06/09/2026
የእምርታ ቀንን ምክንያት በማድረግ በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ላይ የልምድ ልውውጥ ተካሄደ
--------------------------------
ሰንበቴ:ጿጉሜ 01/2018 ዓ.ም(ጅሌ ጥሙጋ ኮሙኒኬሽን)
በጅሌ ጥሙጋ ወረዳ መሰዋ ሀደሬ ቀበሌ ሀደሬ ጎጥ ልዮ ቦታ ካሂማ ጳጉሜ 1 አገር አቀፍ የእምርታ ቀንን ምክንያት በማድረግ የሙዝ እና የተለያዮ አትክልት ልማት ላይ ልምድ ልውውጥ መርሃ ግብር ተካሄዷል።
መርሃ ግብሩ በ«ሆርቲላይፍ» (HortiLife) ፕሮግራም ድጋፍ በሞዴል አርሶ አደሮች መሬት ላይ የተካሄደ የሙዝ እና አትክልት ልማት ልምድ ልውውጥ ነው።
በልምድ ልውውጡ የወረዳ እና ቀበሌ አመራሮች፣ የግብርና ባለሙያዎች እንዲሁም አርሶ አደሮች በመገኘት የሙዝ ልማት የተግባር አፈፃፀም፣ የተሻሻሉ የግብርና ቴክኖሎጂዎች አጠቃቀም እና ምርታማነትን ማሳደጊያ ዘዴዎች ላይ ልምድ እንዲወስዱ ተደርጓል።
በዚህም የልምድ ልውውጥ መድረኩ አርሶ አደሮች ከትናንሽ መሬት የተሻለ የኢኮኖሚ ጥቅም ማግኘት እንደሚችሉ እንዲሁም ምርታማነትን ማሳደግ እና የገቢ ምንጫቸውን ማስፋት የሚችሉበትን ዕድል እንዲገነዘቡ ትልቅ አስተዋጽኦ አድርጓል።
በተያያዘም ከመድረኩ የተገኘውን መልካም ልምድ ወደ ሌሎች ቀበሌዎች ማስፋፋት፣ የሙዝ እና የአትክልት ክላስተር ልማትን ማጠናከር እና ቀጣይነት ያለው የቴክኒክ ድጋፍ እና ክትትልን ማጠናከር እንደሚገባ አቅጣጫዎች ተቀምጧል።