South Ethiopia Regional State Police Commission

South Ethiopia Regional State Police Commission ይህ የደቡብ ኢትዮጵያ ፖሊስ ኮሚሽን ትክክለኛ የፌስቡክ ገፅ ነው። ገፁን ላይክ ሼርና ኮሜንት በማድረግ ፖሊሳዊ መረጃዎችን በየዕለቱ ይከታተሉ! https://t.me/Southpolicecomm
(1)

‎አርባ ሁለት የትራፊክ ፖሊስ ሰልጣኝ ተማሪዎች በዛሬው ዕለት ተመረቁ‎‎ግንቦት 28/2018 ዓ/ም (ላስካ ኮሙኒኬሽን )‎‎የላስካ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽ/ቤት እና የከተማ አስተዳደሩ ትራን...
05/06/2026

‎አርባ ሁለት የትራፊክ ፖሊስ ሰልጣኝ ተማሪዎች በዛሬው ዕለት ተመረቁ

‎ግንቦት 28/2018 ዓ/ም (ላስካ ኮሙኒኬሽን )

‎የላስካ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽ/ቤት እና የከተማ አስተዳደሩ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ዩኒት ጋር በጋራ በመሆን 42 የትራፊክ ፖሊስ ሰልጣኝ ተማሪዎችን አስመርቀዋል።

‎ተማሪዎች ላለፉት ሁለት ወራት መሰረታዊ የትራፊክ ሳይንስ ትምህርቶችን በክፍል ውስጥና በተግባር ተምረው ነው በዛሬው ዕለት የተመረቁት።

‎በምርቃት መርሐግብሩ ላይ ተገኝተው ያስመረቁት የላስካ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ኢ/ር አንለይ ወንድይፍራው
‎ትራፊክ አደጋ ለበርካታ ወገኖቻችን ሞትና አካል መጉደል መንስኤ ሆኖ የቀጠለና በሀገር ሀብትና ንብረት ላይ የከፋ ጉዳት እየደረሰ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

‎የትራፊክ አደጋን ለመከላከልና ለመቀነስ ከዚህ ቀደም በከተማ አስተዳደሩ በርካታ ስራዎች እንደተሰሩና ተጨባጭ ለውጦች መታየታቸውን የገለፁት ከንቲባው ዛሬ የተመረቁ ተማሪዎች ወደ ስራው ስሰማሩ ይበልጥ አዎንታዊ ለውጥ ይኖረዋል ብለዋል።

‎ዘርፉ ክቡር የሆነውን የሰው ህይወት ከሞትና ከአካል ጉዳት መታደግ በመሆኑ ተመራቂ ተማሪዎች እንኳን ደስ ያላችሁ በማለት ይህን ላስተባበሩ አካላትም ምስጋና አቅርበዋል።

‎የትራፊክ አደጋን የመከላከሉ ስራ ማህበረሰቡን ጨምሮ ሁሉም ባለድርሻና ተባባሪ አካላትን ባሳተፈ መልኩ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት የገለፁት የባስኬቶ ዞን ትራንስፖርትና መንገድ ልማት መምሪያ ኃላፊ ኢንጂነር ታደለ ታግፌ የትራፊክ አደጋን ከመከላከል እረገድ ተመራቂ ተማሪዎች ትልቅ መፍትሔን ይዘው ይመጣሉ ብለዋል።

‎ለተመራቂዎቹ ስምርት በመስጠት ወደ ተግባር እንዲገቡ በማድረግ በስልጠናው ያገኙትን ትምህርት ተግባራዊ በማድረግ ሕብረተሰቡን ማገልገል እንደሚገባም አሳስበዋል።

‎የላስካ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ አዛዥ ኢንስፔክተር አዳኝ አማረ በትራፊክ አደጋና ቁጥጥር ላይ በልዩ ትኩረት እየሰሩ መቆየታቸውን የገለጹ ሲሆን በቀጣይ የዛሬ ተመራቂዎችን ከመደበኛ ትራፊክ ፖሊስ ጋር ስምርት በመስጠት የትራፊክ አደጋ የማይሰማባት ላስካን ከተማን እንደሚፈጥሩም አክለዋል።

‎የላስካ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ዪኒት አስተባባሪ አቶ ኢዮብ ጀምበር የትምህርት ቤት መንገድ ደህንነት አደረጃጀቶችን ለማጠናከር የተዘጋጀ ሰነድ አቅርበው ውይይት ተካሂዷል።

