South Ethiopia Region Prosperity Party - የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ

  • Home
  • Ethiopia
  • Sodo
  • South Ethiopia Region Prosperity Party - የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ

South Ethiopia Region Prosperity Party - የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ South Ethiopia Region Prosprity Party Branch Office

የኢትዮጵያ ማንሰራራት!የዘንድሮው የጳጉሜን ወር "የኢትዮጵያ ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል በልዩ ልዩ መርሃ-ግብሮች ይከበራል።ኢትዮጵያ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ዘርፈ-ብዙ ድሎችን እያስመዘገበች፣...
04/09/2026

የኢትዮጵያ ማንሰራራት!

የዘንድሮው የጳጉሜን ወር "የኢትዮጵያ ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል በልዩ ልዩ መርሃ-ግብሮች ይከበራል።

ኢትዮጵያ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ዘርፈ-ብዙ ድሎችን እያስመዘገበች፣ ውስብስብ ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ፈተናዎችን በፅናትና በፈጠራ በመሻገር፣ በአሁን ወቅት በማንሠራራት ምዕራፍ ላይ ትገኛለች።

የጳጉሜን ወር በኢትዮጵያ የዘመን አቆጣጠር ዘይቤ ውስጥ ወደ አዲሱ ዓመት መሸጋገሪያ ድልድይ በመሆን የተገኙ ወረቶች የሚደመሩበት እንዲሁም ለቀጣዩ ዓመት የከፍታ ጉዞ አዲስ ተስፋ የሚሰነቅበት ልዩ ሀገራዊ መለያችን ነው።

የዘንድሮው የጳጉሜን ቀናት አከባበር የነበሩ ጥንካሬዎችን የሚያስቀጥል፣ የታዩ ክፍተቶችን የሚያርም፣ አዳዲስ የፈጠራ ስልቶችን ታሳቢ ያደረገ፣ የቴክኖሎጂ አቅሞችን በሚገባ የሚጠቀም፣ የተመዘገቡ ትላልቅ ስኬቶችን የሚያስታውስ፣ አዳዲስ ብስራቶችን የሚያበስር በመሆሃ በሳቢ ኹነቶችና የንቅናቄ መንገዶች የሚመራ ይሆናል።

የ 2018 ዓ.ም የጳጉሜን ቀናት ከቀደሙት ዓመታት በተለየ መልኩ በብሥራት፣ በተስፋ እና በሁለንተናዊ የብልጽግና ራዕይ ላይ ትኩረት አድርጎ እንደሚከበርም የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ገብረመስቀል ጫላ ተናግረዋል።

የ 2018 ዓ.ም የጳጉሜን ቀናት፤ ጳጉሜን 1 (የእመርታ ቀን)፣ ጳጉሜን 2 (የማንሰራራት ቀን)፣ ጳጉሜን 3 (የጽናት ቀን)፣ ጳጉሜን 4 (የኅብር ቀን) እንዲሁም ጳጉሜን 5 (የነገ ቀን) በሚሉ መርሃ-ግብሮች በድምቀት የሚከበሩ ይሆናል።

የክልሉ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ በኮንሶ ዞን ኮልሜ ወረዳ ለአንድ አቅመ ደካማ ወገን የመኖሪያ ቤት ግንባታን አስጀመረነሐሴ 28/2018 ዓ/ም የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ...
03/09/2026

የክልሉ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ በኮንሶ ዞን ኮልሜ ወረዳ ለአንድ አቅመ ደካማ ወገን የመኖሪያ ቤት ግንባታን አስጀመረ

ነሐሴ 28/2018 ዓ/ም

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ኃላፊ ቦጋለ ቦሼ(ዶ/ር)ን ጨምሮ የቢሮው አመራሮችና ሰራተኞች፣ ከኮልሜ ወረዳ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን፣ በወረዳው ማዕከል በደልቤና ለሚገነባው የአቅመ ደካማ ቤት የሚያስፈልጉ የፋብሪካ ውጤቶችንና ሌሎች የግንባታ ግብዓቶችን በማቅረብ ግንባታውን በይፋ አስጀምረዋል።

የቢሮው ኃላፊ ዶ/ር ቦጋለ በወቅቱ ፣ በጎ ተግባር በተግባር መገለጥ እንዳለበት በመጠቆም የተጀመረው ሥራ ከማህበራዊ ኃላፊነት አንፃር ከፍተኛ ትርጉም ያለው በጎ ተግባር በመሆኑ በተለየ ትኩረትና በተቀናጀ መልኩ መሰራት ይገባል ብለዋል።

በዛሬው ዕለት የተጀመረው ግንባታው ቶሎ እንዲጠናቀቅ ሁሉም የሚመለከታቸው አካላት የበኩላቸውን እንዲወጡ ጥሪ ያቀረቡት ኃላፊው ፣ ቤቱ በ15 ቀናት ውስጥ ሙሉ በሙሉ ተጠናቅቆ ለተጠቃሚው እንዲደርስ አስፈላጊው ርብርብ እንደሚደረግ ገልጸዋል።

