16/03/2026
የሶዶ ዙሪያ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት የCatch up Campaign ኦርንቴሽን እየሰጠ መሆኑን ገለጸ፡፡
መጋቢት 07/2018 ዓ.ም ወላይታ ሶዶ፤ የሶዶ ዙሪያ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት የCatch up Campaign ኦርንቴሽን እየሰጠ መሆኑን ገልጹዋል፡፡
መድረኩን የመሩት የሶዶ ዙሪያ ወረዳ ም/አስተዳዳሪና የወረዳዉ ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት ሲ/ር መስከረም በቀለ ፡- በዚህ ዘመቻ ኦርንቴሽን ላይ የCatch up Campaign፣ የጤናማ እናትነት፣ የጽዱ ኢትዮጵያ/ወረዳ መፍጠር፣ የማዐጤመ ሰነዶች እንደሚቀርቡ አንስተዉ ከዚህ ዘመቻ ጋር በቅንጅት የሚሠሩ የመደበኛ ክትባት አገልግሎት፤ የህጻናት የዕድገት ክትትል፤ የህጻናት፣ የነፍሰጡርና አጥቢ እናቶች የምግብ እጥረት ልዬታ ሥራ እንደሚሠራ ገልጸዋል፡፡
ዘመቻዉ በሁሉም ቀበሌ ቤት ለቤት በመግባት ክትባት ያልጀመሩና ያቋረጡ ህጻናትን በማግኘት አንድም ሳይቀር መከተብ እንዳለባቸዉ ተናግረዉ ሁሉም ከታቢና ሱፔርቫይዘሮች በተጠያቂነት መምራት እንዳለባቸዉ አንስተዋል፡፡ ከዘመቻዉ ጋር በቅንጅት የሚሠሩ ተግባራትም ትኩረት ተሰጥተዉ መመራት እንዳለባቸዉ ተናግረዉ የእያንዳንዱ ሥራ በጤና ኬላም ሆነ በጤና ጣቢያ ተደራጅቶ መቀመጥ እንዳለባቸዉ አንስተዋል፡፡
የጤናማ እናትነት በተመለከተ ሁሉም ነፍሰጡር እናቶች እርግዝናቸዉ ከተከሰተ ከ12 ሳምንት በፊት ጀምሮ ክትትል እንዲጀምሩ ለማድረግ የልየታና ምዝገባ ሥራ በሁሉም ጤና ኤክስቴንሽን ሠራተኞች ተጠናሮ መሠራት እንዳለበት አንስተዋል፡፡ የነፍሰጡር እናቶች ኮንፍራንስም ያለምንም መቆራረጥ በየወሩ በሁሉም ቀበሌ መደረግ እንዳለበት፤ ሁለቱም ጤና ጣቢያ እናቶች የቅድመ ወሊድ ክትትል እስከ 8ኛ ዙር እንዲደርሱ ክትትልና ምርመራ አገ/ሎት ማጠናከር እንዳለባቸዉ፤ የማቆያ ቤት አገ/ሎት ግብዓት ከማሟላትም አንጻር ማጠናከር እንዳለባቸዉ፤ የጤና ጣቢያ አገ/ሎት ሳቢና ማራኪ እንዲሆን በኃላፊነት መምራት እንዳለባቸዉ ተናግረዋል፡፡
የጽዱ ኢትዮጵያ/ወረዳ መፍጠር ዙሪያ ሁሉም ጤና ኤክስቴንሽን የቤተሰብና የጋራ መጸዳጃ ቤት ፣ የደረቅና ፍሳሽ ቆሻሻ ማስወገጃ ኢዲት መሠራት እንዳለበት፤ አንስተዉ ባለፈዉ የተጀመረዉ ንቅናቄ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አንስተዋል፡፡
ሌላዉ ማዐጤመ የአባላት መታወቂያ ከፋይዳ ጋር የማስተሳሰር ሥራ በሁሉም ቀበሌ ተጠናክሮ መሠራት እንዳለበት አንስተዋል፡፡