‎በመጨረሻም በስልጠናው አስተዋጽኦ ላደረጉ ተቋማትንና ግለሰቦች ለተመራቂዎች የምስክር ወረቀት ተሰጥቷቸዋል።

‎ ግንቦት 28/2018 ዓ/ም

የወላይታ ዞን ፖሊስ መምሪያ በበዴሳ ከተማ አስተዳደር  በህገ ወጥ መንገድ ሲጓጓዝ የነበረ ኮንትሮባንድ ተያዘ።ወላይታ ሶዶ ግንቦት 28/2018 ዓ/ም(ደኢፖኮ)የወላይታ ዞን ፖሊስ መምሪያ ከፌ/...
05/06/2026

የወላይታ ዞን ፖሊስ መምሪያ በበዴሳ ከተማ አስተዳደር በህገ ወጥ መንገድ ሲጓጓዝ የነበረ ኮንትሮባንድ ተያዘ።

ወላይታ ሶዶ ግንቦት 28/2018
ዓ/ም(ደኢፖኮ)

የወላይታ ዞን ፖሊስ መምሪያ ከፌ/ል ፖለስ በተሰጠዉ መረጃ መሠረት ከበዴሳ ከተማ ፖሊስ ጋር ባደረገዉ የመንገድ ላይ ፍተሻ ከሀዋሳ ወደ ወላይታ ሲጓዝ የነበረ አይሱዙ የህዝብ ማመላለሻ ሠ/ቁጥር ኮድ 3-04839 ደህ ተሽከርካሪ ሞባይል በቁጥር 400 ፓዉር ባንክ 14 በዴሳ ከተማ ሲደርስ ከ3 ተጠርጣሪዎች ጋር መያዙን የወላይታ ዞን ፖሊስ መምሪያ ዋና አዛዥ ኮማንደር ንጋቱ ጌታቸዉ ተናግረዋል።

ኮንትሮባንድ ዕቃዉ ልያዝ የቻለዉ ከጦቃሚ በተሰጠ መረጃ መሠረት መሆኑን የተናገሩት አዛዥ ጥቆማ ከተሰጠበት ሰዓት ጀምሮ ከበዴሳ ከተማ ፖሊስ ጋር በመሆን ከፍተኛ የመንገድ ላይ ፍተሻ በማድረግ እንደሆነ ተናግረዋል።

ኮንትሮባንድ እና ህገ ወጥ ንግድ ለሀገር ኢኮኖሚ ዕድገት ፀር እንደሆነ የተናገሩት አዛዡ በዞናችን ዉስጥ ህገ ወጦችና ኮንትሮባንድስቶች መተላለፊያ መንገድ የላቸዉም ብሏል።

ጥቆማዉ ከደረሰበት ሰዓት ጀምሮ ጉዳዩን በቅርበት ሲከታተሉ እንደነበረ የተናገሩት አዛዡ ለዚህ ተግባር ስምሪት በመዉሰድ የሥራ ኃላፊነታቸዉን የተወጡ የበደሳ የፖሊስ አመራርና አባላትን ያመሰገኑት ስሆን በቀጣይም በትኩረት መሠራት እንዳለበት አጽንኦት ሰጥተዋል።

በወንጀል ተጠርጥሮ በተያዙ ግለሰቦች ላይ ፖሊስ ከጉሙሩክ ኮሚሽን ሀዋሳ ቅርንጫፍ ጋር በመነጋገር ምርመራዉን አጣርቶ ለህግ የሚያቀርብ መሆኑን ተናግረዋል።

በመጨረሻም ኮንትሮባንድና ህገ ወጥ ንግድ ለሀገር ኢኮኖሚ ዕድገት ፀር መሆኑን በመገንዘብ የተለያዩ የመረጃ ምንጮችን በመጠቀም ለኮንትሮባንድስቶች የማይመች አካባቢ ለመፍጠር በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል።

በጀግንነት መጠበቅ በሰብአዊነት ማገልገል!!

