South Ethiopia Regional State Office Of The President

South Ethiopia Regional State Office Of The President ይህ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት ትክክለኛ የፌስቡክ ገፅ ነው።
(6)

"ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የዜጎች ጤናን ማስጠበቅ ላይ ትኩረት ሰጥቶ መስራት ይገባል"- አቶ እንዳሻው ሽብሩየደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የ 2018 በጀት ዓመት የጤና ልማትና ኢን...
04/08/2026

"ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የዜጎች ጤናን ማስጠበቅ ላይ ትኩረት ሰጥቶ መስራት ይገባል"- አቶ እንዳሻው ሽብሩ

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የ 2018 በጀት ዓመት የጤና ልማትና ኢንቨስትመንት ዕቅድ አፈፃፀም መድረክ በአርባ ምንጭ ከተማ ተካሂዷል።

በበጀት ዓመቱ የእናቶችና ህፃናት ጤና፣ ወረርሽኝ መከላከልና መቆጣጠር፣ ጥራት ያለው የጤና አገልግሎትና ተጠቃሚነት፣ እንዲሁም ነባርና አዳዲስ ወረርሽኞችን መከላከል ላይ የተሰራዉ ስራ አበረታች መሆኑ ተገልጿል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ እንዳሻው ሽብሩ በመዋቅሮች መካከል የሚስተዋለውን የአፈፃፀም ልዩነት ማቀራረብ እንደሚገባ ተናግረዋል።

በክልሉ በሚከናወኑ የጤና ልማት ስራዎች ሕብረተሰቡን ባለቤትና ተሳታፊ ማድረግ ይገባል ያሉት ኃላፊው ለአብነትም 83 የማህበረሰብ ፋርማሲዎችን በሕብረተሰቡና በአጋር አካላት ትብብር ብቻ መገንባት እንደተቻለ ጠቁመዋል።

በክልሉ 43 ወረዳዎች የሰቆጣ ስምምነትን ተግባራዊ በማድረግ የህፃነት መቀንጨርና የስርዓተ- ምግብ ችግሮችን ለመፍታት በመሠራት ላይ መሆኑን አስረድተዋል።

የሌማት ትሩፋት ስራዎችን ከማህበረሰብ የጤና መድህን እና ከህፃናት መቀንጨር ችግሮች ጋር በማስተሳሰር ለመፍትሄዉ መስራት ይገባል ብለዋል።

ጤናማ ህብረተሰብ ሳይኖር ዘላቂ ልማትን ማረጋገጥ አይቻልም ያሉት ኃላፊዉ ለሁለንተናዊ ብልጽግና መረጋገጥ የዜጎችን ጤና ማስጠበቅ ላይ በትኩረት መስራት እንደሚገባ አመልክተዋል።

በበጀት ዓመቱ 1.39 ሚሊዮን ሴቶች የቤተሰብ ዕቅድ አገልግሎት እንዲያገኙ በቅንጅት መሠራቱ ተመልክቷል።

በክልሉ የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አገልግሎት ተጠቃሚዎችን ጠቅላላ ሽፋን 1.01 ሚሊዮን በላይ ማድረስ እንደተቻለም አስረድተዋል።

በሕብረተሰብ ጤና ላይ አደጋ ሊያደርሱ የሚችሉ ነባርና አዳዲስ በሽታዎች፤ ወረርሽኝ እና የተፈጥሮ አደጋ ክስተቶችን አስቀድሞ በመለየትና ምላሽ የመስጠት አቅም መገንባት ተችሏል ብለዋል።

በበጀት ዓመቱ የክልሉ ጤና ቢሮ ላከናወናቸው አመርቂ ስራዎች ዕዉቅና መስጠት እንደሚገባ የመድረኩ ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት ገልፀዋል።

ጠንካራ የድጋፍና ክትትል ስራ መስራት፣ ግንባታቸዉ የተጓተቱ የጤና ተቋማትን ማጠናቀቅ፣ የህፃናት መቀንጨርና የስርዓተ ምግብ ችግሮች ላይ ከታች ጀምሮ መስራት፣ የወባ ስርጭትና መከላከል ላይ በቅንጅት መስራት እንደሚገባ ጠቁመዋል።