ቤቱ በብሎኬት የሚገነባ ሲሆን፣ ለግንባታው የሚያስፈልጉ የፋብሪካ ውጤቶችና ሌሎች ግብዓቶች ተጓጉዘው ወደ ሥፍራው እንዲደርሱ መደረጉ፣ ይህም ግንባታው በተቀመጠለት አጭር ጊዜ ውስጥ እንዲጠናቀቅ ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥር ተገልጿል።

አራት ክፍሎች የሚኖሩት ቤቱ፣ በኮንክሪትና በጥራት እንዲገነባ ተገቢው ትኩረት እንዲሰጠውም አሳስበዋል።

በጎነት በበጀት ብቻ አይለካም ያሉት ዶ/ር ቦጋለ "ለዚህ የበጎ ተግባር ሥራ በተለይ የተመደበ በጀት ባይኖርም፣ በተቀናጀ የሰው ኃይል፣ የቁሳቁስና የሎጂስቲክ አቅም በመጠቀም ሥራውን ማሳካት ይቻላል ብለዋል።

በክልል ደረጃ በርካታ የበጎ ተግባር ቤት ግንባታዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን ጠቁመው፣ ከተያዙት 70 ቤቶች ውስጥ ሁለቱ በኮልሜ ወረዳ እንደሚገነቡ ገልጸዋል።

በማስጀመሪያው መሪሃግብሩ የክልሉ የኢኖቬሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ከፍተኛ አመራሮችና ባለሙያዎች እንዲሁም የወረዳው ከፍተኛ አመራሮች የተገኙ ሲሆን ቢሮ ላደረገው በጎ ሥራ የወረዳው አመራሮች አመስግነዋል።

የአሪ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ በባስኬቶ ዞን በመገኘት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት አካሄደ‎‎ነሐሴ 28/2018 ዓ/ም‎"‎በጎነት ለእህትማማችነት ለሴቶች ተሳትፎ ተጠቃሚነት" በሚል መሪ ቃ...
03/09/2026

የአሪ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ በባስኬቶ ዞን በመገኘት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት አካሄደ

‎ነሐሴ 28/2018 ዓ/ም

"‎በጎነት ለእህትማማችነት ለሴቶች ተሳትፎ ተጠቃሚነት" በሚል መሪ ቃል የአሪ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ድንበር ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በአሪ ዞን አካሂዷል።

‎በመርሃ-ግብሩ ላይ የተገኙት የባስኬቶ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ክንፉ ሻቦ ብልጽግና ፓርቲ እንደ ሀገር ሰውን ታሳቢ ያደረገ ስራ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

‎አቅመ ደካሞችን ፈልጎ በመድረስ በልዩ ትኩረት እውነትን መሰረት ያደረገ በጎ ተግባር ላለፋት ሰባት አመታት እየተሰራ ቆይቷል ስሉም አቶ ክንፉ አክለዋል።

‎ይህ የበጎነት ተግባር በአንድ አካባቢ ተወስኖ እንዳይቀር መስፋት አለበት በማለት የወንድም አሪ ህዝብ ላደረገው ድንበር ተሻጋሪ በጎ አድራጎት አመስግነዋል።

‎የአሪ ዞን ህዝብ ምክር ቤት አፈጉባኤ ወ/ሮ ስመኝ ተስፋዬ ብልጽግና ፓርቲ ሰው ተኮር ፓርቲ ነው ያሉ ስሆን ይህን መርህ በማድረግ በጎነት ድንበር ብሔር ሀይማኖት የለውምና ይህን ታሳቢ በማድረግ ወደ ባስኬቶ ዞን መጥተናል ብለዋል።

‎በበጎ ስራ ከዚህ ቀደም በርካታ አቅመ ደካሞች ተገልግለዋል ስሉም አክለዋል።

‎መደጋገፍና በጎ ተግባር አብሮነትን ከማጠናከር አንጻር ፋይዳው የጎላ መሆኑን የገለፁት የላስካ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጳውሎስ ሀይሌ ከበጎነቱ ባሻገር አሪ ዞን ለወንድም ባስኬቶ ሁለተኛዋ ከተማ ናት ብለዋል።

‎የአሪ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ወ/ሮ ይመኙሻል ተፈሪ በበኩላቸው እንደገጹት በጎ ተግባር ዘር፣ ሀረግ፣ ብሄርንና ኃይማኖትን ባለመለየት ሰው ለሆነው ሁሉ በልግስና የሚከወን መልካም ተግባር መሆኑን ገልጸዋል።

‎የባስኬቶ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ኃላፊ ወ/ሮ መብተ ግሮ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በሴቶች ክንፍ በርካታ የበጎነት ስራዎች ተሰርተዋል ስሉ ገልጸዋል።