በግፍ ሰው የመግደል ወንጀል የተከሰሰው ግለሰብ በሞት እንዲቀጣ ተወሰነበት።ወላይታ ሶዶ ግንቦት 26/2018 ዓ/ም (ደኢፖኮ)ተከሳሽ ጸጋዬ ታደሰ በሞት እንዲቀጣ የተወሰነበት በጌዴኦ ዞን ገደብ...
03/06/2026

በግፍ ሰው የመግደል ወንጀል የተከሰሰው ግለሰብ በሞት እንዲቀጣ ተወሰነበት።

ወላይታ ሶዶ ግንቦት 26/2018 ዓ/ም (ደኢፖኮ)

ተከሳሽ ጸጋዬ ታደሰ በሞት እንዲቀጣ የተወሰነበት በጌዴኦ ዞን ገደብ ከተማ ውስጥ የቀድሞ ፍቅረኛዬን ከኔ ነጥቀህ አገባህብኝ በሚል ሰበብ ማቾን በአደባሠይ በሽጉጥና በስለት ወጋግቶ መግደሉ በማስረጃ በመረጋገጡ ነው።

የዚህን ወንጀል አፈጻጸም በወቅቱ መዘገባችን ይታወሳል።

በከሳሽ አቃቤ ህግ እና በተከሳሽ በአቶ ጸጋዬ ታደሰ መካከል የነበረዉን የወንጀል ክስ መነሻነት የጌዴኦ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ግንቦት 17/2018 ዓ/ም በተከሳሹ ላይ መነሻ ቅጣት በሞት እንዲቀጣ በማለት የተከሳሹን የቅጣት ማቅለያ እና የዐ.ህግን የቅጣት ማክበጃ ለመስማት ለግንቦት 26/2018 ዓ/ም ቀጠሮ መያዙን መግለጻችን ይታወቃል።

የጌዴኦ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የወንጀል ችሎት ተከሳሽ ካቀረባቸዉ የቅጣት ማቅለያ ዉስጥ ሁለት የቅጣት ማቅለያን መቀበሉን ተመልክተናል

በከሳሽ የጌዴኦ ዞን አቃቤ ህግ በተከሳሹ ላይካቀረባቸዉ ልዩ የቅጣት ማክበጃዎች ዉስጥ ሁለቱን ማክበጃዎች ፍርድ ቤቱ መቀበሉን ከስፍራዉ አረጋግጠናል

የጌዴኦ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤትም ከተከሳሽ የቀረበዉን የቅጣት ማቅለያ እና አቃቤ ህግ ያቀረባቸዉን ልዩ የቅጣት ማክበጃ ተመሳሳይ እንደሆነ እንደሆነ ተረድቷል

ስለዚህም የጌዴኦ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት ግንቦት 26/2018 ዓ/ም በተከሳሹ ላይ ቀደም ብሎ የያዘዉን መነሻ ቅጣት የሞት ዉሳኔን አጽድቋል

ፍርድ ቤቱም ዉሳኔዉን ተከታትሎ እንዲያስፈጽም ለዲላ ከተማ ማረሚያ ተቋም ትዕዛዝ መስጠቱን ከስፍራዉ የጌዴኦ ዞን ፖሊስ መምሪያ ህዝብ ግንኙነት ዘግቧል

በረ/ኢንስፔክተር ሐብታሙ ወንዶ
ካሜራ ዋና ሳጅን አሻግሬ ወ/ሚካኤል

"ዜና ችሎት!"ሞባይል ለመንጠቅ ሲሉ የሰው ህይወት ያጠፋ ተከሳሾች በጽኑ እስራት መቀጣታቸውን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የአሪ ዞን ከፍተኛው ፍርድ ቤት አስታወቀ።ወላይታ ሶዶ ግንቦት 25/2018...
02/06/2026

"ዜና ችሎት!"
ሞባይል ለመንጠቅ ሲሉ የሰው ህይወት ያጠፋ ተከሳሾች በጽኑ እስራት መቀጣታቸውን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የአሪ ዞን ከፍተኛው ፍርድ ቤት አስታወቀ።

ወላይታ ሶዶ ግንቦት 25/2018 ዓ/ም(ደኢፖኮ)

የኣሪ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ግንቦት 25/2018ዓ/ም በዋለው ችሎት ተከሣሾች የኢፌዲሪ ወንጀል ህግ አንቀፅ 32 (1)(ሀ )እና 671( 2) ለይ የተመለከተውን በመተላለፍ ከባድ የውንብድና ወንጀል ፈፅመዋል ባላቸው ተከሣሾች ላይ የፅኑ እስራት ቅጣት አስተላልፏል።

