​በማዘጋጃ ቤቱ ምክትል ሥራ አስኪያጅና የማስፈጸም ዘርፍ ኃላፊ አቶ ጳውሎስ ማንጁር የቀረበው የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ማዘጋጃ ቤታዊ ገቢን ከፍ በማድረግ የተሟላ መሠረተ ልማት ማሟላት እና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መቅረፍ ላይ ያተኮረ ነው።

ማዘጋጃ ቤቱ በቀጣዩ 2019 በጀት ዓመት 284 ሚሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ ታላቅ ግብ ጥሎ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን አቶ ጳውሎስ ገልጸዋል። ይህንን ግብ ለማሳካት የከተማዋ ነዋሪዎችና ባለድርሻ አካላት ከፍተኛ ርብርብ ማድረግ እንዳለባቸው አሳስበዋል።

በቀጣይ አዲስ የተከፈቱ መንገዶችን በህብረተሰብ ተሳትፎና በመንግሥት ኮረት የማልበስ፣ እንዲሁም የመንገድ ከፈታ ሥራዎችን አጠናክሮ የመቀጠል አቅጣጫ ተቀምጧል።

​በሌላ በኩል የመሬት ልማትና ማኔጅመንት ዘርፍ ኃላፊና ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ ብሩክ ሰለሞን በሰጡት አስተያየት፤ ባለፉት ዓመታት በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ የታዩ ውስንነቶችን በማረም የህዝብን እርካታ ማረጋገጥ ቀዳሚ ትኩረት እንደሚሆን ተናግረዋል።

ከመሬት ጋር የሚነሱ ጥያቄዎች በሕግ ማዕቀፍ በተለይም የሊዝ አዋጁን መሠረት በማድረግ መፍትሔ እንደሚሰጣቸው ገልጸው፣ ከካዳስተር ጋር የተጀመረው ዘመናዊ የሥራ ሂደት አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።

​በውይይት መድረኩ ላይ የተሳተፉት የቀበሌ ማዘጋጃ ቤት ሥራ አስኪያጆችና የዘርፉ ባለሙያዎች ከተማዋን የተሻለች ለማድረግ የሚከተሉትን ዋና ዋና ሃሳቦች እንደ ግብአት አንስተዋል፡

በኢንቨስትመንት ስም ተወስደው ነገር ግን ታጥረውና ሳይለሙ የተቀመጡ ቦታዎችን ወደ መሬት ባንክ በመመለስ ፈጣን የልማት እንቅስቃሴ ውስጥ እንዲገቡ ማድረግ።

ሰነድ አልባ ይዞታዎችን አዋጁ በሚፈቅደው መሠረት ወደ ሕጋዊ ማዕቀፍ ማስገባት፣ እንዲሁም ከከተማ ፕላን ውጪ የተገነቡ መዋቅሮችን በአሰራር ወደ ሕጋዊ መስመር በማምጣት ተጨማሪ የከተማ ገቢ ማመንጨት።

በደረቅ ቆሻሻ አወጋገድ ዙሪያ አዲስ የወጣውን አዋጅ ቁጥር 38/2017 ዓ/ም መሠረት በማድረግ ሕጉን ወደ መሬት ማውረድና ማስፈጸም፣ እንዲሁም ማህበረሰቡን በማስተባበር ቆሻሻን በየፈርጁ የማስወገድ ልማድ ማዳበር።

የህብረተሰብ ተሳትፎን በማጠናከር የአረንጓዴ ልማት ሽፋንን ወደ 3 ሚሊዮን ችግኞች ለማድረስ ታቅዷል። በኮንስትራክሽን ዘርፍም ከተማዋን የሚመጥኑ ደረጃቸውን የጠበቁና ዘመን ተሻጋሪ ህንፃዎችንና መዋቅሮችን መገንባት እንደሚገባ ተመላክቷል።

​ማዘጋጃ ቤቱ በ2019 በጀት ዓመት ከቀበሌዎችና ከባለድርሻ አካላት ጋር ያለውን ቅንጅታዊ አሠራር በማጠናከር የተያዙ ዕቅዶችን ከግብ ለማድረስ በትኩረት ይሰራል ተብሏል።

