በወላይታ ዞን የብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት- Wolaita Zone Prosperity Party Branch office

  • Home
  • Ethiopia
  • Sodo
  • በወላይታ ዞን የብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት- Wolaita Zone Prosperity Party Branch office

በወላይታ ዞን የብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት- Wolaita Zone Prosperity Party Branch office we are in the community!

ጳጉሜ 1 — የእመርታ ቀንከተስፋ ወደ እመርታ!ሀገራችንን ከተረጂነት ለማላቀቅና በራሷ አቅም የምትቆም ኢትዮጵያን ለመገንባት የተያዘው የእመርታ አቅጣጫ ከቃል ባሻገር ወደ ተጨባጭ ተግባር እየተ...
06/09/2026

ጳጉሜ 1 — የእመርታ ቀን

ከተስፋ ወደ እመርታ!

ሀገራችንን ከተረጂነት ለማላቀቅና በራሷ አቅም የምትቆም ኢትዮጵያን ለመገንባት የተያዘው የእመርታ አቅጣጫ ከቃል ባሻገር ወደ ተጨባጭ ተግባር እየተቀየረ ይገኛል።

በምግብ ራስን መቻል፣ ምርታማነትን ማሳደግ፣ የሥራ ዕድል መፍጠርና ሀገራዊ ሀብትን ወደ ምርት መቀየር የዚህ የእመርታ ጉዞ ዋና አቅጣጫዎች ናቸው።

ይህንን ሀገራዊ ጉዞ በክልላዊ ደረጃ በማጠናከር፣ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ የሕዝቡን አቅምና ያሉትን የልማት ሀብቶች በማስተሳሰር ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ እየሠራ ይገኛል።

በግብርናና መስኖ፣ በቡናና ኮረሪማ፣ በኢንዱስትሪና ንግድ፣ በውሃና መንገድ ልማት፣ በትምህርትና ጤና፣ በአረንጓዴ ልማት፣ በቱሪዝምና ባህል፣ እንዲሁም በበጎ ፈቃድና የሕዝብ ተሳትፎ የተደረጉ ጥረቶች የእመርታው ጉዞ ተጨባጭ አካላት ናቸው።
እመርታ የአንድ ቀን ውጤት ሳይሆን፣ በየቀኑ በተግባር የሚፈጠር ውጤት ነው።

በአዲሱ ዓመትም የተጀመረውን የእመርታ ጉዞ የበለጠ ለማፋጠን፣ ክልላዊ አንድነታችንንና ትብብራችንን በማጠናከር ሁላችንም የየበኩላችንን አስተዋጽኦ በማበርከት ለእመርታው ጉዞ መረባረብ ይጠበቃል።

የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት እና ዋና ፅ/ቤት ኃላፊ ክቡር አቶ አደም ፋራህ የመጀመሪያው ዓለም አቀፍ የፖለቲካ ፓርቲዎች የምክክር መድረክ (Inter-Continental Dialogue ...
06/09/2026

የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት እና ዋና ፅ/ቤት ኃላፊ ክቡር አቶ አደም ፋራህ የመጀመሪያው ዓለም አቀፍ የፖለቲካ ፓርቲዎች የምክክር መድረክ (Inter-Continental Dialogue among Political Parties - ICDPP) ላይ ለመሳተፍ ሴኡል፣ ደቡብ ኮሪያ ገብተዋል።

ከሴፕቴምበር 6 እስከ 9 ቀን 2026 ዓ.ም በሚካሄደው በዚህ ከፍተኛ አለም አቀፍ ጉባኤ ላይ ከአፍሪካ፣ ኤሽያ፣ አውሮፓ፣ ላቲን አሜሪካ እና ሰሜን አሜሪካ የተወጣጡ የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎች ተሳታፊ ይሆናሉ ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን በአሁን ወቅት የተሳታፊዎች እንኳን በደህና መጣችሁ መርሃ ግብር እየተደረገ ይገኛል።