ተከሣሾች የኢፌዲሪ ወንጀል ህግ አንቀፅ 32 (1)(ሀ )እና 671( 2) ለይ የተመለከተውን በመተላለፍ ከባድ የውንብድና ወንጀል ፈፅመዋል ባላቸው ተከሣሾች ላይ የፅኑ እስራት ቅጣት ያስተላለፈ ሲሆን ተከሣሾቹ 1ኛ, አቶ ሐብታሙ አውላ አይኬ 2ኛ ምስጋናው መስፍን መለሰ በቀን 15/02/2018 ዓ.ም ከምሽቱ 3 ስዓት አርክሻ አካባቢ የኃይል ድርጊት በመፈፀም ሟች የአቶ አበበ በየነ ንብረት የሆነውን ቴክኖ ሞባይል ስልክ ለመውሰድ በማሰብ የገደሉት መሆኑን በፍርድ ሒደቱ ተረጋግጧል።

ፖሊስ ከወንጀል ድርጊቱ በኋላ በደረሰው ጥቆማ ተከታትሎ በቁጥጥር ስር ያዋላቸው ሲሆን የምርመራ መዝገቡን በሚገባ አጣርቶ ለዐቃቤ ህግ አስተላልፏል።

በፍርድ ቤት ክርክር ተከሣሾች የወንጀሉን ድርጊት አልፈፀምንም ብለው ክደው ቢከራከሩም ዐ/ ህግ ባቀረባቸው የሰውና የሰነድ ማስረጃ ወንጀሉን ድርጊት ስለመፈፀማቸው ከበቂ በላይ አስረድቷል።

በተከሣሾች በኩል የቀረቡ ሁለት የቅጣት ማቅለያ ምክንያቱችን በመቀበል የአሪ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተከሣሾችን እና መሰሎቻቸውን ያርማል፣ ያስተምራል ያለውን እያንዳንዳቸው ተከሣሾች ላይ የ22 ዓመት ፅኑ እስራት ቅጣት ወስኖባቸዋል።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሰባተኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ በሰላም ይጠናቀቅ ዘንድ የተቋቋመው የፀጥታ ግብረ ኃይል እስካሁን ያለውን አፈጻጸም በመገምገም በድህረ ምርጫ ወቅት ሊከናወኑ በሚገቡ  ተ...
02/06/2026

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሰባተኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ በሰላም ይጠናቀቅ ዘንድ የተቋቋመው የፀጥታ ግብረ ኃይል እስካሁን ያለውን አፈጻጸም በመገምገም በድህረ ምርጫ ወቅት ሊከናወኑ በሚገቡ ተግባራት ላይ አቅጣጫ አስቀምጧል።

ወላይታ ሶዶ ግንቦት 25/2018 ዓ/ም (ደ.ኢ.ፖ.ኮ) እስካሁን ባለው አፈጻጸም በፀጥታው መዋቅር የተሰሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን የፀጥታ ግብረ ኃይሉ ገምግሟል።

7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በሀገር አቀፍ ደረጃ በትላንትናው እለት የድምጽ አሰጣጥ ሂደት መጠናቀቁ ይታወቃል።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልልም በሁሉም አከባቢዎች ሂደቱ በሰላም መጠናቀቁን መግለጻችን ይታወሳል።

ጊዜያዊ የምርጫውጤት በየምርጫ ጣቢያ መለጠፍና የድምጽ መስጫ ሳጥኖችን ወደ ማዕከል የመመለስ ስራ እየተሰራ መሆኑን የፀጥታ ግብረ ኃይሉ በበይነ መረብ በየደረጃው ከተቋቋመው የፀጥታ አካላት ጋር ባደረገው ውይይት አረጋግጧል።

በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች ጊዜያዊ ውጤት የማሳወቅና የምርጫ ቁሳቁስ ወደ ማእከል ተሰብስቦ እስኪጠቃለልና በምርጫ ቦርድ አማካይነት ውጤቱ በይፋ እስክገለጽ ድረስ የፀጥታ ኃይሉ ስምሪት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አቅጣጫ አስቀምጣል።