በመድረኩ የክልሉ ጤና ቢሮ የ 2019 በጀት ዓመት ጠቋሚ ዕቅድ ላይ ዉይይት በማድረግ የጋራ ተደርጓል።

በመድረኩ የክልሉ መንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ የክልሉ ጤና ቢሮ የማኔጅመንት አባላት፣ የጤና መምሪያ ኃላፊዎች፣ ከፍተኛ ባለሙያዎችና ባለድርሻ አካላት ተሳታፊ ሆነዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ የ2018 ዓ.ም የ8ኛ እና የ6ኛ ክፍል ውጤት ይፋ አደረገ ቢሮው ውጤቱን አስመልክቶ ለጋዜጠኞች መግለጫ ሰጥቷል።መግለጫውን የሰጡት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል...
04/08/2026

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ የ2018 ዓ.ም የ8ኛ እና የ6ኛ ክፍል ውጤት ይፋ አደረገ

ቢሮው ውጤቱን አስመልክቶ ለጋዜጠኞች መግለጫ ሰጥቷል።

መግለጫውን የሰጡት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አብዮት ደምሴ፤ የ2018 ዓ.ም የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ማለፊያ ነጥብ ክልላዊ 50 እና ከዚያ በላይ ሲሆን ድጋፍ ለሚሹ ደግሞ 48 እና በላይ ማለፊያ ነጥብ ተቆርጦለታል ብለዋል።

በዚህ መሠረት 8ኛ ክፍል መደበኛ፣ የግል፣ ማታ እና ርቀት ተብሎ ተከፍሎ ውጤቱ መቀመጡን ሀላፊው በመግለጫቸው አብራርተዋል።

በመሆኑ አጠቃላይ 8ኛ ክፍል የተመዘገቡ 86 ሺህ 502 ሲሆኑ የተፈተኑ 78 ሺህ 203 ከእነዚህ ውስጥ 50ና በላይ እንዲሁም 48 እና በላይ ውጤት ያስመዘገቡና ቀጣይ ክፍል ያለፉ 47 ሺህ 307 ናቸው ብለዋል አቶ አብዮት።

በዚህ መሠረት ክልላዊ ውጤት ከመቶ ሲታይ 60 ነጥብ 4 ነው ብለዋል።

በተመሳሳይ የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ለመውሰድ የተመዘገቡ 126 ሺህ 224 ሲሆኑ ፈተና የወሰዱ ደግሞ 110 ሺህ 566 ከእነዚህ ደግሞ ማለፊያ ነጥብ አስመዝግበው ወደ ቀጣይ 7ኛ ክፍል የተዛወሩ 70 ሺህ 584 ናቸው ሲሉም የቢሮ ሀላፊ አብራርተዋል።

በዚህም ክልላዊ ውጤት በመቶ ሲገለፅ 63 ነጥብ 8 እንደሆነ ተገልጿል።

የ8ኛ ክፍል በትምህርት ቤት ደረጃ ሲገለፅ 540 ትምህርት ቤቶች ሙሉ በሙሉ ተመሪዎችን ማሳፍ ሲችሉ 155 ትምህርቶች ደግሞ ምንም ተማሪ አለማሳየታቸውን አቶ አብዮት ገልፀዋል።

በተመሳሳይ የ6ኛ ክፍል 476 ትምህርት ቤቶች ሙሉ በሙሉ ሲያሳልፉ 81 ትምህርት ቤቶች ደግሞ ምንም ተማሪ አላሳለፉም ብለዋል ሀላፊው።

አጠቃላይ ክልላዊ ውጤቱ ከአምና የትምህርት ዘመን ውጤት ጋር ሲነፃፀር የ8ኛ ክፍል 3 በመቶ በማነስ ተመዝግቧል ሲሉም የቢሮ ሀላፊ ተናግረዋል።

ይህ አምና ክልላዊ ውጤት በመቶ 63 በመቶ እንደነበር ተገልጿል።

በተመሳሳይ የ6ኛ ክፍል አምና ክልላዊ ውጤት 56 በመቶ የነበረ ሲሆን በ2018 ደግሞ 63 ነጥብ 84 እንደሆነም ተገልጿል።

ተማሪዎችም በዚህ ሊንክ ገብተው ውጤታቸውን መመልከት እንደሚችሉ ተገልጿል።

https://se.ministry.et/ #/result

https://se6.ministry.et/ #/result

“ክልሉ ወረርሽኞችን መቆጣጠር የቻለ ጠንካራ የጤና ተቋም እና አገልግሎት ሰጪ የጤና ተቋማትን ገንብቷል " አቶ ተፈሪ አባተ የክልሉ ጤና ቢሮ  ያዘጋጀው የምክክር መድረክ በአርባ ምንጭ ከተማ ...
04/08/2026