‎በጎነት የህዝብ ለህዝብ ያለውን መስተጋብር ከማጠናከር አኳያ ያለው ፋይዳ የጎላ ነው ያሉ ስሆን ይህ በሁሉም ማሕበረሰብ ተጠናክሮ የኢትዮጵያን የቀደመ አንድነት መስተጋብር ማጠናከር ይገባል ስሉም ወ/ሮ መብተ አክለዋል።

‎የበጎ ተግባር ስራው በባስኬቶ ዞን ላስካ ከተማ አስተዳደር የአንድት አቅመ ደካማ ቤት ስራ ያስጀመረ ስሆን በላስካ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በመገኘት ለወላድ እናቶች እንዲሁም ለአቅመ ደካሞች ድጋፍ አድርጓል።

‎የመደመር መንግሥት የተፈጥሮ አደጋዎችን በራስ አቅም መወጣት የሚያስችል ተግባራትን አቅዶ እየሰራ ነው፦ አቶ ንጋቱ ዳንሳ‎‎ነሐሴ ፤ 28/2018 በወላይታ ዞን በተፈጥሮ አደጋ ከቀያቸው ለተፈ...
03/09/2026

‎የመደመር መንግሥት የተፈጥሮ አደጋዎችን በራስ አቅም መወጣት የሚያስችል ተግባራትን አቅዶ እየሰራ ነው፦ አቶ ንጋቱ ዳንሳ

‎ነሐሴ ፤ 28/2018

በወላይታ ዞን በተፈጥሮ አደጋ ከቀያቸው ለተፈናቀሉ ወገኖች 2ኛ ዙር መልሶ ለማቋቋም በተዘጋጀው ቦታ የማስፈርና የአቀባበል መርሃግብር ተካሂዷል።

‎በመርሃግብሩ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የክልሉ የመንግስት ረዳት ተጠሪ አቶ ንጋቱ ዳንሳ የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር በክልሉ ባለፉት ዓመታት በርካታ ስራዎችን በመሰራት ሰብዓዊ ያሳየ ማህበር መሆኑን አስታውሰዋል።

‎ወላይታ ህዝብ ሌሎች አከባቢ ህዝቦች አርዓያ የሚሆኑ ስራዎች እየሰራ የሚገኝ ታላቅ ህዝብ መሆኑንም ተናግረዋል።

‎ተፈናቃዮች ራሳቸውን እሰከሚችሉ ድረስ አስፈላጊውን ድጋፍ ይደረጋል ያሉት አቶ ንጋቱ፥ የክልሉ መንግስት ከኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ጋር በቅንጅት እየሰራ እንደሚገኝም አንስተዋል።

‎አለም በተፈጥሮ አደጋ የተለያዩ አደጋዎች እያስተናገደች ትገኛለች ያሉት አቶ ንጋቱ፥ የመደመር መንግስታችን ይህን ችግር ቀድሞ በመገንዘብ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት በሚል ዕሳቤ እየሰራ እንደሚገኝም ጠቅሰዋል።

‎ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር በሚደረገው ጥረት ያሉ ፀጋዎችና እምቅ አቅሞቻችን በተገቢው በመጠቀም መረባረብ እንደሚያስፈልግም አጽንኦት ሰጥተዋል።

‎የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ረ/ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ በዞኑ በተፈጥሮ አደጋ ከቀያቸው ለተፈናቀሉ ዜጎች መልሶ ለማቋቋም ፓርቲያችን ብልፅግና ሰው ተኮር መሆኑን በተወሰደው ቁርጠኝ አቋም ይህ ፕሮጀክት እንዲጠናቀቅ አድርጓል ብለዋል።

‎እንዲህ አይነት ልማቶችን በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ መተባበርና መተጋገዝ እንደሚያስፈልግ አመላካች የሆነ ፕሮጀክት እንዲሆነም ተናግረዋል።

‎የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር በዞኑ በተፈጥሮ አደጋ ከቀያቸው ለተፈናቀሉ ወገኖች 2ኛ ዙር መልሶ ለማቋቋም ያደረገው ድጋፍና ርብርብ ምስጋና አቅርበዋል።

‎ተሳፋሪዎች ራሳቸዉን እስከሚችሉ ድረስ አስፈላጊውን ድጋፍና ትብብር ይደረጋል ያሉት ዋና አስተዳዳሪው፥ አስፈላጊ መሠረተ ልማትና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ማሟላቱንም ገልጸዋል።

‎ቀጣይ 3ኛ ዙር የተፈናቀሉ ዜጎችን መልሶ ለማቋቋም ህብረተሰቡንና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች በማስተባበር እንደሚጀመርም አስታውቀዋል።

‎የክልሉ አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር ወገነህ ብዙነህን ፓርቲያችን ብልፅግና በአደጋ ስጋት ያሉባቸው አከባቢዎች የሚኖሩ ዜጎችን በዘላቂነት ለማቋቋምና ምቹ ሁኔታዎች የመፍጠር ስራ እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