እስካሁን ባለው ሒደት ፀጥታን ለማስከበር የተሠማራው የፀጥታ ኃይል ተልእኮውን በአግባቡ እየፈጸመ እንደሆነ የገመገመው የፀጥታ ግብረ ኃይል ቀሪ ተግባራትን በዚሁ መንፈስ እስከ ፍፃሜው ተጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስቧል።

የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ አሰጣጥ ሂደት በስኬት መጠናቀቁን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል  የምርጫ ኮማንድ ፖስት  አስታወቀ።በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች ድምጽ የመስጠት ሂደ...
02/06/2026

የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ አሰጣጥ ሂደት በስኬት መጠናቀቁን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የምርጫ ኮማንድ ፖስት አስታወቀ።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች ድምጽ የመስጠት ሂደት ፍጹም ሠላማዊ እና ስኬታማ ሆኖ መጠናቀቁን በክልሉ የተቋቋመው የምርጫ ኮማንድ ፖስት አስታውቋል።

ድምጽ የመስጠት ሥርዓቱ በስኬት እንዲጠናቀቅ መራጩ ሕዝብ፣ የምርጫ አስፈጻሚዎች፣ ዕጩዎች እና ታዛቢዎች ላበረከቱት አስተዋጽኦ እና ኃላፊነታቸውን በተገቢው ለተወጡ መላው የጸጥታ አካላት ኮማንድ ፖስቱ ምስጋናውን አቅርቧል።

ድህረ ምርጫ ያለው ሂደት በተመሳሳይ በስኬት እንዲከናወን ባለ ድርሻ አካላት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ የምርጫ ኮማንድ ፖስቱ ጥሪውን አስተላልፏል።

ወላይታ ሶዶ ግንቦት 25/2018 ዓ/ም(ደ.ኢ.ፖ.ኮ)

''ምርጫው በሠላም እንዲጠናቀቅ አስፈላጊው ዝግጅት ተደርጓል'' - የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ፍስሃ ጋረደው።ወላይታ ሶዶ ግንቦት 22/2018 ዓ.ም (ደኢፖኮ) ምርጫው ሠላ...
30/05/2026

''ምርጫው በሠላም እንዲጠናቀቅ አስፈላጊው ዝግጅት ተደርጓል'' - የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ፍስሃ ጋረደው።

ወላይታ ሶዶ ግንቦት 22/2018 ዓ.ም (ደኢፖኮ) ምርጫው ሠላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ አስፈላጊው ዝግጅት መደረጉን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ፍስሃ ጋረደው ገለጹ።

የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ፍስሃ ጋረደው፥ ፖሊስ ከቅድመ ምርጫ ወቅት ጀምሮ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመቀናጀት ምርጫው ሠላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ እየተሰራ ነው ብለዋል።

ክልሉ ለማደግ የሚተጉ ሕዝቦች ያሉበት ሰላማዊ ክልል መሆኑን አንስተው፥ ሂደቱ ፍጹም ሠላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ከፀጥታ አካላት ጋር በመተባበር እየተንቀሳቀሱ ስለመሆኑ ጠቅሰዋል።

ተፎካካሪ ፓርቲዎች የመንግሥት ሥልጣንን ለመያዝ በሚያደርጉት ሠላማዊ ትግል ከቅስቀሳ ወቅት ጀምሮ የሕዝቡን መብት ባከበረ መልኩ እንዲንቀሳቀሱ ሲደረግ መቆየቱን አንስተዋል።

ለምርጫ ጣቢያዎች የምርጫ ቁሳቁስ የማድረስ ሥራ እየተከናወነ ነው ያሉት ኮሚሽነሩ በእስካሁኑ ሂደት ምንም ዓይነት ችግር አለማጋጠሙን ገልፀዋል።

ፓሊስ ምርጫውን ሠላማዊ ሆኖ እንዳይጠናቀቅ የሚንቀሳቀሱ ጸረ ሠላም ኃይሎችን በመከታተል እርምጃ መውሰድ የሚያስችል ዝግጅት መደረጉን ገልፀው፤ ከአድማ ብተና ሠራዊት ጀምሮ በየደረጃው ያሉ አባላት ዝግጁ መሆናቸውን አመላክተዋል።