“ክልሉ ወረርሽኞችን መቆጣጠር የቻለ ጠንካራ የጤና ተቋም እና አገልግሎት ሰጪ የጤና ተቋማትን ገንብቷል " አቶ ተፈሪ አባተ

የክልሉ ጤና ቢሮ ያዘጋጀው የምክክር መድረክ በአርባ ምንጭ ከተማ እያካሄደ ይገኛል

በክልሉ ከ1 ሚሊዮን 18 ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አገልግሎት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረግ መቻሉም ተጠቁሟል።

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የወላይታ ሶዶ ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተፈሪ አባተ በመድረኩ መክፈቻ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት በክልሉ የሚገኙ የጤና ተቋማት ከፈውስ ህክምና ባሻገር ለበሽታ መከላከል ስራ ትኩረት ሊሰጡ እንደሚገባ ገልፀዋል።

የጤና ሴክተር ተግባር በክልሉ ለሚከናወኑ ሁሉም ተግባራት ቁልፍ ነው ያሉት ኃላፊው ለስኬታማነቱ በተቀናጀ መልኩ መረባረብ እንደሚገባ አመላክተዋል።

ቢሮው ከአጋር ድርጅቶች ጋር በመቀናጀጀት በክልሉ ተከስቶ የነበረውን የኮረና ቫይረስ የተቆጣጠረበት ሂደት የሚደነቅ መሆኑን የተናገሩት አቶ ተፈሪ ይህን ልምድ በመጠቀም የወባ በሽታን ለመቆጣጠር በልዩ ትኩረት መስራት እንደሚገባም አሳስበዋል።

በቀጣይ ተላላፊና ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን የመቆጣጣር እና በህገ ወጥ መንገድ ወደ ክልሉ የሚገቡ የህክምና ግብዓቶችን የመቆጣጠር ስራን በትኩረት መስራት እንደሚገባም አቶ ተፈሪ አባተ በመልዕክታቸው አብራርተዋል።

የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ እንዳሻው ሽብሩ በበኩላቸው ዜጎች ጤንነታችው ተጠብቆ ብሩህ፣ ትጉህ እና አምራች ዜጋ ሆነዉ ማየት ቢሮው ከሚሰራቸው ተግባራት መካከል ዋነኛው መሆኑን ገልፀዋል።

ጤናማ ህብረተሰብ ሳይኖር ዘላቂ ልማትን ማረጋገጥ አይቻልም ያሉት ኃላፊዉ ለሁለንተናዊ ብልጽግናና የኢኮኖሚ ዕድገት መሠረት መሆኑን ተገንዝቦ የዜጎችን ጤና ማስጠበቅ በልዩ ትኩረት መስራት እንደሚገባ አመልክተዋል።

በ2018 በጀት ዓመት የእናቶችና ሕፃናትን ጤና ማሻሻል፣ ሞትና ህመምን መቀነስ፣ ጥራት ያለው የጤና አገልግሎትና ተጠቃሚነትን በማረጋገጥ ረገድ እንደ ክልል የተሻለ አፈፃፀም ተመዝግቧል ብለዋል፡፡

በበጀት ዓመቱ 1.39 ሚሊዮን ሴቶች የቤተሰብ ዕቅድ አገልግሎት ተጠቃሚ እንዲሆኑ በቅንጅት መሠራቱንና ከባለፈዉ ዓመት ተመሳሳይ ወቅት አንፃር የ 9 በመቶ ጭማሪ ማሳየቱን ጠቁመዋል።

በክልሉ የወባ በሽታ ህመም ምልክት አሳይተው ከተመረመሩት 2.9 ሚሊዮን ህሙማን ዉስጥ 1.06 ሚሊዮን ሰዎች የወባ በሽታ ተገኝቶባቸው ተገቢውን የሕክምና አገልግሎት ማግኘታቸውንም አብራርተዋል።