ጉባኤው በዓለም አቀፍ ደረጃ በፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል የጋራ ግንዛቤ እና ትብብር ማጠናከርን ዋና አላማው አድርጎ የተነሳ ሲሆን በቀጣይ ቀናት በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ይመክራል ተብሎ ይጠበቃል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት አዲስ ዓመትን ምክንያት በማድረግ ለ8 መቶ 40 የሕግ ታራሚዎች ይቅርታ አደረገርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት መጪውን አዲስ ...
06/09/2026

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት አዲስ ዓመትን ምክንያት በማድረግ ለ8 መቶ 40 የሕግ ታራሚዎች ይቅርታ አደረገ

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት መጪውን አዲስ ዓመት ምክንያት በማድረግ የይቅርታ አዋጁን መስፈርት ላሟሉ 8 መቶ 40 የሕግ ታራሚዎች ይቅርታ ማድረጉን አስታውቀዋል፡፡

ርዕሰ መስተዳድሩ ይቅርታ የተደረገላቸው የሕግ ታራሚዎች በማረሚያ ቤት ቆይታቸው መልካም ሥነ-ምግባር ያሳዩና በሕግ በተደነገገው አግባብ የይቅርታ መስፈርትን ማሟላታቸው በክልሉ መንግስት የይቅርታ ቦርድ ተጣርቶ የቀረቡ መሆናቸውን ገልፀዋል።

የሕግ ታራሚዎቹ በመደበኛ የይቅርታ ሕግ እና ሌሎች ተጨማሪ መስፈርቶችን የሚያሟሉ ተብለዉ በልዩ ሁኔታ የቀረቡ፤ በማረሚያ ቆይታቸው ስለመታረማቸውና ስለመታነፃቸው ማረጋገጫ የቀረበላቸው መሆኑንም ተናግረዋል፡፡

በዚሁ መሰረት የይቅርታው ተጠቃሚዎች በይቅርታ አሰጣጥ ሥነ-ሥርዓት አዋጅ እና አዋጁን ለማስፈፀም በወጣው ደንብ ይቅርታ በማያስከለክሉ ወንጀሎች ተሳትፈው፡-

በማረሚያ ቤት የቆዩ፤ በጤና ችግር፤ በዕድሜ መግፋትና ከሕጻናት ጋር አብረዉ የታሰሩ እንዲሁም ከተፈረደባቸው ሲሶ (1/3) እና ከግማሽ (1/2) በላይ የፍርድ ጊዜያቸውን ያጠናቀቁ መሆናቸውን ርዕሰ መስተዳድሩ አስረድተዋል።

የይቅርታ ተጠቃሚ ከሆኑት የሕግ ታራሚዎች መካከል 56ቱ ሴቶች ሲሆኑ፤ 7 መቶ 84 ደግሞ ወንዶች መሆናቸውን አመልክተዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ የይቅርታው ተጠቃሚ የሆኑ የሕግ ታራሚዎች የይቅርታን እሴት ተላብሰው ሰላም ወዳድ፣ ለሕግ ተገዥና አምራች ዜጋ በመሆን የበደሉትን ህብረተሰብ በማገልግል በልማት ሊክሱ እንደሚገባ አሳስበዋል።

ህብረተሰቡም ይቅርታ የተደረገላቸው የህግ ታራሚዎች በፈፀሙት ጥፋት የተፀፀቱና በአግባቡ ታርመው የወጡ መሆኑን በመረዳት መልካምና አምራች ዜጋ እንዲሆኑ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግላቸው ጥሪ አቅርበዋል።

‎ጳጉሜ-1 የእምርታ ቀን ‎‎እምርታ የወላይታ ሕዝብ የታሪክ፣ የማንነት፣ የተስፋና የአዲስ ዕይታ መገለጫ ነው። ይህ ቀን ያለፈውን በአክብሮት እያሰብን፣ የአሁኑን በትጋት እየገነባን፣ የወደፊቱ...
06/09/2026

