Wolaita Sodo Agricultural College

Wolaita Sodo Agricultural College Home of Agricultural Vocations!

Soddo ATVET College
Situated in Southern Nations Nationalities and People’s Region (SNNPR)
Established in 1972 by Wolaita Agricultural Development Unit (WADU)

Soddo became an ATVET college in 2002

: Crop Production, Livestock Production, Natural Resources, Small Scale Irrigation, Artificial Insemination, & Basic and Supportive Sciences Department By Regular as we

ll as Continues Education Program (CEP)



Striving to see farmers/pastoralists who can contribute to agriculture led industry development apart from food self-sufficiency in the region through strong vocational education and training.



Producing well trained experts in terms of theoretical & practical aspects in modern agriculture, sugar cane crop production, and sugar and ethanol production in order to boost production and productivity, conserve and properly utilize natural resources, produce quality products intended for the industry and for the export market thereby improving the livelihoods of farmers/pastoralists.

ኮሌጃችን የቨርሚ ኮምፖስት ምርት ሽያጭ አጠናክሮ እየቀጠለ ነው።ወ/ሶ/ግ/ኮ ግንቦት 19/2018 ዓ/ም ኮሌጃችን በያዝነው 2018 በጀት ዓመት ዘርፈ-ብዙ ጠቀሜታ ያለውን የቨርሚ ኮምፖስት በስ...
27/05/2026

ኮሌጃችን የቨርሚ ኮምፖስት ምርት ሽያጭ አጠናክሮ እየቀጠለ ነው።

ወ/ሶ/ግ/ኮ ግንቦት 19/2018 ዓ/ም

ኮሌጃችን በያዝነው 2018 በጀት ዓመት ዘርፈ-ብዙ ጠቀሜታ ያለውን የቨርሚ ኮምፖስት በስፋት እያመረተ ነው።

ኮሌጃችን ከወርልድ ቪዥን ኢትዮጵያ ጋር በገባው ውል መሠረት 90 ኩንታል የቨርሚ ኮምፖስት ጠጣር ምርት ሽያጭ በተመጣጣኝ ዋጋ አካሂዷል።

ከዚህ ቀደም ኮሌጃችን ለድርጅቱ፣ለሌሎች መንግስታዊና መንግስታዊ ላልሆኑ ተቋማትና የሕብረተሰብ ክፍሎች የቨርሚ ኮምፖስት ጠጣርና ፈሳሽ ምርት ሽያጭ በስፋት ማካሄዱ ይታወሳል።

የኮሌጃችን ዲን ዶ/ር አሉላ ታፈሰ 1,447ኛውን የኢድ አል አድሃ (አረፋ) በዓል አስመልክተው ለእስልምና ዕምነት ተከታዮች ያስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት፦የእስልምና ዕምነት ተከታ...
26/05/2026

የኮሌጃችን ዲን ዶ/ር አሉላ ታፈሰ 1,447ኛውን የኢድ አል አድሃ (አረፋ) በዓል አስመልክተው ለእስልምና ዕምነት ተከታዮች ያስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት፦

የእስልምና ዕምነት ተከታይ የሆናችሁ የኮሌጃችን አካዳሚክ ኮሚሽንና ማኔጅመንት ኮሚቴ አባላት፣ መምህራን፣ አስተዳደር ሠራተኞች፣ ተማሪዎችና ባለድርሻ አካላት በሙሉ እንኳን ለ1,447ኛው የኢድ አል አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ/አደረሰን!

ይህ በዓል ነቢዩ ኢብራሂም ለፈጣሪያቸው ያሳዩትን ፍጹም ታዛዥነትና መስዋዕትነት በማሰብ በእስልምና ዕምነት ተከታዮች ዘንድ በድምቀት የሚከበር ታላቅ በዓል ነው።

በዓሉን በምናከብርበት ጊዜ በሃይማኖቱ አስተምህሮ መሠረት የተቸገሩ ወገኖችን በመርዳት፣ ያለንን በማካፈልና ሌሎች በጎ ተግባራትን በመፈጸም ልናከብረው እንደሚገባ አሳስባለሁ።

በዓሉ የሰላም፣ የጤና፣ የብልጽግናና የደስታ እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ።

ኢድ ሙባረክ!

