ሲሳይ ደገፉ / Sisay degefu

ሲሳይ ደገፉ / Sisay degefu Private

የሰሜን ለንደኑ ክለብ "ዘ ኢንቪንስብል" (የማይበገሩት) የፕሪሚየር ሊጉ የወርቅ ዋንጫ ባለቤት አርሰናል በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ38 ጨዋታዎች ውድድር አንድም ጨዋታ ሳይሸነፍ የወርቅ ዋንጫ...
15/05/2026

የሰሜን ለንደኑ ክለብ "ዘ ኢንቪንስብል" (የማይበገሩት) የፕሪሚየር ሊጉ የወርቅ ዋንጫ ባለቤት አርሰናል በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ38 ጨዋታዎች ውድድር አንድም ጨዋታ ሳይሸነፍ የወርቅ ዋንጫ ባለቤት መሆን የቻለ ብቸኛ ክለብ ነው በመባል ይህን ደማቅ ታሪክ የጻፈው ከ22 ዓመታት በፊት ልክ በዛሬዋ ዕለት ነበር።

04/05/2026
ማሽነሪው፦ የከተማው ዘላቂ ሀብትየሎደር ግዥ መፈጸም ማለት አንድ ማሽን መግዛት ብቻ አይደለም፤ ይልቁንም፦1. የኪራይ ወጪን ማስቀረት፦ ከዚህ ቀደም ለልማት ስራዎች ይወጣ የነበረውን ከፍተኛ የ...
03/05/2026

ማሽነሪው፦ የከተማው ዘላቂ ሀብት

የሎደር ግዥ መፈጸም ማለት አንድ ማሽን መግዛት ብቻ አይደለም፤ ይልቁንም፦

1. የኪራይ ወጪን ማስቀረት፦ ከዚህ ቀደም ለልማት ስራዎች ይወጣ የነበረውን ከፍተኛ የኪራይ ወጪ በማስቀረት የከተማውን ሀብት መቆጠብ ያስችላል።

2. ፈጣን ምላሽ መስጠት፦ የመንገድ መዘጋት፣ የጎርፍ አደጋ ወይም አዳዲስ የልማት ስራዎች ሲመጡ በሰው እጅና በኪራይ ይጠበቅ የነበረውን ጊዜ ያሳጥራል።

3. ለቀጣይ ትውልድ የሚተርፍ ቅርስ፦ ማሽኑ ለብዙ ዓመታት የከተማው ንብረት ሆኖ በማገልገል የከተማውን የልማት አቅም (Capacity) በከፍተኛ ደረጃ ያሳድገዋል።

እውነተኛ አመራር የሚፈተነው ነገሮች በተመቻቹበት ጊዜ ሳይሆን፣ ሁኔታዎች አስቸጋሪ ሲሆኑ ነው። አሁን ባለው ዓለም አቀፍና ሀገራዊ የኢኮኖሚ ጫና ውስጥ እንዲህ ያለ ትልቅ የልማት መሣሪያ መግዛት ከዛሬው ችግር በላይ የነገው ተስፋ ይታያል። ይህ ውሳኔ አመራሩ ለከተማው ህዝብ የልማት ጥያቄ የሰጠው ትልቅ ዋጋ ማሳያ ነው።

በችግር ውስጥ ትልቅ ነገር መስራት ወይም መሰረት መጣል

👉 Sintayewu Tumato

የናፍታ ነዳጅ አቅርቦት መጠን ከጦርነቱ በፊት ወደነበረበት እንዲመለስ ተወሰነ ሚያዚያ 21፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ናፍታ ነዳጅ ከመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት በፊት ወደነበረበት የአቅርቦት መጠ...
29/04/2026

የናፍታ ነዳጅ አቅርቦት መጠን ከጦርነቱ በፊት ወደነበረበት እንዲመለስ ተወሰነ

ሚያዚያ 21፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ናፍታ ነዳጅ ከመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት በፊት ወደነበረበት የአቅርቦት መጠን እንዲመለስ ተወስኗል አሉ የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ።

አቶ አሕመድ ሽዴ በሰጡት መግለጫ ፥ በአሁኑ ወቅት ያለውን የምርትና የትራንስፖርት እንቅስቃሴ በማየት የናፍታ አቅርቦት ወደነበረበት እንዲመለስ መንግሥት ወስኗል ብለዋል።

በጦርነቱ ምክንያት የናፍታ አቅርቦት በግማሽ ቀንሶ እንደነበር ገልጸው ፥ በዚህም በቀን 4 ነጥብ 5 ሚሊየን ሊትር እንዲቀርብ እየተደረገ ነበር ብለዋል።