‎ጳጉሜ-1 የእምርታ ቀን

‎እምርታ የወላይታ ሕዝብ የታሪክ፣ የማንነት፣ የተስፋና የአዲስ ዕይታ መገለጫ ነው። ይህ ቀን ያለፈውን በአክብሮት እያሰብን፣ የአሁኑን በትጋት እየገነባን፣ የወደፊቱን ደግሞ በአንድነትና በጋራ ራዕይ የምናቅድበት የእድሳት ቀን ነው።

‎እምርታ በተለይ ለእኛ የወላይታ ሕዝብ አንድ ትልቅ መልዕክት ይዞ ይመጣል፤ የተሻለ ነገ የሚገነባውም በዛሬ ተግባራችን ነው።

‎ዛሬ የወላይታ ዞን በመሠረተ ልማት፣ በግብርና፣ በከተማ ልማት፣ በትምህርት፣ በጤና፣ በቱሪዝምና በኢንቨስትመንት ዘርፎች የሚታይ እድገት እያስመዘገበ ነው። እነዚህ ለውጦች የመንግሥት ብቻ ውጤት ሳይሆኑ፣ የሕዝባችን ተሳትፎ፣ የወጣቶቻችን ጉልበት፣ የሴቶቻችን አስተዋፅዖ እና የባለሀብቶቻችን ትጋት የፈጠረው የጋራ ውጤት ነው።

‎በመሆኑም የእምርታ ቀንን ስናከብር በባህላዊ እሴቶቻችን ብቻ ሳንወሰን፣ የተማረ፣ የተደራጀ፣ የሰለጠነ፣ በሥራ የሚተጋና ለራሱ ብሎም ለአካባቢው ኢኮኖሚ አስተዋፅዖ የሚያደርግ ትውልድ ለመፍጠር ቃል የምንገባበት ወቅት ሊሆን ይገባል።

‎በዚህ አጋጣሚ የወላይታ ወጣቶችን በልዩ ሁኔታ እጠራለሁ። ወጣቶች የወላይታ የነገ ተስፋ ብቻ ሳይሆኑ የዛሬ ለውጥ ፈጣሪዎችም ናቸው። በእውቀት፣ በፈጠራ፣ በቴክኖሎጂና በሥራ ፈጠራ የሚገነቡት ነገ የዞናችንን የልማት አቅጣጫ የሚወስኑ ስለሆ በየትኛውም ተግዳሮት ተስፋ ሳትቆርጡ የነገ መዳረሻችሁን አሻግራችሁ እንዲታዩ አሳስባለሁ ።

‎እምርታ የአንድነት ቀንም ነው። ልዩነቶቻችንን በማክበር፣ የጋራ እሴቶቻችንን በማጠናከርና በመተባበር የበለጠ የተረጋጋች፣ የተሻለችና የበለፀገች ወላይታን መገንባት እንችላለን።

‎ ሰላም የልማት መሠረት፣ አንድነት የእድገት ኃይል፣ ተሳትፎ ደግሞ የስኬት ቁልፍ ነው። በመሆኑም የዘንድሮ ዓመት የወላይታ ዘመን መለወጫ ጊፋታ በዓለም የሰው ልጆች ወካይ ቅርስ ሆኖ የተመዘገበበት ዓመትም ነው።

‎ስለሆነም የዘንድሮውን እምርታ በደስታ ብቻ ሳይሆን፣ “ከዛሬ የተሻለ ነገን በጋራ እንገንባ” በሚል ቁርጠኝነት እንከበረው።
‎ የተጀመሩ የልማት ሥራዎችን እናፋጥን፣ የሕዝብ ተጠቃሚነትን እናሳድግ፣ ሰላማችንን እንጠብቅ፣ ባህላችንን እንጠብቅና ለቀጣዩ ትውልድ የሚበቃ የተሻለ ወላይታን እናስረክብ።

‎በመጨረሻም፣ ይህን የእምርታ ቀን ለምታከብሩ መላው የወላይታ ሕዝቦችና የወላይታ ወዳጆች የላቀ ክብርና ምስጋናዬን እገልጻለሁ።
‎በበዓሉ ወቅት ሰላማችንን፣ አንድነታችንንና መተሳሰባችንን እናጠናክር።
‎እምርታ የአዲስ ተስፋ፣ የአዲስ ጉልበትና የአዲስ ምዕራፍ መጀመሪያ ይሁን!