ዶ/ር አሉላ ታፈሰ
የኮሌጁ ዲን

የኮሌጃችን ተመራቂ ተማሪዎች ከአመራሮችና ሠራተኞች ጋር በመሆን የፅዳት ዘመቻ አካሄዱወ/ሶ/ግ/ኮ ግንቦት 15/2018 ዓ/ምበ2018 ትምህርት ዘመን ትምህርታቸውን በማጠናቀቅ የሚመረቁ የኮሌጃች...
23/05/2026

የኮሌጃችን ተመራቂ ተማሪዎች ከአመራሮችና ሠራተኞች ጋር በመሆን የፅዳት ዘመቻ አካሄዱ

ወ/ሶ/ግ/ኮ ግንቦት 15/2018 ዓ/ም

በ2018 ትምህርት ዘመን ትምህርታቸውን በማጠናቀቅ የሚመረቁ የኮሌጃችን ሦስተኛ ዓመት መደበኛ መርሐ-ግብር ተማሪዎች ከኮሌጁ አመራሮችና ሠራተኞች ጋር በመሆን የፅዳት ዘመቻ አካሄደዋል።

በዚህ ወቅት፣ የኮሌጃችን አስተዳደርና ልማት ም/ዲን፣ የዲን ተወካይ አቶ አበባየሁ ሙንኤ፣ ተማሪዎቹ በራስ ተነሳሽነት ኮሌጃችንን ለማሳመር የፅዳት ሥራዎችን መስራታቸውን አድንቀው፤መሠል ሥራዎች ተጠናክረው ልቀጥሉ እንደሚገባ አሳስበዋል።

በዘመቻው ላይ የኮሌጁ አስተዳደርና ልማት ም/ዲን፣ የዲን ተወካይ አቶ አበባየሁ ሙንኤ፣ የመስኖና ፍሳሽ ትምህርት ክፍል ኃላፊ፣ የትምህርትና ሥልጠና ዘርፍ ኃላፊ እና ም/ዲን ተወካይ መ/ር ዳህላክ ጨመሰን ጨምሮ ሌሎች የሥራ ክፍል ኃላፊዎች፣ ሠራተኞችና ተማሪዎች በንቃት ተሳትፈዋል።

በተማሪዎች ማሳ ላይ  የቃሪያና ሌሎች የጓሮ አትክልቶች ልማት ሥራ በስፋት እየተሰራ ነው።ወ/ሶ/ግ/ኮ ግንቦት 13/2018 ዓ/ምኮሌጃችን በተማሪዎች ማሳ ላይ  የተለያዩ የጓሮ አትክልቶችን እያ...
21/05/2026

በተማሪዎች ማሳ ላይ የቃሪያና ሌሎች የጓሮ አትክልቶች ልማት ሥራ በስፋት እየተሰራ ነው።

ወ/ሶ/ግ/ኮ ግንቦት 13/2018 ዓ/ም

ኮሌጃችን በተማሪዎች ማሳ ላይ የተለያዩ የጓሮ አትክልቶችን እያለማ ይገኛል።

እነዚህን ሰብሎች በማልማት ሂደት ከማሳ ዝግጅት ጀምሮ እስከ ምርት መሰብሰብ ድረስ ባሉ የተለያዩ ተግባራት ላይ ተማሪዎች በንቃት ይሳተፋሉ።

በዚህ መሠረት በተማሪዎች ማሳ እየለሙ ካሉ ሰብሎች መካከል ቃሪያ ተጠቃሽ ነው ፤ ኮሌጃችን ከመማር ማስተማር ስራ ባሻገር ምርቶች ለኮሌጁ እና አከባቢው ማህበረሰብ በተመጣጣኝ ዋጋ እየቀረቡ ነው።

