05/12/2023
ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ሰራተኞች ጋር በወላይታ ሶዶ ከተማ እየተወያዩ ነው
ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ሰራተኞች ጋር በወላይታ ሶዶ ከተማ ውይይት እያካሄዱ ይገኛሉ።
ርዕሰ መስተዳድሩ ውይይት እያካሄዱ የሚገኙት
የክልሉ የፖለቲካ እና የአስተዳደር ማዕከል በሆነው ሶዶ ከተማ ከሚገኙ የክልል ተቋማት ሰራተኞች ጋር ነው።
የመንግስት ሰራተኞች እኩልነት እና ፍትሀዊነትን ብሎም የክልሉን ተጨባጭ አቅም ማዕከል ባደረገ አግባብ አገልግሎት መስጠት እንደሚገባቸውም ነው ርዕሰ መስተዳድሩ የገለፁት።
ርዕሰ መስተዳድሩ ከሰራተኞች ለሚነሱ ጥያቄዎች ሚላሽ ከመስጠት ባሻገር በመንግስት ተቋማት የሚሰጡ አገልግሎትን ውጤታማና ህዝብን የሚያረኩ ማድረግ የሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ውይይት ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።