በክልሉ የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አገልግሎት ተጠቃሚዎችን ጠቅላላ ሽፋን 1.01 ሚሊየን በላይ ማድረስ እንደተቻለም አስረድተዋል።

በበጀት ዓመቱ ከ 53 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ህገ ወጥ መድኃኒቶች በቁጥጥር በማስወገድ የዜጎች ደህንነት ማስጠበቅ መቻሉን አቶ እንዳሻዉ ጠቁመዋል።

በሕብረተሰብ ጤና ላይ አደጋ ሊያደርሱ የሚችሉ ነባርና አዳዲስ በሽታዎች፤ ወረርሽኝ እና የተፈጥሮ አደጋ ክስተቶችን አስቀድሞ በመለየትና ምላሽ የመስጠት አቅም መገንባት ተችሏል ብለዋል።

በክልሉ ያጋጠመዉን የማርበርግ ቫይረስ ወረርሽኝ እና ድንገተኛ የተፈጥሮ መሬት ናዳና ጎርፍ አደጋ ለመከላከል የተቋቋመውን የክስተት አስተዳደር ግብረኃይል በመምራት ብሎም ለተመዘገበው ዉጤት ለክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ ምስጋና አቅርበዋል።

በመድረኩ በቢሮው የአገልግሎት ዘመናቸው ተጠናቆ በማህበራዊ ዋስተና የተገለሉ ሰራተኞች የክብር ሽኝት የሀደረገላቸው ሲሆን የተቋሙ የ2018 በጀት ዓመት አፈፃፀም እየቀረበ ይገኛል።

"በመኸር እርሻ ወቅት የወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራ እንቅስቃሴ ሊጠናከር ይገባል " ምክትል ርዕሰ መስተዳደር እና የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር )  ምክትል ርዕሰ መስተዳደ...
04/08/2026

"በመኸር እርሻ ወቅት የወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራ እንቅስቃሴ ሊጠናከር ይገባል " ምክትል ርዕሰ መስተዳደር እና የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር )

ምክትል ርዕሰ መስተዳደር እና የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) በመኸር እርሻ ወቅት የወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራ እንቅስቃሴ እንዲጠናከር መልእክት አስተላለፉ

​ምክትል ርዕሰ መስተዳደሩ ወጣቶችን በስፋት ወደ ሥራ በማሰማራት የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እና የኢኮኖሚ ተሳትፏቸውን ለማሳደግ የተጀመረው የመኸር እርሻ እንቅስቃሴ በላቀ ደረጃ መጠናከር እንዳለበት ጥሪ አቀረቡ።

በተለይም በመኸር፣ በበጋ መስኖ እንድሁም በበልግ እርሻ ልማት ላይ ሰፊ የሥራ ዕድል መኖሩን በመጠቆም፣ ወጣቶች በተደራጀ መልኩ ወደ ተግባር በመግባት የሚፈጠሩ የልማት አማራጮችን በአግባቡ እንዲጠቀሙ ዶ/ር አበባየሁ አሳስቧል።

በዚህም መሰረት በየዞኑ፣ ወረዳውና ቀበሌው የሚገኙ የዘርፍ አመራሮችና ባለሙያዎች ወጣቶችን የመለየት፣ የማደረጀትና ለተደራጁ ወጣቶች ለሥራቸው የሚያስፈልጉ ልዩ ልዩ ግብአቶችን እና የመሬት አቅርቦት አሰራርን ማመቻቸት የዚህ ጥሪ ዋና አካል ነው።

ስለሆነም በየደረጃው ያሉ መዋቅሮች በከተማ አንድ ሄክታር እንዲሁም በገጠር 6 ሄክታር መሬት ለወጣቶች አስተላልፎ የመስጠት ግዴታቸውን እንዲወጡ፤ ጎን ለጎንም ለልማቱ የሚሆኑ የብድር አገልግሎቶችን፣ የምርጥ ዘር፣ የማዳበሪያ እና የመስኖ ውሃ መሳቢያ መሳሪያዎች አቅርቦትን በፍጥነት እንዲያመቻቹ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

​በመጨረሻም ምክትል ርዕሰ መስተዳደሩ፣ በክልሉ የሥራ ፈጠራ ምክር ቤት የተላለፉ ውሳኔዎችን በየደረጃው የሚገኙ አካላት ወደ ተግባር እንዲለውጡና ድርሻቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል። በተጨማሪም ከላይ ከተጠቀሱት ድጋፎች ባሻገር ለልማቱ የሚሆኑ የትራክተር፣ የብድር እና ሌሎች አስፈላጊ አቅርቦቶችን በፍጥነት እንዲያመቻቹ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

