23/08/2021
👉"ነሀሴ 17/2013ዓ.ም "
#በጎፋ ዞን ሣውላ ከተማ ከ7ቱ ወረዳና ከ2ቱ ከተማ አስ/ር ፖሊስ አመራርና አባላት እንድሁም ከሌሎች የፀጥታ መዋቅሮች ጋር በመቀናጀት "ለአገረ እዘምታለሁ!የትም፣መቼም፣በምንም"በሚል መሪ ቃል ጠንካራ ሠላማዊ ሠልፍ መካሄዱ ተገለፀ።
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
=የጎፋ ዞን ፖሊስ መዋቅር አመራሮችና አባላት ፣የማረሚያ ፖሊስ አመራርና አባላት፣ የቀበሌ ሚሊሻዎችና እንድሁም ተቀናሽ የመከላከያ ሠራዊት አባላት በጋራ በመሆን "አገሬን ለማዳን እዘምታለሁ! የትም፣መቼም፣በምንም"በምል መሪ ቃል በዞኑ ርዕሰ ከተማ ሣውላ ጠንከር ያለ ሠለማዊ ሠልፍ መካሄዱን የዞኑ ፖሊስ አዛዥ ም/ኮ/ር ዘላለም ደምሴ ገለፁ።
=አክለውም አዛዡ "የእናት ጡት ነካሽ" የሆነው ጁንታው ለ27ዓመታት በሙሉ በአገርቱ ላይ በፖለቲካው፣በኢኮኖሚውና በማህበራዊ ዘርፎች የመዘበረውና ያቃወሰው እንድሁም በተለይም በሰብዓዊ መብቶች ረገድ የፈፀማቸው ምህረት የለሽ በደሎች ከቁጥር በላይ መሆኑ በታርክ የማይረሳ ጠባሳ እንደሆነም አንስቷል።
=አያይዘውም አዛዡ ጁንታው በዚህ ሁሉ ጥፋቱ ሳይፀፀትና ሳይማር የአገር አለንታና ደጀን በሆኑ ጀግና ሠራዊቶችና በንፁሃን ዜጎች ላይ እንድሁም በንብረታቸው ላይ ጭምር በተደጋጋሚ ጊዜ የክህደት ወንጀል እየፈፀመ ወራትን እያስቆጠረ ያለ ባንዳ ቡድን መሆኑንም አንስተዋል።
=አክለውም አዛዡ በጁንታው የአገር ክህደት ተግባር መላው የፀጥታ መዋቅሮች በመማረራቸው ምክንያት ለአገር መከላከያ ሠራዊት ያላቸውን ፍቅር ለመግለጽ ከወር ደመወዛቸው በ12ወር ተቆርጦ የምያልቅ የገንዘብ ድጋፍ በሞራል እያደረጉ መቀጠላቸውን ጠቅሰዋል።
=ይህ በእንዲህ እንዳለ አገራችንን ከጁንታውና ከኦነግ ሺኔ እንድሁም ከምዕራባዊያን ጣልቃ ገብነት ለማዳን ከጀግናው የአገር መከላከያ ሠራዊት ጎን እንቆማለን፣ከመንግሥት ጥሪ ስቀርብም እንዘምታለን! በሚል ወኔ መላው የዞናችን የፀጥታ ሃይል በአደባባይ ላይ በነቅስ በመውጣት ሠላማዊ ሠልፍ እንደተካሄደም በሰጡት መግለጫ አሳስበዋል።
=በዚህም የጀግንነት ሠለማዊ ሠልፍ ላይ መፈክራቸውን በመያዝ የተገኙ ሠራዊቶች "አገር ስትኖር መኖራችን ይረጋገጣል!ስለሆነም ለአገራችን በጀግንነት እንሰዋለ"አንላቀቅም በማለት ቁጭት በተሞላበት መንገድ ድምፃቸውን በአንድነት አሰምተዋል።
=ስለዚህም አሉ አዛዡ መላው የአካባቢያችን ህዝቦች እስከአሁን ላደረጋችሁት የፀጥታ ትብብር አመስግነው" በመቀጠልም ወጣቶች፣አዛውንቶች፣የአገርና የኃይማኖት ሽማግሌዎች እንድሁም መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅት መሪዎች በያላችሁበት ቦታ ከሚገኙ የፀጥታ መዋቅሮች ጋር በመቀናጀት ለአካባቢያችሁ የሠላም ዘብ በመቆም የዜግነት ግዴታቸውን እንድወጡ ሲሉም ጥር አስተላልፈዋል።
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
🇪🇹ኢትዮጵያን ለማዳን እዘምታለሁ!የትም፣መቼም፣በምንም🇪🇹
👉ም/ኢ/ር ደሳለኝ ጩቱሎ/ዘጋቢ/