አስደሳች ዜና ለኮሌጃችንና ለአካባቢው ማህበረሰብ በሙሉ፦ኮሌጃችን የሥጋ ዶሮ በተመጣጣኝ ዋጋ ለሽያጭ አቅርቧል።በመሆኑም የኮሌጃችንና የሶዶ ከተማ እንድሁም የአካባቢው ማህበረሰብ አባላት በሙሉ ...
20/05/2026

አስደሳች ዜና ለኮሌጃችንና ለአካባቢው ማህበረሰብ በሙሉ፦

ኮሌጃችን የሥጋ ዶሮ በተመጣጣኝ ዋጋ ለሽያጭ አቅርቧል።

በመሆኑም የኮሌጃችንና የሶዶ ከተማ እንድሁም የአካባቢው ማህበረሰብ አባላት በሙሉ ወደ ኮሌጁ ሽያጭ ማዕከል በአካል በመቅረብ መግዛት እንደምትችሉ በደስታ እናሳውቃለን።

ከዞኑ ግብርና መምሪያ የአፈር ለምነት ማሻሻያ ቡድን መሪ በወ/ሮ ብርሃነሽ አበበ የተመራ ልዑክ ወደ ኮሌጃችን በመምጣት በቨርሚ ኮምፖስት ቴክኖሎጂ ዙሪያ ልምድ ልውውጥ አደረገወ/ሶ/ግ/ኮ ግንቦ...
16/05/2026

ከዞኑ ግብርና መምሪያ የአፈር ለምነት ማሻሻያ ቡድን መሪ በወ/ሮ ብርሃነሽ አበበ የተመራ ልዑክ ወደ ኮሌጃችን በመምጣት በቨርሚ ኮምፖስት ቴክኖሎጂ ዙሪያ ልምድ ልውውጥ አደረገ

ወ/ሶ/ግ/ኮ ግንቦት 08/2018 ዓ/ም

ከወላይታ ዞን ግብርና መምሪያ የአፈር ለምነት ማሻሻያ ቡድን መሪ በወ/ሮ ብርሃነሽ አበበ የተመራ ልዑክ ወደ ኮሌጃችን በመምጣት በቨርሚ ኮምፖስት ቴክኖሎጂ ዙሪያ ልምድ ልውውጥ አድርጓል።

በዚህ ወቅት፣ የቨርሚ ኮምፖስት ፕሮጀክት አስተባባሪ መ/ር ሄኖክ ፋንታሁን ለልዑካን ቡድኑ ኮምፖስቱን ለማምረት የሚያስፈልጉ ግብዓቶች፣ የማምረቻ ዘዴዎችና ሞዴሎች ላይ ሰፋ ያለ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

በልምድ ልውውጡ ላይ በዞኑ ግብርና መምሪያ የአፈር ለምነት ማሻሻያ ቡድን መሪ ወ/ሮ ብርሃነሽ አበበ፣ በማህበር ተደራጅተው ቨርሚ ኮምፖስት እያመረቱ የሚገኙ የሕብረተሰብ ክፍሎችና ሌሎች አካላት ተገኝተዋል።

አቮካዶ የምግብና የሥነ-ምግብ ዋስትና ለማረጋገጥና ኢኮኖሚ ለማሻሻል ወሳኝ ሰብል በመሆኑ ትኩረት ተሰጥቶ ሊሰራበት ይገባል፦ አቶ አድማሱ አወቀወ/ሶ/ግ/ኮ ግንቦት 08/2018 ዓ/ምየደቡብ ኢት...
16/05/2026

አቮካዶ የምግብና የሥነ-ምግብ ዋስትና ለማረጋገጥና ኢኮኖሚ ለማሻሻል ወሳኝ ሰብል በመሆኑ ትኩረት ተሰጥቶ ሊሰራበት ይገባል፦ አቶ አድማሱ አወቀ

