Waajjira Fayyaa A/J/Dhummuugaa የጅሌ ጥሙጋ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት

  • Home
  • Waajjira Fayyaa A/J/Dhummuugaa የጅሌ ጥሙጋ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት

Waajjira Fayyaa A/J/Dhummuugaa
የጅሌ ጥሙጋ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Waajjira Fayyaa A/J/Dhummuugaa
የጅሌ ጥሙጋ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት, Government Organization, .

This is the official page of the Jile Timuga Woreda Health Office,
Jile Timuga Woreda Health Office responsible for Jile Timuga Woreda's people Health.

በጅሌ ጥሙጋ ወረዳ በእሳት አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው 17 የቤተሰብ አባላት ድጋፍ ተደረገ---------------------------ሰንበቴ: ነሐሴ 21/2018 ዓ.ም(ጅሌ ጥሙጋ ወረዳ ጤና ፅ/...
27/08/2026

በጅሌ ጥሙጋ ወረዳ በእሳት አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው 17 የቤተሰብ አባላት ድጋፍ ተደረገ
---------------------------
ሰንበቴ: ነሐሴ 21/2018 ዓ.ም(ጅሌ ጥሙጋ ወረዳ ጤና ፅ/ቤት)

​የጅሌ ጥሙጋ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት የ2018 ዓ.ም የበጎ ፈቃድ አገልግሎትን ምክንያት በማድረግ በሉጎ ቀበሌ በሦስት አባዎራዎች ላይ በደረሰ የእሳት አደጋ ለችግር ለተጋለጡ ወገኖች ምግብ እና ምግብ ነክ ያልሆኑ ቁሳቁሶች እና የገንዘብ ድጋፍ በዛሬው እለት አድርጓል።

​በደረሰው የእሳት አደጋ የሶስት አባወራዎች መኖሪያ ቤት ንብረታቸውን ጨምሮ ሙሉ በሙሉ የወደመ ሲሆን በጠቅላላው 17 የቤተሰብ አባላት ለከፍተኛ ችግር መዳረጋቸው ተገልጿል።የደረሰውን አደጋ ተከትሎ የወረዳው ጤና ጽ/ቤት ኃላፊዎች እና ባለሙያዎች በቦታው በመገኘት አደጋ ለደረሰባቸው ወገኖች አስፈላጊውን ድጋፍ አድርገዋል።

​ጽ/ቤቱ በወረዳው የሚገኙ አራት ጤና ጣቢያዎችን በማስተባበር ለምግብነት የሚውሉ ሩዝ፣ ዱቄት እና ዘይት እንዲሁም የህፃናት እና የአዋቂዎች አልባሳት፣ የንጾህና መጠበቂያ የልብስ እና የገላ ሳሙናዎች፣ የውኃ ጀሪካኖች እና የጥሬ ገንዘብ ድጋፍ ነው ያደረገው።ከዚህ በተጨማሪም ተጎጂዎቹ በሉጎ ጤና ጣቢያ ሙሉ ነፃ የሕክምና አገልግሎት እንዲያገኙ ማመቻቸቱንም ጽ/ቤቱ ገልጿል።

​የወረዳው ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አህመድ ኡመር በድጋፍ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ተገኝተው እንደተናገሩት ዛሬ እዚህ የተገኘነው ለቁሳቁስ ድጋፍ ብቻ ሳይሆን ከጎናችሁ መሆናችንን ለመግለጽ ነው በማለት ተናግረዋል።በቀጣይም እንደ ወረዳ ተጨማሪ ድጋፍ ለማድረግ ጥረት እናደርጋለን ብለዋል።

በእሳት አደጋው ጉዳት የደረሰባቸው የቤተሰብ ተወካይ በበኩላቸው በደረሰባቸው ድገተኛ አደጋ መጠለያ እና ንብረታቸውን አጥተው በተጨነቁበት ሰዓት ጤና ጽ/ቤት ባደረገላቸው የቁሳቁስ፣ የገንዘብ እና የነፃ ሕክምና ድጋፍ ትልቅ ደስታ እንደተሰማቸው በመግለጽ ከጎናችን ስለቆማችሁ እናመሰግናለን ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