ይህ የተቀናጀ የክትትልና ድጋፍ አሰራር ወጣቶች በተሰማሩበት የእርሻ ልማት ላይ ዘላቂና ተጨባጭ ውጤት እንዲያስመዘግቡ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ስለሚኖረው፣ ሁሉም መዋቅር ለተግባራዊነቱ በቁርጠኝነት መስራት ይኖርበታል።

የክልሉ ጤና ቢሮ በ2018 የጤና ልማትና ኢንቨስትመንት አፈፃፀምና በ2019 በጀት ዓመት ጠቋሚ ዕቅድ ዙሪያ የምክክር መድረክ እያካሄደ ይገኛል የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ በ2018 በጀት...
04/08/2026

የክልሉ ጤና ቢሮ በ2018 የጤና ልማትና ኢንቨስትመንት አፈፃፀምና በ2019 በጀት ዓመት ጠቋሚ ዕቅድ ዙሪያ የምክክር መድረክ እያካሄደ ይገኛል

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ በ2018 በጀት ዓመት የጤና ልማትና ኢንቨስትመንት እቅድ አፈፃፀምና በ2019 በጀት ዓመት ጠቋሚ ዕቅድ ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር በአርባ ምንጭ ከተማ የምከክር መድረክ እያካሄደ ነው።

በመድረኩ የ2018 በጀት አመት አፈፃፀምና የቀጣይ በጀት ዓመት ጠቋሚ ዕቅድ ቀርቦ ምክክር እንደሚደረግበት ከወጣው መርሃ ግብር ለማወቅ ተችሏል።

በመርሃ ግብሩ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የወላይታ ሶዶ ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተፈሪ አባተን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች፣ የዞን አስተዳዳሪዎች፣ የሪጂዮ ፖሊስ ከተማ አስተዳደር ከንቲባዎች የጤና መዋርቅ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች እንዲሁም ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ይገኛል።

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በክልሉ 76 ሚሊዮን ችግኝ በመትከል ታሪክ መሰራቱን ተከትሎ ለክልሉ ህዝብ የምስጋና መልዕክት አስተላልፈዋል "በኅብረት የተስፋ አሻራችንን በማኖር ዳግም ታሪክ ...
03/08/2026

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በክልሉ 76 ሚሊዮን ችግኝ በመትከል ታሪክ መሰራቱን ተከትሎ ለክልሉ ህዝብ የምስጋና መልዕክት አስተላልፈዋል

"በኅብረት የተስፋ አሻራችንን በማኖር ዳግም ታሪክ መስራት ችለናል!

ዛሬ ሐምሌ 27/2018 ዓ/ም በሀገራዊው የአረንጓዴ አሻራ የአንድ ጀንበር ተከላ በክልላችን ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸውን 69 ሚሊዮን ችግኞች ለመትከል አቅደን፤ ተፈጥሮን መጠበቅ የህልውና ጉዳይ መሆኑን በውል በተረዳው የክልላችን ህዝብ ንቁ ተሳትፎ ለመጪው ትውልድ የተስፋ አሻራችንን ለማኖር በጋራ ባደረግነው ርብርብ ከዕቅድ በላይ 76 ሚሊዮን ችግኞች በመትከል እንደ ሀገር ዳግም ለአለም ተምሳሌት የሆነ ታሪክ መስራት በመቻላችን የተሰማኝን ልባዊ ደስታ እየገለጽኩ ለመላው የክልሉ ህዝብ የላቀ ምስጋናዬን ለማቅረብ እወዳለሁ፡፡

በዕለቱ በመላዉ የክልላችን ህዝቦች ፅናት እና ትጋት ለተመዘገበው ስኬት በማስተባበርና በመምራት ጉልህ አስትዋጽኦ ላበረከታችሁ እንዲሁም ከማለዳ እስከ ምሽት በትጋት ለተከላችሁ በሙሉ ዳግም ልባዊ ምስጋናዬን እያቀረብኩ፤ በቀጣይ የተተከሉትን በመንከባከብና በመጠበቅ ደህንነቱ የተጠበቀ አረንጓዴ ከባቢን ለትውልድ ለማሻገር እንድንተጋ ከአደራ ጭምር አሳስባለሁ፡፡

ፈጣሪ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿን ይባርክ!!"