​በመድረኩ የዋና ማዘጋጃ ቤቱ ዋናና ምክትል ሥራ አስኪያጆች፣ የአራቱ ቀበሌ ማዘጋጃ ቤት ምክትል ሥራ አስኪያጆች፣ የማዘጋጃ ቤቱ ማኔጅመንት አባላት እና የየዘርፉ ባለሙያዎች በንቃት ተሳትፈዋል።ዘገባው የከተማ አስተዳደሩ ኮምንኬሽን ነው።
በሚከተለዉ የሚዲያ አማራጮች ይከታተሉን
📌Tiktok
tiktok.com/
📌Telegram
https://t.me/benchshekozonecommunication

📌 Youtube
https://youtube.com/?si=PUe2-AlSQHCpY1_r

📌 WhatsApp
https://chat.whatsapp.com/IDBp91eytBbL0m0u2rSiSU

ታይላንድ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ስትራቴጂካዊ ግንኙነት ማጠናከር ትፈልጋለችታይላንድ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ስትራቴጂካዊ ትብብር ለማጠናከር እና ከአፍሪካ አህጉር ጋር ያላትን አጋርነት ለማስፋ...
31/08/2026

ታይላንድ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ስትራቴጂካዊ ግንኙነት ማጠናከር ትፈልጋለች

ታይላንድ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ስትራቴጂካዊ ትብብር ለማጠናከር እና ከአፍሪካ አህጉር ጋር ያላትን አጋርነት ለማስፋት ፍላጎት እንዳላት የታይላንድ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሲሃሳክ ፉአንግኬትኪኦ ገለጹ።

የታይላንድ የውጭ ጉዳይ ምክትል ሚኒስትር ሲሃሳክ ፉአንግኬትኪኦ በኢትዮጵያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት አድርገዋል።

ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ አዲስ አበባ በደቡብ ምስራቅ እስያ እና በአፍሪካ መካከል ዋና የትስስር ድልድይ ሆና እየወጣች መሆኗን ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ ከታይላንድ ጋር የቆየ ታሪካዊ ግንኙነት ያላት ሀገር መሆኗን አንስተው፤ ሀገራቸው ይህንን ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር እና ሁለንተናዊ ትብብሯን ለማሳደግ እንደምትሠራ አስታውቀዋል።

በተለይም በኢንዱስትሪ ልማት እና በግብርና ምርቶች ላይ እሴት በመጨመር ረገድ ያላትን መልካም የልማት ተሞክሮ ለኢትዮጵያ ለማካፈል ዝግጁ መሆኗን ገልጸዋል።

የጉብኝታቸው ዋና ዓላማም ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን ታሪካዊ የሁለትዮሽ ግንኙነት ማጠናከር እና መቀመጫነቱ አዲስ አበባ ከሆነው የአፍሪካ ኅብረት ጋር ያለውን ተሳትፎ ማሳደግ እንደሆነ አብራርተዋል።

በዚህም ታይላንድ በአዲስ አበባ ኤምባሲዋን ለመክፈት መወሰኗን ጠቁመዋል፡፡

ሀገራቸው በአፍሪካ ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ተጽዕኖ ለማጠናከር እና አዲስ አበባን የመላው አህጉራዊ ግንኙነቷ ዋና ማዕከል ለማድረግ የምታደርገውን ጥረት የሚያሳይ መሆኑን ጠቅሰዋል።

በተጨማሪም ሀገራቸው ከአፍሪካ ጋር ያላትን የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ እና የልማት አጋርነት ለማሳደግ ያለመውን "የታይላንድ-አፍሪካ ተነሳሽነት" የተሰኘ መርሃ-ግብር በልዩ ትኩረት እየተገበረች እንደምትገኝ ገልጸዋል።