በዚሁ የድጋፍ መርሃ-ግብር ላይ የጽ/ቤቱን ኃላፊ አቶ አህመድ ኡመርን ጨምሮ የጽ/ቤቱ ምክትል ኃላፊ ወ/ሮ አፍራህ ሰይድ፣ የጽ/ቤቱ ኦፊሰሮች እና የአራቱም ጤና ጣቢያ ተወካዮች በቦታው በአካል ተገኝተው ለተጎጅዎች ድጋፉን አበርክተዋል።

መረጃ:ከጅሌ ጥሙጋ ወረዳ ጤና ፅ/ቤት ከሚድያ ክፍል የተገኘ

Buufata Fayyaa Baxxetti koreen WaSH FIT marii gaggeesse.Hagayya 18, 2018 (W/Fayyaa A/J/Dhummuuga)Buufanni Fayyaa Baxxee ...
24/08/2026

Buufata Fayyaa Baxxetti koreen WaSH FIT marii gaggeesse.

Hagayya 18, 2018 (W/Fayyaa A/J/Dhummuuga)

Buufanni Fayyaa Baxxee guyyaa har'aa Koree WaSH FIT Waliin marii Waloo hojiiwwan bara 2018 keessa hojjatamanii fi karoora bara 2019 fi kurmaana tokkoffaa keessa hojiiwwan hojjatamuu qaban irratto marii bal'aa bakka itti gaafatamaan buufata Fayyaa Baxxee obbo Alii Adam argamanitti gaggeessanii joru.

በአማራ ክልል በኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር  "አንድ ደርዘን ደብተር ለአንድ ተማሪ" መርሃ ግብር  ተጠናክሮ ቀጥሏል።በዛሬው እለት የኦሮሞ ዞን ጤና መምሪያ  ኅላፊ አቶ ኡስማን አሊ  ለኦሮሞ ...
19/08/2026

በአማራ ክልል በኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር "አንድ ደርዘን ደብተር ለአንድ ተማሪ" መርሃ ግብር ተጠናክሮ ቀጥሏል።

በዛሬው እለት የኦሮሞ ዞን ጤና መምሪያ ኅላፊ አቶ ኡስማን አሊ ለኦሮሞ ዞን ትምህርት መምሪያ ኀላፊ ለአቶ አሊ ተፈራ ደብተር ፣ እስኪርቢቶ እና ሌሎች የትምህርት ቁሳቁሶችን አቅም ለሌላቸው ተማሪወች እንድሆን ድጋፍ አድርገዋል።

እንኳን ደስ አላችሁ‼️የኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን ጤና መምሪያ በዓመታዊ የግምገማ መድረክ የላቀ አፈጻጸም በማስመዝገብ የእውቅና ሰርተፊኬት ተሸለመ፦🏆🏆🏆🎖🎖🎖የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት (አብክ...
17/08/2026

እንኳን ደስ አላችሁ‼️

የኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን ጤና መምሪያ በዓመታዊ የግምገማ መድረክ የላቀ አፈጻጸም በማስመዝገብ የእውቅና ሰርተፊኬት ተሸለመ፦
🏆🏆🏆🎖🎖🎖
የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት (አብክመ) ጤና ቢሮ የበሽታ መከላከልና መቆጣጠር ኬዝ ቲም ባካሄደው የ2018 በጀት ዓመት ዓመታዊ የሥራ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ፣ የኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን ጤና መምሪያ በበርካታ የጤና ፕሮግራሞች የተሻለ አፈጻጸም በማስመዝገብ የእውቅና ባለቤት ሆኗል።
መምሪያው በግምገማ መድረኩ በሦስት ዋና ዋና የጤና ዘርፎች ባሳየው የላቀ የሥራ እንቅስቃሴ የደረጃና የእውቅና ሽልማቶችን አግኝቷል፡
* በዘርፈ-ብዙ (Multisectoral) ፕሮግራም፡ 3ኛ ደረጃ
* በቲቢ (TB) መከላከልና መቆጣጠር ፕሮግራም፡ 2ኛ ደረጃ
* በወባ (Malaria) መከላከልና መቆጣጠር ፕሮግራም፡ 2ኛ ደረጃ
ይህ የተገኘው ውጤት በመምሪያው፣ በጤና ባለሙያዎችና በሕብረተሰቡ የተቀናጀ ጥረት የተመዘገበ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፣ በቀጣይም የጤና አገልግሎት ተደራሽነትንና ጥራትን አጠናክሮ ለማስቀጠል መነሻ እንደሚሆን ተመልክቷል።