ጥላሁን ከበደ
ርዕሰ መስተዳድር

በዘንድሮ ዓመት እስካሁን 6 ነጥብ 5 ቢሊዮን በላይ ችግኞች ተተክለዋል ፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዛሬው ዕለት በመላው ኢትዮጵያ የ...
03/08/2026

በዘንድሮ ዓመት እስካሁን 6 ነጥብ 5 ቢሊዮን በላይ ችግኞች ተተክለዋል ፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዛሬው ዕለት በመላው ኢትዮጵያ የተካሄደውን የአንድ ጀንበር የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር በስኬት መጠናቀቅ አስመልክተው የማጠቃለያ መልዕክት አስተላልፈዋል።

በመልዕክታቸውም ኢትዮጵያ በተያዘላት ዕቅድ መሠረት በአንድ ቀን ብቻ 805.3 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል ወደር የማይገኝለት ታሪካዊ ስኬት ማስመዝገቧን አረጋግጠዋል።

ከ26 ሚሊዮን በላይ የሚሆን የኢትዮጵያ ሕዝብ ምንም ዓይነት ክፍያ ሳይጠይቅ፣ አብዛኛው በዝናብ ውስጥ ሙሉ ቀን ችግኝ እየተከለ መዋሉ በዋዛ ፈዛዛ ሊተገበር የሚችል ቀላል ተግባር አለመሆኑንም ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአጽንኦት ተናግረዋል።

ይህን ታላቅ ሀገራዊ ኃላፊነት በከፍተኛ ጽናትና ቁርጠኝነት የተወጣውን መላውን የኢትዮጵያ ሕዝብ ከልብ ያመሰገኑት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፣ በዚሁ ልክ ተደምረን እና በአንድነት ቆመን ለነገው ትውልድ ተስፋን መትከላችን ከፍተኛ ሞራልና መነሳሳት የፈጠረ መሆኑን አስረድተዋል።

በዘንድሮ ዓመት እስካሁን 6 ነጥብ 5 ቢሊዮን በላይ ችግኞች መተከላቸውን ገልጸው፣ ቀሪው 1.5 ቢሊዮን ችግኞች በቀሪ ወራት የሚፈጸም ይሆናል ብለዋል።

በክልሉ እየተካሄደ ከሚገኘው  የአንድ ጀንበር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በምስል-
03/08/2026

በክልሉ እየተካሄደ ከሚገኘው የአንድ ጀንበር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በምስል-

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በጋሞ ዞን ለተፈናቃዮች እየተገነባ በሚገኘው መልሶ ማቋቋሚያ  መንደር አረንጓዴ አሻራቸውን አኑረዋል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በጋሞ ዞን በጋጮ ባባ ወረዳ...
03/08/2026

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በጋሞ ዞን ለተፈናቃዮች እየተገነባ በሚገኘው መልሶ ማቋቋሚያ መንደር አረንጓዴ አሻራቸውን አኑረዋል

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በጋሞ ዞን በጋጮ ባባ ወረዳ ማዞ ዶይሳ ቀበሌ በደረሰ የመሬት ናዳ ምክንያት የተፈናቀሉ ወገኖች እንዲሁም ስጋት ባለባቸው አካባቢዎች የሚኖሩ ህብረተሰብ ክፍሎች መልሶ ለማቋቋም በምዕራብ አባያ ወረዳ ዳልቦ ቀበሌ የቤት ግንባታ እየተካሄደ ይገኛሉ ።

ርዕሰ መስተዳድሩም በአረንጓዴ አሻራ ተከላቸው በመልሶ ማቋቋሚያ መንደር በመገኘት አረንጓዴ አሻራቸውን አኑረዋል።

ክቡር ርዕሰ መስተዳድሩ በዛሬው ዕለት የአንድ ጀንበር አረንጓዴ አሻራ ባስጀመሩበት ወቅት በአሁን ወቅት የአለም የአየር ንብረት መዛባት በሰው ልጅ ህልውና ላይ ከፍተኛ ስጋት ደቅኗል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ ኢትዮጵያ በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችን መሪነት የወሰደችው የአረንጓዴ አሻራ ፍቱን የመፍትሄ እርምጃ ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ተምሳሌት መሆን መቻሉን ገልፀዋል።

