05/06/2026
የወላይታ ዞን ፖሊስ መምሪያ በበዴሳ ከተማ አስተዳደር በህገ ወጥ መንገድ ሲጓጓዝ የነበረ ኮንትሮባንድ ተያዘ።
ወላይታ ሶዶ ግንቦት 28/2018
ዓ/ም(ወዞፖመም)
የወላይታ ዞን ፖሊስ መምሪያ ከፌ/ል ፖለስ በተሰጠዉ መረጃ መሠረት ከበዴሳ ከተማ ፖሊስ ጋር ባደረገዉ የመንገድ ላይ ፍተሻ ከሀዋሳ ወደ ወላይታ ሲጓዝ የነበረ አይሱዙ የህዝብ ማመላለሻ ሠ/ቁጥር ኮድ 3-04839 ደህ ተሽከርካሪ ሞባይል በቁጥር 400 ፓዉር ባንክ 14 በዴሳ ከተማ ሲደርስ ከ3 ተጠርጣሪዎች ጋር መያዙን የወላይታ ዞን ፖሊስ መምሪያ ዋና አዛዥ ኮማንደር ንጋቱ ጌታቸዉ ተናግረዋል።
ኮንትሮባንድ ዕቃዉ ልያዝ የቻለዉ ከጦቃሚ በተሰጠ መረጃ መሠረት መሆኑን የተናገሩት አዛዥ ጥቆማ ከተሰጠበት ሰዓት ጀምሮ ከበዴሳ ከተማ ፖሊስ ጋር በመሆን ከፍተኛ የመንገድ ላይ ፍተሻ በማድረግ እንደሆነ ተናግረዋል።
ኮንትሮባንድ እና ህገ ወጥ ንግድ ለሀገር ኢኮኖሚ ዕድገት ፀር እንደሆነ የተናገሩት አዛዡ በዞናችን ዉስጥ ህገ ወጦችና ኮንትሮባንድስቶች መተላለፊያ መንገድ የላቸዉም ብሏል።
ጥቆማዉ ከደረሰበት ሰዓት ጀምሮ ጉዳዩን በቅርበት ሲከታተሉ እንደነበረ የተናገሩት አዛዡ ለዚህ ተግባር ስምሪት በመዉሰድ የሥራ ኃላፊነታቸዉን የተወጡ የበደሳ የፖሊስ አመራርና አባላትን ያመሰገኑት ስሆን በቀጣይም በትኩረት መሠራት እንዳለበት አጽንኦት ሰጥተዋል።
በወንጀል ተጠርጥሮ በተያዙ ግለሰቦች ላይ ፖሊስ ከጉሙሩክ ኮሚሽን ሀዋሳ ቅርንጫፍ ጋር በመነጋገር ምርመራዉን አጣርቶ ለህግ የሚያቀርብ መሆኑን ተናግረዋል።
በመጨረሻም ኮንትሮባንድና ህገ ወጥ ንግድ ለሀገር ኢኮኖሚ ዕድገት ፀር መሆኑን በመገንዘብ የተለያዩ የመረጃ ምንጮችን በመጠቀም ለኮንትሮባንድስቶች የማይመች አካባቢ ለመፍጠር በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል።
በጀግንነት መጠበቅ በሰብአዊነት ማገልገል!!