ጳጉሜን 1 - የእመርታ ቀን፡ ጳጉሜን 1 "የእመርታ ቀን" ሲከበር፣ ኢትዮጵያ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ያሳካቻቸውን ዘርፈ ብዙ የስኬት ጉዞዎችና ለሁለንተናዊ ብልጽግና መሰረት የሆኑ ታላላቅ ምዕ...
06/09/2026

ጳጉሜን 1 - የእመርታ ቀን፡

ጳጉሜን 1 "የእመርታ ቀን" ሲከበር፣ ኢትዮጵያ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ያሳካቻቸውን ዘርፈ ብዙ የስኬት ጉዞዎችና ለሁለንተናዊ ብልጽግና መሰረት የሆኑ ታላላቅ ምዕራፎችን በማሰብ ነው። በብልጽግና ፓርቲ የሚመራዉ የመደመር መንግሥት ተስፋን ወደ ተግባር፣ ህልምን ወደ እውነታ በመቀየር በተለያዩ የልማት መስኮች የያዘዉን የዕድገት መስመር በግልጽ ያሳየበት ወቅት ላይ እንገኛለን። በኢኮኖሚ፣ በማህበራዊና በዲፕሎማሲዉ መስክ የተመዘገቡ እምርታዊ ስኬቶች ኢትዮጵያን ወደሚገባት የብልጽግና ከፍታ የሚያሻግሩ መሰረቶች ናቸዉ፡፡

በግብርና እና በምግብ ሉዓላዊነት የተመዘገበዉ እመርታ ትልቅ አብነት ነዉ፡፡ በበጋ መስኖ የተሸፈነው መሬት ከ400 ሺህ ሄክታር ወደ 3 ሚሊዮን ሄክታር በማደጉ ከ100 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ተሰብስቧል። ኢትዮጵያ የበጋ መስኖ በመጠቀም በስንዴ ምርት ላይ ያካሄደችዉ አብዮት ከስንዴ አስመጪነት ወደ አምራችነትና ላኪነት አሸጋግረዋታል፡፡ በዚህ ዘርፍ የተመዘገበዉ እመርታ ሀገራችን የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋጥ የምታደርገዉ ጥረት ተጨባጭ ዉጤት ማምጣቱ የማይቀር መሆኑን የሚያስረግጥ ሀቅ ነዉ፡፡

መላዉን ኢትዮጵያዉያንን በአንድነት በማነሳሳት ለአንድ ታሪካዊ አላማ በህብረት ቆመዉ ዘመን ተሻጋሪ ታሪክ እንዲጽፉ ምክንያት ሆኗል የአረንጓዴ አሻራ፡፡ እኛ ስንደመር የማናሳካዉ ድል አለመኖሩን የተከልናቸዉ በቢሊዮን የሚቆጠሩ ችግኞች ይመሰክራሉ፡፡ በአንድነት የተከልናቸዉ ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞች የአየር ንብረት ለውጥን የመቋቋም፣ የአፈር ለምነትን የመጠበቅና የምግብ ዋስትናን የማረጋገጥ አህጉራዊ አርአያነት ያለው ስራ ማከናወናችንን ይመሰክራሉ፡፡