ከዚህም ባለፈ የፌደራል መንግሥት የሚያስተዳድራቸው ክልሉን አቋርጠው የሚያልፉ መንገዶችን በመጠበቅ ሠላማዊ ሆነው እንዲዘልቁ እየተደረገ ነው ብለዋል።

ፖሊስ የምርጫ አስፈፃሚዎችን፣ መራጮች እና የምርጫ ቁሳቁስ ደህንነት በመጠበቅ በክልሉ የሚገኙ ከሦስት ሺህ በላይ ምርጫ ጣቢያዎች ሠላማዊ ሆነው እንዲጠናቀቅ ግብረ-ኃይል ተቋቁሞ እየተሰራ ነው ብለዋል።

ግብረ-ኃይሉ ምርጫው ተጠናቆ ውጤት ይፋ እስኪደረግ ሥራውን በተቀናጀ መልኩ እንደሚያከናውን ጠቁመዋል።

ዘገባው የደቡብ ሬድዮና ቴሌቭዥን ነው።

ከመደበኛ ስራ በተጨማሪ የሪፎርሙ ተግባራቶች በጌዴኦ ዞን ፖሊስ  መምሪያ አበረታች ለዉጥ መኖሩን ኮምሺነር ፍሰሃ ጋርደዉ ተናገሩዲላ ግንቦት 20/2018 ዓለም/ምን ጌዴኦ ዞን ፖሊስ መምሪያ የ...
29/05/2026

ከመደበኛ ስራ በተጨማሪ የሪፎርሙ ተግባራቶች በጌዴኦ ዞን ፖሊስ መምሪያ አበረታች ለዉጥ መኖሩን ኮምሺነር ፍሰሃ ጋርደዉ ተናገሩ

ዲላ ግንቦት 20/2018 ዓለም/ምን ጌዴኦ ዞን ፖሊስ መምሪያ የህዝብ ግንኙነት፦

የሪፎርም ተግባራቶች ዘመናዊ በሆነ መንገድ የፖሊስ ተቋምን ለአገልግሎት ምቹ እና ሳቢ ለማድረግ የክልሉ ፖሊስ በርካታ ስራዎችን በመተግበሩ በሁሉም ፖሊስ ተቋም አበረታች ለዉጦች እንዳለ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ፍስሃ ጋርደዉ ገልጸዋል

ለፖሊስ ተቋም መሠረታዊ ለዉጥ እንዲመጣና የፖሊስ አመራርና አባላት የዕዉቀት ባለቤት እንዲሆኑ ከዘመኑ ጋር ለማዘመን የቴክኖሎጂ ዉጤቶችን በመጠቀም የተቋሙን ደረጃ ከፍ ለማድረግ የሪፎርም ትግበራ የማይተካ ሚና እንዳለዉ ኮሚሽነር ፍስሃ ጋርደዉ አክለዉ ተናግረዋል።

የጌዴኦ ዞን ፖሊስ መምሪያ የለዉጥ ስራዎች ዙሪያ ከፖሊስ መምሪያዉ ጀምሮ እስከ ታችኛዉ ፖሊስ መዋቅር ወጥ በሆነ መንገድ ሪፎርሙ መተግበሩ የዞኑ ፖሊስ ለለዉጥ ስራዎች የሰጠዉን ትኩረት በግልጽ የሚያሳይ እንደሆነም አስተያየታቸዉን የሰጡ የፖሊስ አመራሮች ተናግረዋል።

ይርጋጨፌ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት የለዉጥ ስራዎችን በተቋሙ ዉስጥ እየሰራ ሲሆን ይህ አተገባበር ከሐሳብ በዘለለ በተግባር ትኩረት ሰጥቶ የመስራት ዉጤት መሆኑ የማይካድ ሀቅ ነዉ ተብሏል።

በምልከታቸዉም የፖሊስ ኃይሉ ከሌሎች ከጸጥታ አካላት ጋር ሰላምን ለማረጋገጥ በምድብ ቦታቸዉ ያሉትን የጸጥታ መዋቅር የቅንጅት ስራ ለሰላምና ደህንነት ዋስትና እንደሆነ ተጠቁሟል።

በዛሬዉ ዕለትም በጌዴኦ ዞን በይርጋጨፌ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት እየተተገበሩ የሚገኙትን የሪፎርሙ ስራዎች ኮምሽነር ፍስሃ ጋርደዉን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የፖሊስ አመራሮች፣ የጌዴኦ ዞን ፖሊስ አመራሮች የተሰሩ ስራዎችን ተዟዙረዉ ተመላክተዋል።