‎የክልሉ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ከዞኑ አስተዳደር ጋር በመቀናጀት አቅሙን የቻለውን ሁሉአቀፍ ድጋፍ እንደሚያደርግም አስታውቀዋል።

‎የአበላ አባያ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ተፈራ ታንቱ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

"በሠላም ጉዳይ ስር ነቀል ለውጥ እንዲመጣ ሁሉም ቅን ልቦናን ይዞ የሚጠበቅበትን ኃላፊነት በአግባቡ መወጣት አለበት" ክቡር አቶ አዳማ ትንጳዬ ነሐሴ 28/2018 ዓ.ምበደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ...
03/09/2026

"በሠላም ጉዳይ ስር ነቀል ለውጥ እንዲመጣ ሁሉም ቅን ልቦናን ይዞ የሚጠበቅበትን ኃላፊነት በአግባቡ መወጣት አለበት" ክቡር አቶ አዳማ ትንጳዬ

ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋርዱላ ዞን በዲራሼ ወረዳ "ሠላም ለሁሉም ሁሉም ለሠላም" በሚል መሪ ቃል ታላቂ የዕርቀ ሠላም የማጠቃለያ ኮንፍራንስ ተካሂዷል።

በወረዳው በኦርጊሌ ቀበሌ ማዕከል ላይ በተካሄደው በዚሁ ታላቂ መርሃ - ግብር ላይ የተገኙት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፌ - ጉባኤ የተከበሩ አቶ አዳማ ትንጳዬ በዞኑ በሠላም ጉዳይ ላይ ስር ነቀል የሆነ ለውጥ እንድመጣ ሁሉም ቂን ልቦናን ተላብሶ የሚጠበቅበትን ኃላፊነት በአግባቡ መወጣት እንዳለበት ገልጸዋል።

ክልሉን የሠላም፣ የመቻቻል እና የብልፅግና ተምሳሌት ለማድረግ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሚገኝም አፌ - ጉባኤው ጠቅሰዋል።

ክልሉ በሠላም ጉዳይ ላይ በየደረጃቸው የጀመራቸው ተግባራትን ከየትኛውም ጊዜ በላይ አጠናክሮ እንደሚያስቀጥልም ጠቁመዋል።

ክቡር ዋና አፌ - ጉባኤው በዞኑ ለዛሬው በአከባቢው አንፃራዊ ሠላም መስፈን ከክልል ጀምሮ ትልቅ ዋጋ ለከፈሉ አካላት ያላቸውን ትልቅ ክብር፣ ዕውቅናና አድናቆታቸውን ገልጸዋል።

የክልሉ ሠላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ አበነዘር ተረፈ በበኩላቸው የአከባቢው ሠላም እንድፀና ሁሉም ሰው አለያይ ከሆኑት ትርክቶች በመራቅ ለሠላም ዙሪያ ላይ የጀመረውን ዜብ የመቆምእሳበውን አጠናክሮ ማስቀጠል እንዳለበት ጠይቀዋል።

የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ፍሰሀ ጋርደው ሠላም ከሁሉ በላይ ቀዳሚ ጉዳይ መሆኑን በማመላከት ዛሬ ላይ በአከባቢው የጠብ፣ የጥላቻ እና የመናቆር መንፈስ ተቀርፎ ሁሉም ወደ በመተቃቀፍ ዕርቅ መፈፀሙ ከምንም በላይ ትልቅ ነገር እና የአከባቢው ገጽታ የሚገነባ መሆኑን አብራርተዋል።

የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ግንኙነት ኪታሞ በዚህን ወቅት ቀደም ሲል በአከባቢው ተከስተው የነበሩ ግጭቶቾ ህዝቡ ያልተገባ ዋጋ እንድከፍል እና ትልቅ የስነ ልቦና እና ቁሳዊ ክሳራዎችን እንድያልፍ ማድረግ መቻሉን አብራርተዋል።

ለግጭቶች መከሰት መንስኤ እየሆነ ያለው የተፈጥሮ ሀብቶች አጠቃቀም
ዙሪያ የሚስተዋሉ ችግሮች ሠላማዊ በሆነ መንገድ እልባት ላይ መድረስ እንድችሉ በልዩ ትኩረት መሰራቱንና በመሰራት ላይ እንዳለም ዋና አስተዳዳሪው ተናግረዋል።

ቀደም ሲል በህዝቡ መካከል ተዘርተው የነበሩ የጥላቻ እና የተዛቡ ትርክቶች ህዝቡ እንድለያይ ምክንያት ሆኗል ያሉት ዋና አስተዳዳሪው ዛሬ ላይ ሁሉም የሠላም ጉዳይ ያገበኛል ብሎ በመነሳሳቱ ቀድሞ የነበሩ የአንድነትና የአብሮነት እሴቶችን ተመልሰው እንድጠገኑ ህዝቡ የጋራ ተግባቦቶችን በመፍጠሩ እነኝህን መልሶ መጠገን መቻሉንም ዋና አስተዳዳሪው በገለፃቸው አክለዋል።