በመላዉ ኢትዮጵያውያን የተቀናጀ ህብረት እና የኢኮኖሚ ነፃነት ምልክት የሆነው የህዳሴው ግድብ ተጠናቅቆ የኤሌክትሪክ ሓይል ማምረት መጀመሩ፤ በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች እየተካሄደ ያለዉ የኮሪደር ልማት የከተሞችን ውበት፣ የትራፊክ ፍሰት እና የዜጎችን የመኖሪያ ምቾት ወደ አዲስ ደረጃ ማሸጋገሩና የቱሪዝም ዘርፉን ለማነቃቃት በገበታ ለሀገር፣ በገበታ ለትዉልድና በገበታ ለሸገር የተሰሩ የልማት ስራዎች ያስመዘገቡት እመርታ በተምሳሌትነት ከሚጠቀሱ አበይት ስኬቶች መካል ናቸዉ፡፡

ባለፉት የለዉጥ አመታት በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የሀገር ውስጥ አምራች ኢንዱስትሪዎችን በማጠናከርና ለወጣቶች የቴክኖሎጂና አዲስ የስራ እድሎችን በመፍጠር ረገድ ተጨባጭ ውጤት ተመዝግቧል።

ጳጉሜን 1 የእመርታ ቀን፣ ያለፉትን ስኬቶች ከማሰብ በላይ ወደፊት ለሚጠብቁን ታላላቅ ሀገራዊ ግቦች አዲስ የቁርጠኝነትና የጋራ ጥረት መንፈስ የምናድስበት ታሪካዊ አጋጣሚ ነው።

የእመርታ ቀን አባቶቻችን የኢትዮጵያን ዳር ድንበር በደምና በአጥንታቸው አስከብረው ታላቅ ሀገር አውርሰውናል፤ ዛሬ ደግሞ እውነተኛ ሉዓላዊነትን እያረጋገጥን ያለነው ከልመናና ከጥገኝነት በተላቀ...
06/09/2026

የእመርታ ቀን

አባቶቻችን የኢትዮጵያን ዳር ድንበር በደምና በአጥንታቸው አስከብረው ታላቅ ሀገር አውርሰውናል፤ ዛሬ ደግሞ እውነተኛ ሉዓላዊነትን እያረጋገጥን ያለነው ከልመናና ከጥገኝነት በተላቀቀው አዲሱና ታሪካዊው መንገዳችን ነው! በሚሊዮን በሚቆጠር ዶላር ስንዴ ከማስገባት ተነስተን ዛሬ የአፍሪካ ቀዳሚ ስንዴ አምራች በመሆን የሚሊዮን ዶላሮችን ወጪ ማስቀረት ችለናል። በ«ሌማት ትሩፋት» የምግብ ዋስትናን በተግባር እያረጋገጥን፣ በ«ኢትዮጵያ ታምርት» ንቅናቄም አዳዲስ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋትና የሥራ ዕድል በመፍጠር ሉዓላዊነታችንን እያረጋገጥን እንገኛለን። ከዚህ ቀደም የማይደፈሩና አይነኬ ይባልላቸው የነበሩ ከባድ የማክሮ-ኢኮኖሚ ሪፎርም ውሳኔዎችን በቁርጠኝነት በመተግበር፤ የሀገራችንን ኢኮኖሚ በፅኑ መሠረት ላይ እየገነባን እንገኛለን። እነዚህ ሁሉ ታላላቅ ድሎች ኢትዮጵያ በሚያጋጥሟት ውስጣዊና ውጫዊ ፈተናዎች ሸብረክ ሳትል በፅናት መጓዝ መቻሏን የሚያረጋግጡ ህያው ምስክሮች ናቸው፤ ይህ የእመርታ ጉዟችን ለመጪው ዓመት የሰነቀው ተስፋ እጅግ ግዙፍ ነው!