በረ/ኢንስፔክተር ሐብታሙ ወንዶ
ካሜራ ዋና ሳጅን አሻግሬ ወ/ሚካኤል

ሳምንታዊ የትራፊክ አደጋ መረጃ‎‎በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ባሳለፍነው አንድ ሳምንት  በደረሰ  10 የትራፊክ አደጋ በ10 ሰዎች ላይ ሞት ማስከተሉን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የትራ...
28/05/2026

ሳምንታዊ የትራፊክ አደጋ መረጃ

‎በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ባሳለፍነው አንድ ሳምንት በደረሰ 10 የትራፊክ አደጋ በ10 ሰዎች ላይ ሞት ማስከተሉን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የትራፊክ አደጋ መከላከልና ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት አስታወቀ።

‎ወላይታ ሶዶ ግንቦት 20/2018 ዓ/ም (ደ.ኢ.ፖ.ኮ)
‎በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ባሳለፍነው አንድ ሳምንት 10 የትራፊክ አደጋ መመዝገቡን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን የትራፊክ አደጋ መከላከልና ቁጥጥር ዳይሮክቶሬት ግንዛቤ መፍጠር ዲቪዥን ሃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ፍሬው ከፈለው የላከልን መረጃ ያመላክታል።

‎ባሳለፍነው አንድ ሳምንት በክልሉ ከባድ አደጋ ተብሎ የተመዘገበው በወላይታ ዞን ዲምቱ ከተማ አስተዳደር ፋንጎ ቦሎሶ ቀበሌ ከዲላ ወደ ሶዶ ሲንቀሳቀስ የነበረ ሚኒባስ ተሽከርካሪ ከሶዶ ወደ ሀዋሳ ሲንቀሳቀስ ከነበረ የህዝብ ማመላለሻ ቅጥቅጥ ተሽከርካሪ ጋር ተጋጭቶ በ6 ሰዎች ላይ የሞት አደጋ ስያስከትል በ8 ሰዎች ከባድ በ22 ሰዎች ላይ ቀላል የአካል ጉዳት ማድረሱን የተላከልን መረጃ ያመላክታል።

‎በወላይታ ዞን በተለያዩ 2 ቀናት በደረሰ የትራፊክ አደጋ በ1 ሰው ላይ የሞት አደጋ ሲደርስ በ1 ሰው ላይ ደግሞ ከባድ የአካል ጉዳት ማድረሱ ተገልጿል።

‎በኮንሶ ዞን ካራት ከተማ አስተዳደር በተለያዩ 3 ቀናት በደረሰ የትራፊክ አደጋ በ1 ሰው ላይ የሞት አደጋ ስያስከትል በ5 ሰዎች ላይ ከባድ የአካል ጉዳት አድርሷል ተብሏል።

‎በጋሞ ዞን ካምባ ወረዳ ኦቶሎ ቀበሌ ከካምባ ወደ በቶ ሲንቀሳቀስ የነበረ ሞተር ሳይክል ተገልብጦ በ1 ሰው ላይ የሞት አደጋ ስያስከትል በ1 ሰው ላይ ከባድ የአካል ጉዳት አድርሷል ተብሏል

‎በጌዴኦ ዞን ገደብ ከተማ አሮ ቀበሌ ውስጥ ለውስጥ ሲንቀሳቀስ የነበረ ሞተር ሳይክል እግረኛ ገጭቶ በ1 ሰው ላይ የሞት አደጋ ማድረሱ ተገልጿል።

በ‎ኮሬ ዞን ኬሌ ከተማ ውስጥ ለውስጥ ሲንቀሳቀስ የነበረ ሞተር ሳይክል እግረኛ ገጭቶ በ1 ሰው ላይ ከባድ በ2 ሰው ላይ ቀላል የአካል ጉዳት አድርሷል።

‎በጎፋ ዞን ደንባ ጎፋ ወረዳ ምረጃ ወላ ቀበሌ ከቡልቅ ወደ ሳውላ ሲንቀሳቀስ የነበረ ሞተር ሳይክል ተገልብጦ በ3 ሰዎች ላይ ከባድ የአካል ጉዳት ማድረሱ ተገልጿል።

‎በሪፖርተር ተመስገን መልካሙ!!