ከአጎራባች ዞኖች ተሳታፊ የነበሩት የኧሌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሐርሻሎ አርካሌ እና የኮንሶ ዞን ህዝብ ምክር ቤት አፌ - ጉባኤ የሆኑት አቶ ገረመው አያኖ በየበኩላቸው ዛሬ በአከባቢው የተካሄደው ይህ ታላቂ ዕርቅ የመጨረሻ መቋጫ መሆን አለበት ብለዋል።

በአከባቢው የሚስተዋሉ ግጭቶች ማህበረሰቡን እንደማይወክል አበክረው የገለጹት አካላቱ አጎራባች ዞኖች የጀመሩትን የጋራ የሠላም ትስስርን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ እንደዚሁ አመላክተዋል።

በኮንፍራንሱ ላይም የተጋጩ ሰዎች በይፋ በአደባባይ ላይ በመውጣት በፀፀት የይቅርታ እና የምህረት መርሃ - ግብሮችን አከናውነዋል።

በመጨረሻም ዕርቁ እንድፀና ባለ12 ነጥብ የአቋም መግለጫዎችን በማውጣት የዕለቱ መርሃ - ግብር በኢትዮጵያ ብሔራዊ መዝሙር ፊፃሜውን ማግኘቴ ችሏል።


‎በወላይታ ዞን በተፈጥሮ አደጋ ከቀያቸው የተፈናቀሉ ወገኖችን ለ 2ኛ ዙር መልሶ የማቋቋም መርሃግብር እየተደረገ ነው‎‎ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም በወላይታ ዞን በተፈጥሮ አደጋ ከቀያቸው ለተፈና...
03/09/2026

‎በወላይታ ዞን በተፈጥሮ አደጋ ከቀያቸው የተፈናቀሉ ወገኖችን ለ 2ኛ ዙር መልሶ የማቋቋም መርሃግብር እየተደረገ ነው

‎ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም

በወላይታ ዞን በተፈጥሮ አደጋ ከቀያቸው ለተፈናቀሉ ወገኖች 2ኛ ዙር መልሶ ለማቋቋም በተዘጋጀው ቦታ የማስፈር መርሃግብር እየተደረገ ይገኛል።

‎ከተረጂነት ወደ ምርታማነት በሚል ዕሳቤ የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋዎችን በራስ አቅም ለመሸፈን ታቅዶ እየተሰራ ይገኛል።

‎በዚህም በዞኑ ካዎ ኮይሻ ወረዳ በተከሰተው በመሬት መንሸራተት እና ናዳ ምክንያት ከቀያቸው ለተፈናቀሉት ወገኖች በአበላ አባያ ወረዳ አባያ ጮካሬ አባይ ኮይሻ መንደር ላይ "ሰፈራ ጣቢያ" ተዘጋጅቶ ሲሰራ መቆየቱ ይታወሳል።

‎ለዚህም ለተፈናቃዮች የመኖሪያ ቤት ግንባታ፣ የንፁህ መጠጥ ውሃ፣ የሕክምና ተቋማት፣ ትምህርት ቤት እና ሌሎች አስፈላጊ መሠረተ ልማትና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት በማሟላት በዛሬው ዕለት የማስፈር መርሃግብር በመካሄድ ላይ ይገኛል።

‎የሁለተኛ ዙር ተፈናቃዮች አቀባበል የተዘጋጀውን የመኖሪያ ቤት ርክክብ የሚደርግ ሲሆን የመኖሪያ ቤቱን የዞኑ አስተዳደር ህዝቡንና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማትን በማስተባበር የገነባ መሆኑን ተገልጿል።

‎የዞኑ አስተዳደር በተፈጥሮ አደጋ ከቀያቸው ለተፈናቀሉ ዜጎችን ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመቀናጀት በአጭር ጊዜ ውስጥ መልሶ ለማቋቋም ስራ ሲሰራ ቆይቷል።

‎ለሚሰፍሩ ዜጎች አከባቢው ምቹ እንዲሆን የዞኑ አስተዳደር አከባቢውን ከሚመለከታቸው አካላት ጋራ በመሆን ተቀናጅተው የማልማትና የማስዋብ ስራም ሰርቷል።

‎የነዋሪዎቹን ሠላምንና ደህንነትን ለማስጠበቅ ከአጎራባች አከባቢዎች ጋር በመሆኑ በቅንጅት መሰራቱን እና አስፈላጊውን የሰው ኃይልና ሎጂስቲክ የማሟላት ስራም ተሰርቷል።