የወላይታ ብሔር የዘመን መለወጫ "ጊፋታ" በዓልን በታላቅ ድምቀት ለማክበር በዝግጅት ላይ የምትገኘው ውቢቷ ወላይታ ሶዶ ከተማ፤
05/09/2026

የወላይታ ብሔር የዘመን መለወጫ "ጊፋታ" በዓልን በታላቅ ድምቀት ለማክበር በዝግጅት ላይ የምትገኘው ውቢቷ ወላይታ ሶዶ ከተማ፤

የ"ጊፋታ ቱር" የዞኑን እና የሶዶ ከተማ የቱሪስት መዳረሻዎችን በማስተዋወቅ ረገድ የተሳካ እንደነበር ተገለጸወላይታ ሶዶ፣ ነሐሴ 30/2018 ዓ.ም በወላይታ ዞን እና ሶዶ ከተማ ለሦስት ተከታ...
05/09/2026

የ"ጊፋታ ቱር" የዞኑን እና የሶዶ ከተማ የቱሪስት መዳረሻዎችን በማስተዋወቅ ረገድ የተሳካ እንደነበር ተገለጸ

ወላይታ ሶዶ፣ ነሐሴ 30/2018 ዓ.ም በወላይታ ዞን እና ሶዶ ከተማ ለሦስት ተከታታይ ቀናት የተካሄደው የ"ጊፋታ ቱር" ተጠናቅቋል።

የተካሄደውን የጊፋታ ቱር የሦስቱን ቀናት ቆይታ አስመልክቶ መግለጫ የሰጡት የዞኑ ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ ወ/ሮ ፀጋ ፋንታ የወላይታ ብሔር ዘመን መለወጫ ጊፋታ በዓልን ከሌሎች ወንድም ህዝቦች ጋር በድምቀት ለማክበር ዝግጅት መጠናቀቁን ገልጸዋል።

ወ/ሮ ፀጋ አያይዘውም በዓሉን ለማክበር የሚመጡ ለእንግዶቻችን ያሉንን የቱሪስት መስህቦች በማወቅ የቆይታ ጊዜያቸውን እንዲያራዝሙ ለማድረግ ታስቦ የተዘጋጀ ፕሮግራም መሆኑን አብራርተዋል።

ፕሮግራሙ ያሉንን ፀጋዎች ለሌሎች አጉልተን ከማሳየት አንፃር የተሳካ እና ግቡን የመታ ነው ሲሉም ተናግረው የሦስቱን ቀናት ቆይታ የታቀደው የፕሮሞሽንና ማስተዋወቅ ሥራ እንዲሳካ ላበረከቱት አስተዋፅኦ የቱር ቡድኑን አባላት አመስግነዋል።

የወላይታ ዞን መንግሥት ኮሚዩኒኬሽን አገልግሎት ኃላፊ እና የጊፋታ በዓል ማስታወቂያ እና ፕሮሞሽን ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ አቶ በረከት ወርቁ እንደተናገሩት የጊፋታ በዓል በዓለም የሰው ልጅ ወካይ ቅርስነት መመዝገቡን ተከትሎ ዘንድሮ በድምቀት እንደሚከበር ይከበራል።

ለሦስት ቀናት በተካሄደው የ"ጊፋታ ቱር" የዞናችንን የቱሪስት መስህቦችን ከሚዲያ ተቋማት፣ ከማህበራዊ ሚዲያ አንቂዎች እንዲሁም ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች ጋር የተካሄደው የማስተዋወቅ ሥራ ወደ ዞናችን የሚመጡ እንግዶች የቱሪስት መዳረሻዎችን እንዲያውቁ ከማድረግ አንፃር ከፍተኛ ሚና መጫወቱን አብራርተዋል።

የወላይታ ሶዶ ከተማ ቱሪዝም በጊፋታ ቱር ፕሮግራም የከተማዋን የቱሪዝም ፀጋዎች ማስተዋወቅ መቻሉን እና ስኬታማ ሥራ መሠራቱን አብራርተው በቀጣይ ከማህበራዊ ሚዲያ አንቂዎች እና ከሚዲያ ተቋማት ጋር በቅንጅት እንደሚሠሩ ገልጸዋል።

