05/06/2026
አርባ ሁለት የትራፊክ ፖሊስ ሰልጣኝ ተማሪዎች በዛሬው ዕለት ተመረቁ
ግንቦት 28/2018 ዓ/ም (ላስካ ኮሙኒኬሽን )
የላስካ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽ/ቤት እና የከተማ አስተዳደሩ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ዩኒት ጋር በጋራ በመሆን 42 የትራፊክ ፖሊስ ሰልጣኝ ተማሪዎችን አስመርቀዋል።
ተማሪዎች ላለፉት ሁለት ወራት መሰረታዊ የትራፊክ ሳይንስ ትምህርቶችን በክፍል ውስጥና በተግባር ተምረው ነው በዛሬው ዕለት የተመረቁት።
በምርቃት መርሐግብሩ ላይ ተገኝተው ያስመረቁት የላስካ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ኢ/ር አንለይ ወንድይፍራው
ትራፊክ አደጋ ለበርካታ ወገኖቻችን ሞትና አካል መጉደል መንስኤ ሆኖ የቀጠለና በሀገር ሀብትና ንብረት ላይ የከፋ ጉዳት እየደረሰ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
የትራፊክ አደጋን ለመከላከልና ለመቀነስ ከዚህ ቀደም በከተማ አስተዳደሩ በርካታ ስራዎች እንደተሰሩና ተጨባጭ ለውጦች መታየታቸውን የገለፁት ከንቲባው ዛሬ የተመረቁ ተማሪዎች ወደ ስራው ስሰማሩ ይበልጥ አዎንታዊ ለውጥ ይኖረዋል ብለዋል።
ዘርፉ ክቡር የሆነውን የሰው ህይወት ከሞትና ከአካል ጉዳት መታደግ በመሆኑ ተመራቂ ተማሪዎች እንኳን ደስ ያላችሁ በማለት ይህን ላስተባበሩ አካላትም ምስጋና አቅርበዋል።
የትራፊክ አደጋን የመከላከሉ ስራ ማህበረሰቡን ጨምሮ ሁሉም ባለድርሻና ተባባሪ አካላትን ባሳተፈ መልኩ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት የገለፁት የባስኬቶ ዞን ትራንስፖርትና መንገድ ልማት መምሪያ ኃላፊ ኢንጂነር ታደለ ታግፌ የትራፊክ አደጋን ከመከላከል እረገድ ተመራቂ ተማሪዎች ትልቅ መፍትሔን ይዘው ይመጣሉ ብለዋል።
ለተመራቂዎቹ ስምርት በመስጠት ወደ ተግባር እንዲገቡ በማድረግ በስልጠናው ያገኙትን ትምህርት ተግባራዊ በማድረግ ሕብረተሰቡን ማገልገል እንደሚገባም አሳስበዋል።
የላስካ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ አዛዥ ኢንስፔክተር አዳኝ አማረ በትራፊክ አደጋና ቁጥጥር ላይ በልዩ ትኩረት እየሰሩ መቆየታቸውን የገለጹ ሲሆን በቀጣይ የዛሬ ተመራቂዎችን ከመደበኛ ትራፊክ ፖሊስ ጋር ስምርት በመስጠት የትራፊክ አደጋ የማይሰማባት ላስካን ከተማን እንደሚፈጥሩም አክለዋል።
የላስካ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ዪኒት አስተባባሪ አቶ ኢዮብ ጀምበር የትምህርት ቤት መንገድ ደህንነት አደረጃጀቶችን ለማጠናከር የተዘጋጀ ሰነድ አቅርበው ውይይት ተካሂዷል።
በመጨረሻም በስልጠናው አስተዋጽኦ ላደረጉ ተቋማትንና ግለሰቦች ለተመራቂዎች የምስክር ወረቀት ተሰጥቷቸዋል።
ግንቦት 28/2018 ዓ/ም