‎በመጀመሪያው ዙር ከ120 በላይ አባወራዎች መልሶ የማስፈር ስራ መሰራቱንም ይታወሳል።

‎በመርሃግብሩ የክልሉ የመንግስት ረ/ተጠሪ አቶ ንጋቱ ዳንሳ፣ የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ረዳት ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ፣ የወላይታ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ ዶ/ር አማረ አቦታ፣ የክልሉ አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር ወገነህ ብዙነህን ጨምሮ የክልልና የዞኑ ከፍተኛ አመራሮች እና ሌሎች ህብረተሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል።

የክልሉ ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ በወላይታ ሶዶ ከተማ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች ያስገነባውን የማምረቻ ሼድ ርክክብ አደረገነሐሴ 28/2019 ዓ.ም ቢሮው  ከ30 ሚሊዮን ብር በላይ በሚሆን ...
03/09/2026

የክልሉ ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ በወላይታ ሶዶ ከተማ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች ያስገነባውን የማምረቻ ሼድ ርክክብ አደረገ

ነሐሴ 28/2019 ዓ.ም

ቢሮው ከ30 ሚሊዮን ብር በላይ በሚሆን ወጪ በአርባምንጭ፣ ወላይታ ሶዶ እና ዲላ ከተሞች ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የማምረቻ ሼድ ማስገንባቱም ተመላክቷል።

በወላይታ ሶዶ ከታማ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተገነባው የማምረቻ ቦታ ለከተማ አስተዳደሩ የማስረከብ ስራም ተከናውኗል።

የክልሉ ንግድና ኢንዱስትሪ ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሰናይት ሰለሞን በርክክብ መርሃ ግብሩ ላይ የክልሉ መንግስት ለአምራች ኢንዱስትሪዎች ምቹ የስራ ቦታ ከማዘጋጀት ባሻገር ተኪ ምርት እንዲያመርቱ ለማስቻል መጠነ ሰፊ ስራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኝ ገልፀዋል።

ቢሮው ከክልሉ መንግስት ባገኘው የ30 ሚሊዮን ብር ገንዘብ ድጋፍ በወላይታ ሶዶ፣ በአርባምንጭ እና በዲላ ከተማ አስተዳደሮች ለአምራች ኢንዱስትሪዎች አገልግሎት የሚውል የማምረቻ ቦታ፣ የምርት ማከማቻ መጋዘን እንዲሁም አገልግሎት የሚሰጡ ህንፃዎች ያሉት ሼድ ማስገንባቱን ኃላፊዋ አብራርተዋል።

የማምረቻ ሼዱ በክልሉ የሚገኙ አምራች ኢንዱስትሪዎች እንዲጠናከሩ ያግዛል ያሉት ወ/ሮ ሰናይት ተኪ ምርት በማምረት የውጭ ምንዛሪ እንዲገኝ ከማድረግ አንፃር የጎላ አበርክቶ እንዳለውም አመላክተዋል።

መሠል ሼዶች በክልሉ በሚገኙ ዞኖች እንደሚገነቡ የገለፁት የቢሮው ኃላፊዋ በርካታ ወጣቶች በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ እንዲሰማሩ የማድረግ ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባም አሳስበዋል።

የወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር ንግድና ኢንዱስትሪ መምሪያ ኃላፊ አቶ ኃይሌ ስላስ በበኩላቸው በከተማ የተደራጁ ማህበራት ከፍተኛ ችግራቸው የማምረቻ ቦታ መሆኑን ገልፀው ቢሮው አስገንብቶ ያስረከበው የማምረቻ ሼድ ችግሩን በተወሰነ ደረጃ እንደሚቀርፈው ተናግረዋል።

መምሪያው ለተረከበው የማምረቻ ሼድ የመሠረተ ልማት በሟሟላት ውጤታማ ለሚሆኑ ማህበራት ፍትሃዊ በሆነ መንገድ እንደሚያስተላልፍም የመምሪያ ኃላፊው ጠቁመዋል።

በርክክብ መርሃ ግብሩ የቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሰናይት ሰለሞን፣ ምክትል የቢሮ ኃላፊዎች፣ የማኔጅመንት አባላትና የወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር አመራሮች ተገኝተዋል።

የክልሉ ጤና ቢሮ ከተጠሪ ተቋማት ጋር በመተባበር ለሁለት አቅመ ደካማ እናቶች ዘመናዊ መኖሪያ ቤት ግንባታ አስጀመረነሐሴ 28/2018 ዓ.ምየበጎነት ተግባራትን በማስፋፋት አቅመ ደካማ ወገኖችን...
03/09/2026

የክልሉ ጤና ቢሮ ከተጠሪ ተቋማት ጋር በመተባበር ለሁለት አቅመ ደካማ እናቶች ዘመናዊ መኖሪያ ቤት ግንባታ አስጀመረ

ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም

የበጎነት ተግባራትን በማስፋፋት አቅመ ደካማ ወገኖችን የመደገፍ ባህል ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታውቋል።