የማህበረሰብ እና በሁኔታዎች ላይ የተመሰረተ የህብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቅኝት እና አሰሳ(CEBS) ስልጠና መስጠት ተጀመረ---------------------------------ሰንበቴ:ነሐሴ 09...
15/08/2026

የማህበረሰብ እና በሁኔታዎች ላይ የተመሰረተ የህብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቅኝት እና አሰሳ(CEBS) ስልጠና መስጠት ተጀመረ
---------------------------------
ሰንበቴ:ነሐሴ 09/2018 ዓ.ም
(ጅሌ ጥሙጋ ወረዳ ጤና ፅ/ቤት)

የማህበረሰብ እና በሁኔታዎች ላይ የተመሰረተ የህብረተሰብ ጤና አደጋዎች የበሽታዎች ቅኝት እና አሰሳ(CEBS) ስልጠና ለቀበሌ ሴቶች ህብረት/VHL/መስጠት ተጀመረ።

በዛሬው እለት ከማህበረሰቡ የተመረጡ የቀበሌ ሴቶች ህብረት/VHL/አባላት በሰንበቴ ክላስተር መረዋ እና እዝግዬ እንድሁም በበጤ ክላስተር በበጤ ከተማ ፤በጎዳ፤በጎሮ ድሬ በደና፤በባልጪ፤በጥቁሬ ጎሮ ወዳዎ፤በወሰንቁርቁር እንድሁም በገርቢ ክላስተር ጤና ጣቢያ በገርቢ ድሬ ገልማ ቀበሌዎች በሁኔታዎች ላይ የተመሰረተ የህብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቅኝት እና አሰሳ ስልጠና መውሰድ ጀምረዋል።
ሰልጣኝ የሴቶች ህብረት/VHL/አባላት ከስልጠና ቡኀላ በቀበሌያቸው በየጎጣቸው በህብረተሰቡ የጤና አደጋዎችን መለየት፤ለሚመለአተው የጤና ተቋም ርፖርት በማድረግ ፤በህብረተሰቡ ውስጥ ንቁ ተሳትፎ በማድረግ ጠንካራ የበሽታ ቅኝት እና አሰሳ ስራን ለመፍጠር ነው።
በወረዳው የማህበረሰብ እና በሁኔታዎች ላይ የተመሰረተ የህብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቅኝት እና አሰሳ/CEBS/ስልጠና ሰሞኑን ለጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች መሰጠቱ ይታወቃል።በቀጣይ ቀናት ስልጠናው በተለያዩ የወረዳው ቀበሌዎች ላይ የሚሰጥ ይሆናል።

መረጃ፦ከጅሌ ጥሙጋ ወረዳ ጤና ፅ/ቤት ከሚድያ ክፍል የተገኘ።

የጅሌ ጥሙጋ ወረዳ ጤና ፅ/ቤት የ2019 ዓ.ም የ1ኛ ሩብ ዓመት  የ1ወር የጤና ፕሮግራም ዕቅድ  አፈፃጸም ግምገማ አካሄደ።ሰንበቴ:- ነሐሴ 06/2018 ዓ.ም(ጅሌ ጥሙጋ ወረዳ ጤና ፅ/ቤት)...
12/08/2026

የጅሌ ጥሙጋ ወረዳ ጤና ፅ/ቤት የ2019 ዓ.ም የ1ኛ ሩብ ዓመት የ1ወር የጤና ፕሮግራም ዕቅድ አፈፃጸም ግምገማ አካሄደ።
ሰንበቴ:- ነሐሴ 06/2018 ዓ.ም
(ጅሌ ጥሙጋ ወረዳ ጤና ፅ/ቤት)

