07/08/2026
በጊዜያዊ ግጭት ምክንያት ትዳር አጋሯን የገደለችው ግለስብ በ20 ዓመት ጽኑ እስራት መቀጣቷን የኮሬ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት አስታወቀ።
ወላይታ ሶዶ ነሐሴ 1/2018 ዓ/ም (ደ.ኢ.ፖ.ኮ)
ተከሳሽ ተስፋነሽ ዘለቀ በእስራት ልትቀጣ የቻለችው በኮሬ ዞን ሳርማላ ወረዳ ቢደርባ ማናና ቀበሌ ውስጥ ታህሳስ 21/2018 ዓ/ም ከምሽቱ 2፡00 ሰዓት ላይ የትዳር አጋሯን በቆጮ መቁረጫ ቢላዋ ቆርጣ በመግደሏ ነው።
ግለሰቧ በእለቱ ቤት ውስጥ በተፈጠረ አለመግባባት ከቤት በመውጣቷ ምክንያት ሟች ባለቤቷ ፍለጋ ጀምሯል ጎረቤት በመሔድም ጠይቆ እዛ እንዳልሔደች አረጋግጦ በምሽት የት ገብታ ይሆን በሚል ባትሪ አብርቶ ወደ ጓሮ ሲገባ ስለት ይዛ አድፍጣ ትጠብቀው የነበረ ሲሆን አንገቱ ላይ በጭካኔ በማሳረፍ ህይወቱ እንዲያልፍ ማድረጓ ተረጋግጧል።
ፖሊስ የወንጀል ድርጊቱ እንደተፈጸመ ተጠርጣሪዋን በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራውን በሰውና በሰነድ ማስረጃ አስደግፎ ለአቃቤ ህግ ልኳል።
አቃ-ዐቤ ህግም ክስ መስርቶ ለኮሬ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት አቅርቧል።
የኮሬ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤትም የተከሳሽ ተስፋነሽ ዘለቀን መዝገብ ከተመለከተ በኋላ ጥፋተኛ ሆና በመገኘቷ ሐምሌ 29/2018 ዓ/ም በዋለው ችሎት ተከሳሽን ያስተምራል ሌላውን ያስጠነቅቃል በሚል በ20 ዓመት ጽኑ እስራት እንድትቀጣ ወስኗል።
ምንጭ የኮሬ ዞን ፖሊስ መምሪያ ህዝብ ግንኙነት ነው።