ሚኒስትሩ የአፍሪካ አህጉር ፈጣን ዕድገት በማስመዝገብ ላይ እንደምትገኝ ጠቅሰው፤ አሁን ላይ አፍሪካ በዓለም አቀፍ ደረጃ በደቡቡ የዓለም ክፍል (Global South) ውስጥ ጠንካራ እና ተጽዕኖ ፈጣሪ ድምፅ ሆና መውጣቷን ተናግረዋል።

በአሁኑ ወቅት የደቡቡ የዓለም ክፍል በዓለም አቀፍ መድረክ ያለው ተጽዕኖ እንደሚያመላክት ጠቅሰው፤ የታይላንድ ዋና ዓላማም ከዚሁ እውነታ ጋር የተጣጣመ አህጉራዊ አጋርነት መገንባት መሆኑን ገልጸዋል።

ከነባርና ከአዳዲስ የአፍሪካ ሀገራት ጋር በጋራ በመሥራትም ቀደም ሲል ከተመዘገቡት ስኬቶች በላይ በርካታ የጋራ ውጤቶችን ማስመዝገብ እንደሚቻል እምነታቸውን ተናግረዋል።

አዲስ አበባ የአሴአን (ASEAN) እና የአፍሪካ ዋና የትስስር ማዕከል መሆኗን የጠቆሙት ዲፕሎማቱ፤ ኢትዮጵያና ታይላንድ በአፍሪካ ኅብረትና በአሴአን መካከል ጠንካራ የትብብር ድልድይ በመገንባት ከፍተኛ ሚና መጫወት እንደሚችሉ ገልጸዋል።

በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር በከፍተኛ አመራሮች ደረጃ የሚደረጉ የጋራ ጉብኝቶችና ተደጋጋሚ ውይይቶች ወሳኝ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

ሚኒስትሩ ታይላንድ እና የአፍሪካ ሀገራት ሕግን መሠረት ያደረገውን ዓለም አቀፍ ሥርዓት ለማስጠበቅ፣ ነፃ ንግድን ለማስቀጠል እና በዓለም የንግድ ድርጅት (WTO) ሥር ያለውን የንግድ ሥርዓት ለማጠናከር በጋራ መሥራት እንዳለባቸው አሳስበዋል።

የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባል መሆንም ከዓለም አቀፍ የንግድ ሕጎች እና ኢኮኖሚ ጋር በንቃት እንድትሳተፍ የሚያበረታታ መሆኑን አብራርተዋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።
በሚከተለዉ የሚዲያ አማራጮች ይከታተሉን
📌Tiktok
tiktok.com/
📌Telegram
https://t.me/benchshekozonecommunication

📌 Youtube
https://youtube.com/?si=PUe2-AlSQHCpY1_r

📌 WhatsApp
https://chat.whatsapp.com/IDBp91eytBbL0m0u2rSiSU

መንግሥት ተግባራዊ ባደረገው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፖሊሲ በሀገሪቱ የንግድ ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ ስኬት ተመዝግቧል መንግሥት ተግባራዊ ባደረገው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፖሊሲ በሀገሪቱ የንግ...
31/08/2026

መንግሥት ተግባራዊ ባደረገው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፖሊሲ በሀገሪቱ የንግድ ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ ስኬት ተመዝግቧል

መንግሥት ተግባራዊ ባደረገው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፖሊሲ በሀገሪቱ የንግድ ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ ስኬት ተመዝግቧል አለ የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር፡፡

የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው በኢትዮጵያ የወጪ ንግድ ገቢ ላይ ከፍተኛና ታሪካዊ እድገት እንዲመዘገብ ምክንያት መሆኑ ተገልጿል።

በ2018 በጀት ዓመት ኢትዮጵያ ከወጪ ንግድ 11 ነጥብ 2 ቢሊየን ዶላር ገቢ በማግኘት የዕቅዱን 119 ነጥብ 14 በመቶ ማሳካት መቻሉ ነው የተገለጸው፡፡

በበጀት ዓመቱ መጀመሪያ ላይ ከወጪ ንግድ 9 ነጥብ 40 ቢሊየን ዶላር ገቢ ለማግኘት ታቅዶ የነበረ ቢሆንም፤ አፈጻጸሙ ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር በከፍተኛ ደረጃ ጨምሮ 11 ነጥብ 2 ቢሊየን ዶላር ሆኖ መመዝገቡ ተመላክቷል፡፡