ወ/ሶ/ግ/ኮ ግንቦት 08/2018 ዓ/ም

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ግብርና ቢሮ እና በክልሉ ብሔራዊ የአቮካዶ ልማት ፕሮግራም (NADP) በመተባበር «በክልላችን በክላስተር የተመሠረተ ጥራት ያለው አቮካዶ በማምረትና ለሀገር ውስጥና ለውጭ ሀገር ገበያ በዘላቂነት በማቅረብ ጠንካራና ተወዳዳሪ የአቮካዶ ኢንዱስትሪ እንመሠርታለን!» በሚል መሪ ሃሳብ በአቮካዶ እሴት ሰንሰለት ዙሪያ ለዘርፉ ባለሙያዎች የተዘጋጀ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና በኮሌጃችን እየተሰጠ ይገኛል።

በሥልጠናው ማስጀመሪያ ላይ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የክልሉ ግብርና ቢሮ ም/ኃላፊና የእርሻ ዘርፍ ኃላፊ እንዲሁም የኮሌጃችን አስተዳደር ቦርድ ሰብሳቢ አቶ አድማሱ አወቀ እንደገለጹት፣ የብልጽግና ፓርቲ ግብርናን ለማዘመን ሰፊ ሥራዎችን እየሰራ ነው።

ግብርናን በማሸጋገር ገጠርን ለማሸጋገር፣ገጠርን በማሸጋገር መዋቅራዊ ሽግግርን ለማምጣት ሰፊ ስራዎች ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰሩ እንደሚገኙ በማከል ተናግረዋል።

ግብርናን ትራንስፎርም ለማድረግ አንድ አርሶአደር ከሚያመርተው 70 በመቶ ወደ ማዕከላዊ ገበያ ማቅረብ አለበት ያሉት አቶ አድማሱ፤ ይህንን ለማሳካት የተለያዩ ሥራዎች በትኩረት እየተሰሩ እንደሚገኙ አመላክተዋል።

አቮካዶ የምግብና የሥነ-ምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ፣የአርሶ አደር ኢኮኖሚ በቤተሰብ ደረጃ ለማሻሻልና የአቮካዶ ምርት በማቀነባበር ወደ ውጭ ገበያ በማቅረብ ለሀገራችን የውጭ ምንዛሬ በማስገኘት የሀገራችን ኢኮኖሚ ለማሳደግ ወሳኝ ሰብል መሆኑን ተናግረው፤ የባለድርሻ አካላት በሰብሉ ላይ ትኩረት
ሰጥተው መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል።

የኮሌጃችን አስተዳደርና ልማት ዘርፍ ኃላፊና ም/ዲን እንዲሁም ዲን ተወካይ አቶ አበባየሁ ሙንኤ በበኩላቸው፤ የአረንጓዴ አሻራ ኢኒሼቲቭ መጀመሪያ ምዕራፍ ማጠቃለያ ዘንድሮው እንደሚደረግ ጠቅሰው፤በበጀት ዓመቱ በክልሉ ለፍራፍሬና ቡና ችግኞች ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል ።

አቶ አበባየሁ አክለውም፣ ክልሉ በዘንድሮው አረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር ላይ ለፍራፍሬ ችግኝ የሰጠውን ትኩረት መነሻ በማድረግ ኮሌጃችን 100 ሺህ የአቮካዶ ችግኞችን እያፈላ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

የዩኒቨርሲቲው የእንስሳት እርባታ ተማሪዎች በኮሌጃችን በአሳማ እርባታ ዙሪያ የተግባር ልምምድ አደረጉወ/ሶ/ግ/ኮ ግንቦት 07/2018 ዓ/ምየወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የእንስሳት እርባታ የሁለተኛ...
15/05/2026