የወላይታ ህዝብ ታሪክ እና ባህል ተመራማሪ አቶ አዳነ አይዛ ጉብኝቱን በተመለከተ በሰጡት አስተያየት የተደረገው የ"ጊፋታ ቱር" ፕሮግራም ያሉንን የቱሪስት መዳረሻዎች በጥልቀት በማወቅ የለሙትን ለሌሎች ከማስተዋወቅ አንፃር እንዲሁም ያልለሙ እና የመሠረተ ልማት ችግር ባለባቸው አካባቢዎች ትኩረት ሰጥቶ ለመሥራት አቅጣጫ የሚጠቁም መሆኑን አብራርተዋል።

ጊፋታን ከማስተዋወቅ አንፃር የወጣቱ አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን እና ምክንያታዊ አስተሳሰብ ያለው ወጣት እየተፈጠረ መሆኑን በአድናቆት ገልጸዋል።

‎የዓለም ቅርስ የሆነው 'ጊፋታ' በዓልን በታላቅ ድምቀት ለማክበር አስፈላጊ የዝግጅት ስራ እየተጠናቀቀ ይገኛል፦ ረ/ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ‎‎ወላይታ ሶዶ፤ ነሐሴ 30/2018 የወላይታ የዘመን...
05/09/2026

‎የዓለም ቅርስ የሆነው 'ጊፋታ' በዓልን በታላቅ ድምቀት ለማክበር አስፈላጊ የዝግጅት ስራ እየተጠናቀቀ ይገኛል፦ ረ/ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ

‎ወላይታ ሶዶ፤ ነሐሴ 30/2018 የወላይታ የዘመን መለወጫ የጊፋታ በዓል ከወትሮ በላቀ ደረጃ ለማክበር የሚያስችል ንቅናቄ መድረክ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ተካሂዷል።

‎የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ረ/ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ የጊፋታ በዓልን ስናከብር የበዓሉ እሴቶችን በተጠበቀ መልኩ ማክበር ይጠብቅብናል ብለዋል።

‎በዓሉን ከመላው ዓለም የተወጣጡ ህብረተሰቦች ጋር በአደባባይ ለማክበር የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተጠናቀቁ መሆናቸውንም አስታውቀዋል።

‎ወላይታ ሶዶ ከተማ ጊፋታ በዓልን ለማክበር የሚመጡ እንግዶቿን ለመቀበል ከመቼውም ጊዜ በላይ እየተወበች መሆኗንም ገልፀዋል።

በዓሉን በወላይታ ብቻ ሳይሆን በሌሎች ሀገራት ጭምር በልዩ ድምቀት ለማክበር በቂ ዝግጅት እየተደረገ እንደሚገኝም ጠቅሰዋል።

‎በየአካባቢው የሚገኙ የቱሪስትና ተፈጥሮ መስህብ ቦታዎችን የማስተዋወቅ ስራ መጠናከር እንዳለበትም አንስተዋል።

‎የዓለም ቅርስ የሆነው የወላይታ ብሔር ዘመን መለወጫ 'ጊፋታ' በዓልን በታላቅ ድምቀት ለማክበር ሁሉም ሰው የበኩሉን አስተዋጽኦ ማበርከት እንዳለበትም ጥሪ አቅርበዋል።

‎የወላይታ ዞን የመንግስት ዋና ተጠሪ ዶ/ር አማረ አቦታ በጊፋታ በዓል አከባበር ዙሪያ ከተለያዩ ህብረተሰብ ክፍሎች ጋር በየደረጃው ውይይት ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል።

‎ጊፋታ በዓል የዓለም ሀብት ሆኗል ያሉት የመንግስት ዋና ተጠሪው፥ በዓሉን በታላቅ ድምቀት ለማክበር ሁሉም ከራሱ የሚጠበቅበትን መውጣት እንዳለበትም አሳስበዋል።