የክልሉ ጤና ቢሮ ከህብረተሰብ ጤና ኢንስትቲዩት ጋር በመቀናጀት በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በደቡብ ኦሞ ዞን በና ጸማይ እና በማሌ ወረዳ ቃቆና በነታ ማዘጋጃ ቤቶች ለአቅመ ደካማ እናቶች ዘመናዊ ቤት የማስገንባት ሥራ በይፋ አስጀምሯል።

የክልሉ ጤና ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊና ጤና ፕሮግራሞች ዘርፍ ኃላፊ አቶ መና መኩሪያ መንግስት ለዜጎች ክብር የሰጠውን ሰው ተኮር ተግባርን ተግባራዊ እያደረጉ መሆናቸውን ገልፀዋል።

በማይመች ኑሮ ሁኔታ ውስጥ ያሉ ወገኖችን በመለየትና በመደገፍ የተጀመረው በጎነት የአከባቢው ማህበረሰብ እንዲያስቀጥል አቶ መና ጠይቀዋል።

የክልሉ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስትቲዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ አጉኔ አሾሌ በበኩላቸው በመተባበር የክረምቱን የበጎ ፈቃድ ስራዎች በማስፋት ለአቅሜ ደካማ እናቶች እየተደረገ ያለው የቤት ግንባታ እስኪጠናቀቅ ያማይቋረጥ ክትትል እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል።

በደቡብ ኦሞ ዞን ማሌና በበና ጸማይ ወረዳዎች ለተመረጡ 2
አቅመ ደካማ እናቶች የተጀመረው ቤት ግንባታ ለዘመናት የነበረባቸውን የመኖሪያ ቤት ችግር እንደሚቀርፍ ዳይሬክተሩ ተናግረዋል።

የቤት ግንባታ የተጀመረላቸው አቅመ ደካማ እናቶች ወ/ሮ አርዲ ዶቃ እና ወ/ሮ አባለች ኪቴ ለተደረገላቸው በጎ ተግባር ታላቅ ደስታ እንደተሰማቸው ተናግረዋል።

“ፈጣሪ ተመልክቶናል፤ ከዘመናት መከራችን ታድጎናል ስደገፋችሁን ፈጣሪ ያክብራችሁ” ሲሉ የክልሉን ጤና ቢሮ አመስግነዋል።

በመርሃግብሩ የበና ጸማይ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዮሐንስ ጋርሾ እና የማሌ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አልጋጋ ባለንሲ የጤና ቢሮና ተጠሪ ተቋማቱ በወረዳው ለተደረገ ታላቅ ተግባር ምስጋና ችረዋል።

አቅመ ደካሞችን በመለየት ቤታቸው እንዲሰራ መደረጉ ለአመታት ከነበረባቸው የቤት ችግር የሚያላቅቅ ታላቅ ወገናዊ ተግባር መሆኑን ዋና አስተዳዳሪዎቹ ገልጸዋል።

ዋና አስተዳዳሪዎቹ ተቋማቱ በመቀናጀት በወረዳዎቹ ያስጀመሩት የበጎነት ተግባር ቁርጠኝነትን አድንቀዋል።

በመርሃ ግብሩ የክልሉ ጤና ቢሮ እና ሕብረተሰብ ጤና ኢንስትቲዩት አመራሮችና ማናጅመንት አካላት፣ የማሌና በናፀማይ ወረዳ አስተዳዳሪዎችና የአከባቢ ነዋሪዎች ተግኝተዋል።

በጋርዱላ ዞን ዲራሼ ወረዳ የማጠቃለያ የዕርቀ ሠላም ኮንፍራንስ እየተካሄደ ይገኛልነሐሴ 28/2018 ዓ.ምበጋርዱላ ዞን ዲራሼ ወረዳ "ሠላም ለሁሉም ሁሉም ለሠላም" በሚል መሪ ቃል የዕርቀ ሠላ...
03/09/2026

በጋርዱላ ዞን ዲራሼ ወረዳ የማጠቃለያ የዕርቀ ሠላም ኮንፍራንስ እየተካሄደ ይገኛል

ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም

በጋርዱላ ዞን ዲራሼ ወረዳ "ሠላም ለሁሉም ሁሉም ለሠላም" በሚል መሪ ቃል የዕርቀ ሠላም የማጠቃለያ ኮንፍራንስ በመካሄድ ላይ ይገኛል።

በጋርዱላ ዞን ዲራሼ ወረዳ የማጠቃለያ የዕርቀ ሠላም ኮንፍራንስ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልና የጋርዱላ ዞን ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የኃይማኖት አባቶች፣ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍል ተወካዮች በተገኙበት በወረዳው በኦርጊሌ ቀበሌ ማዕከል ላይ በመካሄድ ላይ እየተካሄደ ነው።