አረንጓዴ አሻራ የተራቆተ ሥነ-ምኅዳር መልሶ በማልማት፤ የአፈር ለምነትን በመጨመር እንዲሁም የገፀ ምድርና የከርሰ ምድር የውሀ ሀብታችንን በማጎልበት ተፈጥሮን ከማከምና ምርታማነትን ከማሳደግ ባለፈ የተፈጥሮ አደጋ ተጋላጭነትን ለመከላከል ሚናው ከፍተኛ መሆኑንም መናገራቸው ይታወሳል።

#ርዕሰመስተዳድርጽቤት

ከ21 ሚሊየን በላይ ዜጎች በ8 ሰዓታት ውስጥ 650 ሚሊየን ገደማ ችግኞችን ተክለዋል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐ...
03/08/2026

ከ21 ሚሊየን በላይ ዜጎች በ8 ሰዓታት ውስጥ 650 ሚሊየን ገደማ ችግኞችን ተክለዋል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአንድ ጀምበር የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር በመጀመሪያዎቹ 8 ሰዓታት ውስጥ ከ21 ሚሊየን በላይ ዜጎች 650 ሚሊየን ገደማ ችግኞችን ተክለዋል አሉ።

መርሐ ግብሩ የሕዝቡ ከፍተኛ ተሳትፎና የተግባር ቁርጠኝነት የታየበት መሆኑን ገልጸው፥ በቀሪው ሰዓታት 800 ሚሊየን ችግኞችን በመትከል ዕቅዳችንን ለማሳካት ይሰራል ነው ያሉት፡፡

አረንጓዴ ዐሻራ ከችግኝ ተከላ ባሻገር ተስፋን፣ አንድነትን፣ የሀገር ፍቅርን እና ለቀጣይ ትውልድ ዘላቂ ሀብት የመተው ዕሴትን የሚያጠናክር ሀገራዊ ንቅናቄ መሆኑን አስረድተዋል።

በመርሐ ግብሩ የአካባቢ ሥነ ምህዳርን ለመጠበቅ ሀገር በቀል የዛፍ ዝርያዎችን መትከል፣ የአፈር መሸርሸርን መከላከልና አረንጓዴ ሽፋንን ማስፋፋት ቀዳሚ ትኩረት መሆኑን ነው የገለጹት፡፡

የፍራፍሬ ችግኞችን በስፋት መትከል የምግብ ዋስትናን፣ የገቢ ፈጠራንና የውጭ ምንዛሪ ግኝትን ለማጠናከር ከፍተኛ ሚና እንዳለው አንስተዋል፡፡

በአቮካዶ ምርት የተመዘገበው የወጪ ንግድ መሻሻል የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ከአካባቢ ጥበቃ ባሻገር ለኢኮኖሚ እድገት የሚያበረክተውን አስተዋጽኦ የሚያሳይ ነው ብለዋል፡፡

በቀጣይም በዚህ ዘርፍ የበለጠ ውጤት ለማስመዝገብ ሰፊ ዕድል መኖሩን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ የሀገሪቱ የልማት ጉዞ ዘላቂ መሠረት የሚያገኘው የተፈጥሮ ሀብትን በመጠበቅና አረንጓዴ ልማትን በማስፋፋት መሆኑንም አመልክተዋል።

በዛሬው ዕለት በተለያዩ አካባቢዎች እስከ 100 ችግኞችን ለመትከል ዕቅድ እንዳላቸው የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ ሥራው አድካሚ ሊሆን ቢችልም በተገባው ቃል መሠረት ተስፋን ለመትከል ርብርብ ማድረግ እንደሚገባ ጥቁመዋል።

ይህም የአፈርና የአካባቢ ጥበቃንና የኢኮኖሚ ልማትን በአንድነት የሚያስቀጥል መሆኑን ጠቁመው፥ የተያዘው ዕቅድ እስከሚሳካ ድረስ ዜጎች በጽናት እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል።

Address

Wolaita S**o
S**o
1000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when South Ethiopia Regional State Office Of The President posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to South Ethiopia Regional State Office Of The President:

Shortcuts

Share