ኢትዮጵያ ሁላችንም የምንጠብቃት የሁላችንም ቤት ናት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ፍስሃ ጋርደዉ ተናገሩዲላ ግንቦት 20/2018 ዓለም/ምን ጌዴኦ ዞን ፖሊስ መምሪያ የህ...
28/05/2026

ኢትዮጵያ ሁላችንም የምንጠብቃት የሁላችንም ቤት ናት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ፍስሃ ጋርደዉ ተናገሩ

ዲላ ግንቦት 20/2018 ዓለም/ምን ጌዴኦ ዞን ፖሊስ መምሪያ የህዝብ ግንኙነት፦

ኮሚሽነሩ ይህን ያሉት በጌዴኦ ዞን አሁናዊ ጸጥታ ሁኔታን ለመገምገምና በቀጣይ በሚሰሩ ተግባራቶች ዙሪያ ከፌዴራልና ከክልሉ ጸጥታ አካላት ጋር በጌዴኦ ዞን ገደብ ከተማ ዉይይት ባደረጉበት ወቅት ነዉ

ከዉስጥም ከዉጪም ያሉ ጠላቶች ሁሌም አላማቸዉ ኢትዮጵያን ማጥቃት እንደሆነ የገለጹት ኮሚሽነር ፍስሃ ለዚህም ዓላማ መመከት የሚችል በቂ የጸጥታ አካላት በመኖሩ ህብረተሰብም ከጸጥታዉ አካል ጎን በመሆን የሰላምን ስራ እንዲሰሩ ኮሚሽነሩ ጥሪ አቅርበዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጸጥታ ምክር ቤት የመከላከያ ሰራዊት ተወካይ የሆኑት ጄነራል አስፋው ማመጫ በበኩላቸዉ የሰራዊቱን ዉስጣዊ አንድነቱን በማጎልበት የተጠናከረ የጸጥታ ስራን በመስራት የህዝብን መብቶች ማስከበር ተቀዳሚ ተግባር መሆኑን ተናግረዋል።

የምርጫ ሂደት ምንም አይነት ወከባ እንዳይኖር ዜጎች በራሳቸዉ ፍቃድ ለመረጡት አካል የድምጽ መስጠት ሂደትን በሰላማዊ መንገድ እንዲሰጡ ሁሉም የጸጥታ አካላት የማህበረሰቡ ሰላምና ደህንነት የመጠበቅ ስራን በትኩረት እንደሚሰራ ጄኔራሉ አክለዉ ገልጸዋል።

የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ ዶ/ር የጌዴኦ ህዝብ ሰላም ወዳድ ህዝብ በመሆኑ የራሱንና የአካባቢዉን ሰላም ለማስጠበቅ የሚፈጠሩ ችግሮችን በባህላዊ ስርዓት የሚፈታ ለሰላም ቅድምያ ሰጥቶ የሚሰራ ህዝብ እንደሆነ ጠቁመዋል

የማህበረሰባችንን ሰላምና ደህንነት አስጠብቀን 7ኛዉ ሀገራዊ እና ክልላዊ ምርጫ በሰላማዊ መንገድ እንዲጠናቀቅ ከጸጥታዉ አካል ጎን በመሆን የሰላሙን ስራ በቅንጅት ይሰራል ሲሉ ዝናቡ ወልዴ ዶ/ር መናገራቸዉን ተመላክተናል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የጸጥታዉ ከፍተኛ አመራሮች በጌዴኦ ዞን ገደብ ወረዳ በሀገራዊ ጉዳይ እና 7ኛዉ ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫን አስመልክቶ እስከ በታች በመዉረድ የሰላምና የደህንነት ሁኔታ በመቃኘት በቀጣይ ስራ ዙሪያ ምክክር አድርገዋል ሲል የጌዴኦ ዞን ፖሊስ ህዝብ ግንኙነት ዘግቧል።

በረ/ኢንስፔክተር ሐብታሙ ወንዶ
ካሜራ ዋና አሻግሬ ወ/ሚካኤል

Address

Wolaita
S**o

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when South Ethiopia Regional State Police Commission posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to South Ethiopia Regional State Police Commission:

Share