የዩኒቨርሲቲው የእንስሳት እርባታ ተማሪዎች በኮሌጃችን በአሳማ እርባታ ዙሪያ የተግባር ልምምድ አደረጉ

ወ/ሶ/ግ/ኮ ግንቦት 07/2018 ዓ/ም

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የእንስሳት እርባታ የሁለተኛ ዓመት መደበኛ መርሐ-ግብር ተማሪዎች ወደ ኮሌጃችን በመምጣት በአሳማ እርባታ ዙሪያ የተግባር ልምምድ አካሂደዋል።

በተግባር ልምምዱ ወቅት ለተማሪዎቹ የአሳማ እርባታ ዘዴዎች፣ የበሽታ መከላከልና ቁጥጥርን ጨምሮ በሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ገለጻና የተግባር ስልጠና ተሰጥቷቸዋል።

አስተያየታቸውን የሰጡት ተማሪዎች ፣የተግባር ልምምዱ በንድፈ ሃሳብ የተማሩትን እውቀት ከተግባር ጋር በማጣመር የሙያ ብቃታቸውን እንዲያሳድጉ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንዳለው ገልጸዋል።

የኮሌጃችን ማኔጅመንት ኮሚቴና አካዳሚክ ኮሚሽን አባላት በዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ላይ ውይይት አካሄዱወ/ሶ/ግ/ኮ ግንቦት 03/2018 ዓ/ምየኮሌጃችን ማኔጅመንት ኮሚቴና አካዳሚክ ኮሚሽን ...
11/05/2026

የኮሌጃችን ማኔጅመንት ኮሚቴና አካዳሚክ ኮሚሽን አባላት በዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ላይ ውይይት አካሄዱ

ወ/ሶ/ግ/ኮ ግንቦት 03/2018 ዓ/ም
የኮሌጃችን ማኔጅመንት ኮሚቴና አካዳሚክ ኮሚሽን አባላት በ2018 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ላይ ውይይት አካሂደዋል።

በዚህ ወቅት፣ በትምህርትና ሥልጠና እንዲሁም በአስተዳደርና ልማት ዘርፎች በዘጠኝ ወራት ውስጥ ታቅደው የተከናወኑ ተግባራት ላይ በልማት ዕቅድ ዝግጅት፣ ክትትልና ግምገማ ቡድን መሪ አቶ ፋንቱ ወ/መስቀል ገለጻ አቅርበዋል።

ከገለጻው በኋላ አስተያየት የሰጡ የማኔጅመንት ኮሚቴና አካዳሚክ ኮሚሽን አባላት፣ ኮሌጃችን በዘጠኝ ወራት ውስጥ ባከናወናቸው ተግባራት የተሻለ ውጤት ማስመዝገቡን ገልጸዋል።

የኮሌጃችን አስተዳደርና ልማት ዘርፍ ኃላፊና ም/ዲን አቶ አበባየሁ ሙንኤ ከመድረኩ ለተነሱ ጉዳዮች ምላሽና ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት፣ በዘንድሮው በጀት ዓመት ከመማር ማስተማር ሥራ ጎን ለጎን የተለያዩ የግብርና ልማት ሥራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኙ ገልጸዋል።

በበጀት ዓመቱ በችግኝ ጣቢያ ላይ የአቮካዶ፣ ቡናና ፓፓያን ጨምሮ የተለያዩ የፍራፍሬና የደን ዛፍ ችግኞች እየፈሉ እንደሚገኙም ጠቁመዋል።

በኮሌጃችን የሚመረቱ የግብርና ምርቶችን በወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር በተሰጠው የሽያጭ ማዕከል በዘላቂነት ለማቅረብ ሥራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን ጨምረው ገልጸዋል።

