18/11/2021
ከእግዚአብሔር ጋር ስላለን ሕብረት
“ሁለቱን አንድ ያደረገ፣ የሚለያየውንም የጥል ግድግዳ ያፈረሰ ሰላማችን እርሱ ራሱ ነውና፤”
— ኤፌሶን 2፥14 (አዲሱ መ.ት)
በሕይወት ለእኛ ከምንም በላይ ትልቁ ጉዳይ ከእግዚአብሔር ጋር ያለን ሰላማዊ ሕብረት ነው። እኛ ከእግዚአብሔር ጋር ሰላም አለን ስንል፣ እርሱ ለእኛ ለመልካም ይሰራል፣ ጠላታችን አይደለም ማለታችን ነው።
ከእርሱ ጋር ያለን ሕብረት በጨመረ ቁጥር በእርሱ ላይ ያለን እምነት እያደገ ይሄዳል። ይህ ሲሆን ሕይወታችን ወደ ከፍታ ይጓዛል።
ከምንም በላይ በሕይወት አስቀድማችሁ ከእርሱ ያላችሁን ሕብረት ጠብቁ እርሱ ሁሉን ያከናውናል። ከእርሱ ጋር ያለን ሕብረት ለመልካም ነገር ሁሉ መንገድ ነው።
ሰው ከእግዚአብሔር ጋር ያለውን ሕብረት ካጣ ሕይወቱን አጥቷል ማለት ነው። ያለ እርሱ ሕብረት ሕይወት የለንም።
እንፀልይ