‎በበዓሉ የማንነት መገለጫ የሆኑ ቅርሶችን ለዓለም ህዝብ ማስተዋወቅ ያስፈልጋል ያሉት የመንግስት ዋና ተጠሪው፥ ለዚህም በቂ ዝግጅት መጠናቀቅ እንዳለበትም አመላክተዋል።

‎የወላይታ ሶዶ ከተማ ም/ከንቲባ አቶ መንግስቱ ትግሮ በበኩላቸው የዘንድሮው ጊፋታ በዓልን በልዩ ድምቀት ለማክበር የከተማ አስተዳደሩ ከራሱ የሚጠበቅበትን ስራዎች እየሰራ እንደሚገኝ ገልፀዋል።

‎የበዓሉን ድባብ የሚያሳዩ ክንዋኔዎችን ወጣቶችና ሴቶች በየአካባቢው መከናወንና ማሳየት እንዳለባቸውም አሳስበዋል።

‎ጊፋታ በዓል ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፍ የመጣ የወላይታ ህዝብ የማንነት መገለጫ ነው፦ ረ/ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ ‎‎ወላይታ ሶዶ፤ ነሐሴ 30/2018 የወላይታ የዘመን መለወጫ የጊፋታ በ...
05/09/2026

‎ጊፋታ በዓል ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፍ የመጣ የወላይታ ህዝብ የማንነት መገለጫ ነው፦ ረ/ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ

‎ወላይታ ሶዶ፤ ነሐሴ 30/2018 የወላይታ የዘመን መለወጫ የጊፋታ በዓል ከወትሮ በላቀ ደረጃ ለማክበር የሚያስችል ንቅናቄ መድረክ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት እየተካሄደ ይገኛል።

‎በመድረኩ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ረ/ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ ጊፋታ በዓል ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፍ የመጣ የወላይታ ህዝብ የማንነት መገለጫ መሆኑን ገልፀዋል።

‎የወላይታ ብሔር ዘመን መለወጫ ጊፋታ በዓል ዩኒስኮ ያስቀመጠውን መስፈርቶችን በማሟላት የሰው ልጆች ወካይ ቅርስ ሆኖ መመዘገቡንም አስታውሰዋል።

‎ዘንድሮ ጊፋታ በዓል በልዩ ድምቀት ከመላው ኢትዮጵያዊያን ጋር በጋራ ለማክበር የዞኑ አስተዳደር ከወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑንም ገልፀዋል።

‎በጊፋታ በዓል የተጣሉት የሚታረቁበት የእርቅ፣ የሠላምና የአንድነት በዓል መሆኑንም አስገንዝበዋል።

‎የበዓሉ እሴቶች ሳይበረዙ ለቀጣይ ትውልድ እንዲተላለፍ ሁሉም የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ አጽንኦት ሰጥተዋል።

‎ጊፋታ ሰዎች ብቻ ሳይሆኑ አእዋፋትና የቤት እንስሳትም ጭምር በጋራ የሚያከብሩት በዓል በመሆኑ የእርድ ሥርዓቱን ማክበር እንዳለበትም አንስተዋል።

‎ለበዓሉ ዝግጅት ሁሉም የራሱን ድርሻ መውጣት እንዳለበት ያሳሰቡት ዋና አስተዳዳሪው፥ በዓሉን ለማክበር የሚመጡ እንግዶች ለመቀበል ሁሉም የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያበረክት ጥሪን አቅርበዋል።

‎የወላይታ ዞን ባህልና ስፖርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ስሞዖን ስላሎ በበኩላቸው ጊፋታ ከማንኛውም ባህላዊ እምነትም ሆነ ዘመናዊ ኃይማኖትና የአምልኮ ሥርዓት ጋር ምንም ግኑኝነት የሌለው የዘመን መለወጫ በዓል መሆኑን አስረድተዋል፡፡

Address

S**o
026

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when በወላይታ ዞን የብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት- Wolaita Zone Prosperity Party Branch office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to በወላይታ ዞን የብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት- Wolaita Zone Prosperity Party Branch office:

Shortcuts

Share