የኮሌጃችን ትምህርትና ሥልጠና ዘርፍ ኃላፊና ም/ዲን አቶ ታሪኩ ጨመረ በበኩላቸው፣ ኮሌጃችን ዘመናዊ ችግኝ ጣቢያ ለማቋቋም በያዘው ዕቅድ መሠረት የችግኝ ሽፋን (Shade Net) የመሸፈን ሥራ መጠናቀቁን ገልጸው፣ ይህም የተለያዩ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞችን በዘላቂነት በማፍላት ለአካባቢው ማህበረሰብና ተቋማት ለማቅረብ ትልቅ አቅም የሚፈጥር ቋሚ ሀብት መሆኑን አስገንዝበዋል።

የኮሌጃችን ዲን ዶ/ር አሉላ ታፈሰ በማጠቃለያው ላይ እንደገለጹት፣ በዘንድሮው በጀት ዓመት እየተተገበሩ ያሉ የችግኝ ጣቢያ፣ ቨርሚ ኮምፖስት፣ የግቢ ውበትና ግሪነሪ እንዲሁም የሰው ሰራሽ አዳቃይ (Artificial Insemination) የምርምርና ስርጸት ፕሮጀክቶች በተሻለ አፈጻጸም ደረጃ ላይ እንደሚገኙ አመላክተዋል።

ኮሌጃችን በትምህርት፣ ሥልጠና፣ ምርምር፣ማህበረሰብ አገልግሎትና የግብርና ልማት ዘርፎች እያስመዘገበ ያለውን ውጤት የበለጠ ለማጠናከር በቀሪዎቹ ወራት የታቀዱ ተግባራትን በተቀናጀ አመራርና አንድ በመሆን በብቃት ለማሳካት በመግባባት ውይይቱ ተጠናቋል።

በኮሌጃችን ሲካሄድ የቆየው የሙያ ብቃት ምዘና በሰላምና በስኬት ተጠናቀቀ።ወ/ሶ/ግ/ኮ ግንቦት 01/2018 ዓ/ም ኮሌጃችን ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሙያ ብቃት ምዘና ማረጋገጫ ኤጀንሲ ጋር በመቀ...
09/05/2026

በኮሌጃችን ሲካሄድ የቆየው የሙያ ብቃት ምዘና በሰላምና በስኬት ተጠናቀቀ።

ወ/ሶ/ግ/ኮ ግንቦት 01/2018 ዓ/ም

ኮሌጃችን ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሙያ ብቃት ምዘና ማረጋገጫ ኤጀንሲ ጋር በመቀናጀት ከሚያዝያ 30/2018 ዓ/ም እስከ ግንቦት 01/2018 ዓ/ም ድረስ ሲያካሂድ የቆየው የሙያ ብቃት ምዘና በሰላምና በስኬት መጠናቀቁን የኮሌጃችን ትምህርትና ሥልጠና ዘርፍ ኃላፊና ም/ዲን አቶ ታሪኩ ጨመረ ገልጸዋል።

አቶ ታሪኩ አያይዘውም ፣ ለምዘናው ስኬት አስተዋጽኦ ላደረጉ የኤጀንሲው ማኔጅመንት ኮሚቴ አባላትንና መዛኞችን፣ የኮሌጃችን ትምህርት ክፍል ኃላፊዎችን፣ የሙያ ብቃት ምዘና ኮሚቴ አባላትን፣ የኮምፒውተር ባለሙያዎችንና ሌሎችን አመስግነዋል።

የኮሌጃችን ሙያ ብቃት ምዘና ማስተባበሪያ ኃላፊ መ/ር በለጠ ቦቴ በበኩላቸው ፣ ምዘናው በእንስሳት እርባታ፣ በተፈጥሮ ሀብት አያያዝ ፣ በእንስሳት ጤና እና በሕብረት ሥራ ሂሳብ አያያዝና ኦዲቲንግ የሙያ መስመሮች መካሄዱን አብራርተዋል።

መ/ር በለጠ አክለውም፣ በአራቱ የሙያ መስመሮች በአጠቃላይ 298 ተመዛኞች መሳተፋቸውን ተናግረዋል።

Address

Woliata S**o
S**o
120

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Wolaita Sodo Agricultural College posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share