29/08/2026
የወላይታ ዞን ወጣቶች ጉዳይና በጎ ፈቃድ አገልግሎት ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ከዞኑ ወጣቶች አደረጃጀት ጋር በመሆን ለአንድ አቅም ደካማ ቤተሰብ የቤት ግንባታ አስጀመረ
ወላይታ ሶዶ፤ ነሐሴ 23/ /2018 ዓ.ም የወላይታ ዞን ወጣቶች ጉዳይና በጎ ፈቃድ አገልግሎት ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ከዞኑ ወጣቶች አደረጃጀት ጋር በመሆን በወላይታ ዞን ሶዶ ዙሪያ ወረዳ ቶሜ ከተማ "በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ!" በሚል መሪ ቃል የክረምት ወራት የወጣቶች በጎ ፍቃድ አካል የሆነው ለአንድ አቅም ደካማ ቤተሰብ የቤት ግንባታ አስጀምሯል።
የወላይታ ዞን ወጣቶች ጉዳይና በጎ ፈቃድ አገለግሎት ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ታምራት ከበደ ይህ ተግባር ተጀመረ ብለን የሚናቆመው ሳይሆን እሰከ መጨረሻው ድረስ ተጠናቅቆ አገለግሎት መስጠት እንዳለበት አሳስበዋል።
የክረምት በጎ የሚሰሩ ቤቶች በብሎኬት የሚሠራው ከጊዜ አንፃርም ቶሎ ተገንብቶ ተጠናቅቆ አገለግሎት እንዲሰጥና ዘለቀታ ያለው ዕድሜ እንዲኖርም ታስቦ እንደሆነም ገልፀዋል።
የሶዶ ዙሪያ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊና የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ ወንድሙ ታከለ የጎነት የኢትዮጵያ ከፍታ በሚል መሪ ቃል እየተሠራ በሶዶ ዙሪያ ወረዳ በግንባታም በጥገናም በርካታ ቤቶች እየተገነቡ እንደሚገኙ በመጥቀስ ሌሎችም በርካታ በጎ ሥራዎች እየተከናወኑ እንዳሉ አሳስበዋል።
የክረምት በጎ ሥራው አንድ ጊዜ ብቻ ተሠርቶ የሚቆም ሳይሆን የሁል ጊዜ ተግባር ቀጣይነት ባለው መንገድ የሚሠራ መሆኑን ተገልጿል።