የማዕድን ዘርፍ 5 ነጥብ 07 ቢሊየን ዶላር ገቢ በማስመዝገብ የዕቅዱን 152 ነጥብ 75 በመቶ በማሳካት ቀዳሚውን ስፍራ ይዟል፡፡

በግብርና ምርቶች 3 ነጥብ 83 ቢሊየን ዶላር ገቢ የተገኘ ሲሆን፤ ይህም የዕቅዱን 90 ነጥብ 01 በመቶ መሸፈኑ ተጠቁሟል፡፡

የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ 493 ነጥብ 55 ሚሊየን ዶላር ወይም 93 ነጥብ 80 በመቶ አፈጻጸም አስመዝግቧል፡፡

የኤሌክትሪክና ሌሎች ዘርፎች 425 ነጥብ 45 ሚሊየን ዶላር ገቢ ማስገኘታቸው ነው የተገለጸው፡፡

የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም ከ2017 ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በሁሉም ዘርፎች ላይ ተስፋ ሰጪ ዕድገት አሳይቷል፡፡

የማዕድን ዘርፍ የ2 ነጥብ 1 ቢሊየን ዶላር (71 ነጥብ 18 በመቶ) ከፍተኛ ጭማሪ ሲያሳይ፣ የግብርና ዘርፍ የ238 ነጥብ 24 ሚሊየን ዶላር (6 ነጥብ 64 በመቶ) ዕድገት አስመዝግቧል፡፡

እንዲሁም የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ 45 ነጥብ 68 ሚሊየን ዶላር፣ የኤሌክትሪክና ሌሎች ዘርፎች ደግሞ 115 ነጥብ 41 ሚሊየን ዶላር (37 ነጥብ 22 በመቶ) ጭማሪ ማሳየቱ ተገልጿል።

ለዚህ ታሪካዊ የወጪ ንግድ ገቢ ዕድገት የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ውጤታማ አተገባበር በዋነኝነት የሚጠቀስ ነው፡፡

የገበያ ትስስርና ፖሊሲ፡ ኢትዮጵያ የአፍሪካ ነጻ ንግድ ቀጣና መመሪያን አጽድቃ ተግባራዊ ማድረጓ በአህጉሪቱ ያለውን የገበያ ፍላጎት እንድትጠቀም አስችሏታል፡፡

የምርት ቁጥጥርና ክትትል፡ በህገ-ወጥ የምርት ክምችትና በህገ-ወጥ ኬላዎች ላይ የተደረገው ጥብቅ ቁጥጥር ምርቶች ወደ ውጭ ገበያ እንዲወጡ መንገድ ከፍቷል፡፡

የዋጋ ተመን ክለሳ፡ የማነጻጸሪያ ዋጋ ተመን በየወቅቱ ከዓለም አቀፍ የገበያ ሁኔታ ጋር ተጣጥሞ እንዲከለስ መደረጉ መሆኑ ተነስቷል፡፡

የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ መሻሻል፡ የኢትዮጵያ ምድር ባቡር አገልግሎት በስፋት ስራ መጀመሩና ከጎረቤት ሀገራት ጋር ያለው የምድር ትራንስፖርት አመቺ መሆን የሎጂስቲክስ ወጪን በመቀነስ ለንግዱ መሳለጥ ትልቅ እገዛ ማድረጉን ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡

በአጠቃላይ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው በምርትና ምርታማነት ላይ ያመጣው መነቃቃት ሀገሪቱ ከውጭ ንግድ የምታገኘው የውጭ ምንዛሬ ገቢ እንዲያድግና የንግድ ሚዛኗ እንዲሻሻል መሰረት መጣሉ ተመላክቷል ሲል ኤፍ ኤም ሲ ዘግቧል፡፡

Address

Mizan Aman
Mizan Teferi

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Bench Sheko Zone Communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share