የጅሌ ጥሙጋ ወረዳ ጤና ፅ/ቤት የ2019 ዓ.ም በጀት አመት የ1ኛ ሩብ አመት አፈፃጸም የሀምሌ ወር የጤና ፕሮግራማቲክ /PMT/ግምገማ አካሄዷል።
የእቅድ አፈፃጸሙን የጅሌ ጥሙጋ ወረዳ ጤና ፅ/ቤት የፕላን ዝግጅት ኬዝ ቲም አስተባባሪ በአቶ ወንደሰን ወ/የስ የቀረበ ስሆን ሪፖርቱ ከቀረበ ቡኀላ የጅሌ ጥሙጋ ወረዳ ጤና ፅ/ቤት ም/ኀላፊ አፍራ ሰይድ መድረኩን በመምራት በሀምሌ ወር እቅድ አፈፃጸም በሁሉም የጤና ፕሮግራም የተሻለ አፈፃጸም የተመዘገበ ስሆን በቀጣይ ወር በሁሉም ፕሮግራሞች መስተካከል ያለባቸው ነጥቦች ተለይተው ለሁሉም ክላስተር ጤና ጣቢያ ግብረ-መልስ በመስጠት እና ጠንካራ ተቋማዊ ድጋፍ ማድረግ እንዳለበት አቅጣጫ በማስቀመጥ የዛሬ መድረክ ተጠናቋል።

መረጃ :-ከጅሌ ጥሙጋ ወረዳ ጤና ፅ/ቤት ከሚድያ ክፍል የተገኘ ነው

የአማራ ክልል ጤና ቢሮ የመድሀኒትና የሕክምና መሣሪያዎች አስተዳደር  ዳይሬክቶሬት ከነሀሴ 5_6 ቀን 2018 ዓ.ም በኮምቦልቻ ከተማ ሲያካሂድ የነበረውን የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም...
12/08/2026

የአማራ ክልል ጤና ቢሮ የመድሀኒትና የሕክምና መሣሪያዎች አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ከነሀሴ 5_6 ቀን 2018 ዓ.ም በኮምቦልቻ ከተማ ሲያካሂድ የነበረውን የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማና የ2019 ዕቅድ ትውውቅ አጠናቀቀ።

‎ በማጠቃለያ መርሃ ግብሩ ላይ በምስራቅ አማራ ክላስተር የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ የዞን ጤና መምሪያዎች እና ሆስፒታሎች የዕውቅና እና የምስጋና የምስክር ወረቀት ተበርክቷል።

በዚህም መሰረት:-ከክላስተሩ ሆስፒታሎች
1. ቦሩ ሜዳ ጠቅላላ ሆስታል 5ኛ ደረጃ
2.ደብረ ሲና የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል፥ወግዲ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል፥ወልድያ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በተመሳሳይ ውጤት 4ኛ ደረጃ
3. አማራ ሳይንት የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል፥ደብረ ብርሃን አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል፥መካነ ሰላም ጠቅላላ ሆስፒታል በተመሳሳይ ውጤት 3ኛ ደረጃ
4. አቃስታ ጠቅላላ ሆስፒታል 2ኛ ደረጃ
5. ዋድላ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል 1ኛ ደረጃ የወጡ ሲሆን
ከዞን ጤና መምሪያዎች ደግሞ
1. አሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ጤና መምሪያ እና ሰሜን ሸዋ ዞን ጤና መምሪያ በተመሳሳይ ውጤት 3ኛ ደረጃ
2. ሰሜን ወሎና ደቡብ ወሎ ዞን ጤና መምሪያ በተመሳሳይ ውጤት 2ኛ ደረጃ የወጡ ሲሆን
ከከተማ አስተዳደር ጤና መምሪያ ደግሞ
1.ወልድያ ከተማ አስተዳደር ጤና መምሪያ 2ኛ ደረጃ
2. ደሴ ከተማ አስተዳደር ጤና መምሪያ 1ኛ ደረጃ በመያዝ የዕውቅና የምስክር ወረቀት ከቢሮው ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ አበበ ተምትሜ እጅ ተቀብለዋል።
ነሀሴ 6/2018 ዓ.ም

Address


Telephone

+251331180059

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Waajjira Fayyaa A/J/Dhummuugaa የጅሌ ጥሙጋ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Waajjira Fayyaa A/J/Dhummuugaa የጅሌ ጥሙጋ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት:

Shortcuts

  • Want your organization to be the top-listed Government Service?

Share