አሁን ላይ ግን ከጦርነቱ በፊት ይቀርብ የነበረው በቀን 9 ሚሊየን ሊትር ናፍታ እንዲገባ ተወስኗል ነው ያሉት።

ለዚህም መንግሥት ተጨማሪ 20 ቢሊየን ብር በወር ለነዳጅ ድጎማ እንደሚያደርግ አስገንዝበዋል።

ናፍታው ከጅቡቲ ወደ አዲስአበባ መጓጓዝ ጀምሯል ያሉት ሚኒስትሩ፥አጠቃላይ የነዳጅ ድጎማም ከ300 ቢሊየን ብር ማለፉን ጠቁመዋል።

ቤንዚን እና የአውሮላን ነዳጅ ከጦርነቱ በፊት በነበረው ልክ እየቀረበ እንደሆነ አንስተዋል።

ለአዲስ አበባ ከዛሬ ጀምሮ ለክልሎች ደግሞ ከነገ ጀምሮ ከጅቡቲ ናፍታ የማጓጓዝ ሥራ እንደሚከናወንም ሚኒስትሩ አጽንኦት ሰጥተዋል።

በዙፋን ካሳሁን

በአርሲ እየተካሄደ ያለውን ፀረ ኦርቶዶክስ ዘመቻን በፅኑ እቃወማለሁ ።መንግስት የዜጎችን ደህንነት ማረጋገጥ እና አጥፊዎችን የመቅጣት ሀላፊነቱን መወጣት ይገባል ❗️❗️
03/03/2026

በአርሲ እየተካሄደ ያለውን ፀረ ኦርቶዶክስ ዘመቻን በፅኑ እቃወማለሁ ።
መንግስት የዜጎችን ደህንነት ማረጋገጥ እና አጥፊዎችን የመቅጣት ሀላፊነቱን መወጣት ይገባል ❗️❗️

ከዛሬ አመሻሽ ጀምሮ በሥራ ላይ የሚውል የነዳጅ ምርቶች ችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ይፋ ተደረገአዳስ አበባ ታኅሣሥ 29/2017 (ንቀትሚ) የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ከዛሬ ታህሳስ 29/2017...
07/01/2025

ከዛሬ አመሻሽ ጀምሮ በሥራ ላይ የሚውል የነዳጅ ምርቶች ችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ይፋ ተደረገ

አዳስ አበባ ታኅሣሥ 29/2017 (ንቀትሚ) የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ከዛሬ ታህሳስ 29/2017 ዓ.ም አመሻሽ ጀምሮ በሥራ ላይ የሚውል የነዳጅ ምርቶች ችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ይፋ አድርጓል።

ሚኒስትር መስሪያ ቤቱ የነዳጅ ምርቶችን ችርቻሮ ዋጋ መሸጫ ዋጋ ይፋ የሆነው በየወሩ እየተከለሰ በስራ ላይ እንዲውል በሚኒስቴሮች ምክር ቤት ውሳኔ በተሰጠው ኃላፊነት ሠረረት ነው።

በዚህም ከዛሬ ታኅሣሥ 29 ቀን 2017 ዓ.ም ምሽት 12 ሰዓት ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ ተግባራዊ የሚደረግ የነዳጅ ምርቶች ችርቻሮ መሸጫ ዋጋን ይፋ አድርጓል።

በዚህም መሠረት አንድ ሊትር የነዳጅ ምርት ችርቻሮ ዋጋ በብር ሲገበያይ እንደነዳጁ አይነት በሚከተለው መልኩ እንዲሆን መወሰኑን ገልጿል።

አንድ ሊትር ቤንዚን በብር 101.47፣ ናፍጣ በብር 98.98፣ ኬሮሲን በብር 98.98፣ የአውሮፕላን ነዳጅ በብር 109.56፣ የከባድ ጥቁር ናፍጣ በብር 105.97 እንዲሁም የቀላል ጥቁር ናፍጣ በብር 108.30 እንዲሸጥ ተወስኗል።

የነዳጅ ማደያዎችም ህጉን አክብረው ህብረተሰቡን በቅንነትና በታማኝነት እንዲያገለግሉ ሚኒስት መስሪያ ቤቱ መልዕክቱን ያስተላልፋል።

Address

Wolaita
S**o
LULSEGED

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ሲሳይ ደገፉ / Sisay degefu posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share

Category