በመድረኩ ላይ የወረዳ ሱፔርቫይዘሮች፣ የሁለቱም ጤና ጣቢያ ኃላፊዎችና የሁሉም ቀበሌ ጤና ኤክስቴንሽን ሠራተኞች ተገኝተዋል፡፡የሶዶ ዙሪያ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት የCatch up Campaign ኦርንቴሽን እየሰጠ መሆኑን ገለጸ፡፡
መጋቢት 07/2018 ዓ.ም ወላይታ ሶዶ፤ የሶዶ ዙሪያ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት የCatch up Campaign ኦርንቴሽን እየሰጠ መሆኑን ገልጹዋል፡፡
መድረኩን የመሩት የሶዶ ዙሪያ ወረዳ ም/አስተዳዳሪና የወረዳዉ ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት ሲ/ር መስከረም በቀለ ፡- በዚህ ዘመቻ ኦርንቴሽን ላይ የCatch up Campaign፣ የጤናማ እናትነት፣ የጽዱ ኢትዮጵያ/ወረዳ መፍጠር፣ የማዐጤመ ሰነዶች እንደሚቀርቡ አንስተዉ ከዚህ ዘመቻ ጋር በቅንጅት የሚሠሩ የመደበኛ ክትባት አገልግሎት፤ የህጻናት የዕድገት ክትትል፤ የህጻናት፣ የነፍሰጡርና አጥቢ እናቶች የምግብ እጥረት ልዬታ ሥራ እንደሚሠራ ገልጸዋል፡፡
ዘመቻዉ በሁሉም ቀበሌ ቤት ለቤት በመግባት ክትባት ያልጀመሩና ያቋረጡ ህጻናትን በማግኘት አንድም ሳይቀር መከተብ እንዳለባቸዉ ተናግረዉ ሁሉም ከታቢና ሱፔርቫይዘሮች በተጠያቂነት መምራት እንዳለባቸዉ አንስተዋል፡፡ ከዘመቻዉ ጋር በቅንጅት የሚሠሩ ተግባራትም ትኩረት ተሰጥተዉ መመራት እንዳለባቸዉ ተናግረዉ የእያንዳንዱ ሥራ በጤና ኬላም ሆነ በጤና ጣቢያ ተደራጅቶ መቀመጥ እንዳለባቸዉ አንስተዋል፡፡
የጤናማ እናትነት በተመለከተ ሁሉም ነፍሰጡር እናቶች እርግዝናቸዉ ከተከሰተ ከ12 ሳምንት በፊት ጀምሮ ክትትል እንዲጀምሩ ለማድረግ የልየታና ምዝገባ ሥራ በሁሉም ጤና ኤክስቴንሽን ሠራተኞች ተጠናሮ መሠራት እንዳለበት አንስተዋል፡፡ የነፍሰጡር እናቶች ኮንፍራንስም ያለምንም መቆራረጥ በየወሩ በሁሉም ቀበሌ መደረግ እንዳለበት፤ ሁለቱም ጤና ጣቢያ እናቶች የቅድመ ወሊድ ክትትል እስከ 8ኛ ዙር እንዲደርሱ ክትትልና ምርመራ አገ/ሎት ማጠናከር እንዳለባቸዉ፤ የማቆያ ቤት አገ/ሎት ግብዓት ከማሟላትም አንጻር ማጠናከር እንዳለባቸዉ፤ የጤና ጣቢያ አገ/ሎት ሳቢና ማራኪ እንዲሆን በኃላፊነት መምራት እንዳለባቸዉ ተናግረዋል፡፡
የጽዱ ኢትዮጵያ/ወረዳ መፍጠር ዙሪያ ሁሉም ጤና ኤክስቴንሽን የቤተሰብና የጋራ መጸዳጃ ቤት ፣ የደረቅና ፍሳሽ ቆሻሻ ማስወገጃ ኢዲት መሠራት እንዳለበት፤ አንስተዉ ባለፈዉ የተጀመረዉ ንቅናቄ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አንስተዋል፡፡
ሌላዉ ማዐጤመ የአባላት መታወቂያ ከፋይዳ ጋር የማስተሳሰር ሥራ በሁሉም ቀበሌ ተጠናክሮ መሠራት እንዳለበት አንስተዋል፡፡
በመድረኩ ላይ የወረዳ ሱፔርቫይዘሮች፣ የሁለቱም ጤና ጣቢያ ኃላፊዎችና የሁሉም ቀበሌ ጤና ኤክስቴንሽን ሠራተኞች ተገኝተዋል፡፡