ኮንፍራንሱ በተለያዩ የሀይማኖት አባቶች ፀሎት እና በአከባቢው ታላላቂ የባህል አባቶች ቡራከም ነው የተጀመረው።

የዕርቀ ሠላም ኮንፍራንሱ በአከባቢው የተፈጠረውን አንፃራዊ ሠላምን አልምቶ በዘላቂነት ለማረጋገጥ ያለሜ መሆኑም ተመላክቷል።

የማጠቃለያ የዕርቅ ኮንፍራንሱ በዞኑ ከዚህ ቀደም በየደረጃው በሚገኙ መዋቅሮች ላይ ሲካሄዱ የቆዩ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት የተግባቦት ውጤቶችን መነሻ በማድረግ እየተከናወነ ያለ እንደሆነም ተጠቅሷል።

በኮንፍራንሱ ላይ የተጋጩ ሰዎች በይፋ በአደባባይ የዕርቅ ስነ - ስርዓትን እንደሚፈፅሙ፤ የዕለቱ ዕርቅ እንድፀና የወጡ የአቋም መግለጫዎች እንደሚደመጡ፤ የምስክር ወረቀት አሰጣጥ ፕሮግራም እንደሚኖር፤ በመጨረሻም የማጠቃለያ መልዕክትና የቀጣይ የሥራ መመሪያዎች ከተሰጡ በኃላ የኮንፍራንሱ አጠቃላይ መርሃ - ግብር በሀይማኖት አባቶች ፀሎት እና በታላላቂ የባህል አባቶች ቡራከ እና የቀጣይ መልካም ምልጃ እንደሚጠቃለል ለዕለቱ የወጣው መርሃ - ግብር አመላክቷል።

በመርሃ ግብሩ ላይ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፌ -ጉባኤ የተከበሩ አቶ አዳማ ትንጳዬ፣ የክልሉ ሠላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ አበነዘር ተረፈ፤ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ፍሰሀ ጋርደው ጨምሮ ሌሎችም የክልል እና የዞን ከፍተኛ አመራሮች፣ ታላላቂ የባህል አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ ከሩቅም ከቅርብም የመጡ የአከባቢው ምሁራን፤ ከወረዳውወ ከየቀበሌያቱ የተወጣጡ የህብረተሰብ ክፍሎች፣ የአጎራባች ዞኖች ተወካዮች እንደዚሁም ሌሎችም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

!

የርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ መልዕክትየሰብዓዊ ድጋፍ ሉዓላዊነትን በማረጋገጥ ወደ ተሟላ ሀገራዊ ክብርና ሉዓላዊነት ለመሸጋገር የተያዘው ሀገራዊ እና ክልላዊ ግብ፤ የሉዓላዊነት ጥያቄ ብቻ ...
03/09/2026

የርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ መልዕክት

የሰብዓዊ ድጋፍ ሉዓላዊነትን በማረጋገጥ ወደ ተሟላ ሀገራዊ ክብርና ሉዓላዊነት ለመሸጋገር የተያዘው ሀገራዊ እና ክልላዊ ግብ፤ የሉዓላዊነት ጥያቄ ብቻ ሳይሆን ከሰው ልጅ ህይወት ጋር የተሳሰረ የህልውና ጉዳይ በመሆኑ፤ በየደረጃው ያለው አመራር በክልሉ ለዚሁ ግብ ስኬት በመከናወን ላይ የሚገኙ ዘርፈ ብዙ ተግባራትን ከተለምዷዊ አሰራሮች ወጣ ባለ መልኩ ብዝኃ ታታሪነትንና የተሟላ የአመራር ብቃትን ተላብሶ፤ በከፍተኛ ፖለቲካዊ ቁርጠኝነት በመምራት እና ሕዝባዊ ተሳትፎን ባረጋገጠ መልኩ በማስፈፀም በተቀመጠው ጊዜ ውስጥ ከግብ ለማድረስ ከምን ጊዜውም በላይ የተቀናጀ ርብርብ ማድረግ ይገባዋል፡፡

ለዚህ የሕዝባችንን ድንቅ የመተሳሰብና የመደጋገፍ እሴቶች በአግባቡ ተጠቅሞ ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍሎች፡- መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት፤ የልማት ማህበራትና ድርጅቶች፤ የኃይማኖት ተቋማት፤ መንግስት ሠራተኛውንና የንግዱን ህብረተሰብ፤ አርሶና አርብቶ አደሩን እና ሌሎች ባለድርሻ አካላትን በንቅናቄ በማሳተፍ ተግባራትን በጠንካራ ተቋማዊ ማዕቀፍ አልቆ በመፈፀምና በማስፈፀም ለውጤት ማብቃት ያስፈልጋል፡፡

ለተሻለ ነገ ዛሬን በኅብረት እንትጋ!!

ጥላሁን ከበደ
ርዕሰ መስተዳድር

Address

S**o

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when South Ethiopia Region Prosperity Party - የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share