Wolaita Zone Police Department new

Wolaita Zone Police Department new Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Wolaita Zone Police Department new, Government Official, south Ethiopia wolaita zone, Sodo.

በምቤ ከተማ አስ/ር ወጣቶች እና አጋዥ ኃይሎች ከፖሊስ ጋር  የማታ ሮንድ ሥራ  ሠሩወላይታ ሶዶ ነሐሴ  01/2018 ዓ/ም የከረምት በጎ ፊቃድ አገልገሎት አካል የሆነው የማታ ሮንድ ሥራ በበ...
07/08/2026

በምቤ ከተማ አስ/ር ወጣቶች እና አጋዥ ኃይሎች ከፖሊስ ጋር የማታ ሮንድ ሥራ ሠሩ

ወላይታ ሶዶ ነሐሴ 01/2018 ዓ/ም የከረምት በጎ ፊቃድ አገልገሎት አካል የሆነው የማታ ሮንድ ሥራ በበጎ ፊቃደኛ ወጣቶች እና አጋዥ ኃይሎች ተከናውኗል።

የመታ ሮንድ ሥራ በአከባቢው አስተማማኝ ሠላምን ለማረጋገጥ እና ወንጀልን ለመከላከል የሚያግዝ መሆኑ ተገልጿል።

በመረሀግብሩ የተሳተፉት የቦምቤ ከተማ አስ/ር ብልጽግ ፓርቲ ፖለቲካና ሕዝብ ግኙነት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ዘሪሁን ዲካ:-የወጣቶቾ ተሳትፎ በከተማው ሠላምና ፀጥታ ላይ ያለው አስዋፅኦ ከፍተኛ መሆኑ ገልጸው በከረምት በጎ ፊቃድ አገልገሎት የሚካሄዱ መሰል ተግባራት እንደ ሚጠናከሩ ተናግረዋል ።

የቦምቤ ከተማ አስ/ር ፖሊስ አዛዥ የሆኑት ም/ኢ/ር ደረሰ ዳርጮ የማታ ሮንድ ሥራ በማህበርሰብ ውሰጥ የሚፈጠሩ ማናቸውም ፀጥታ ሥጋቶቾ በፍጥነት በመለየት ተገቢውን ሚላሽ ለመስጠት ይረዳል ብለዋል ።

የቦምበ ከተማ አስ/ር ፖሊስ /ጽ/ቤት ማ/አ/ወ/መ/መስተባበሪያ ኃላፊ ዋ/ሣጅን ጳውሎስ ዳካ የማህበረሰብ ፓትሮል ቅኝት ሥራ በአከባቢው ሠላምና የፀጥታ ሁነታን ለማጠናከር እና ወንጀልን ለመከላከል የሚያግዝ መሆኑ ገልፀዋል ።

በማታ ሮንድ የፀጥታ ሥራ ላይ የተሳተፉት ወጣቶች ከፀጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት የአከባቢው ሠላም ለመጠበቅ ቁርጠኛ መሆናቸዉን ተናግረዋል

በመረሀግብሩ የቦምቤ ከተማ አስ/ር ብልጽግና ፓርቲ ፖለቲካና ሕዝብ ግኙነት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ዘሪሁን ዲካ፣ የከተማው ፖሊስ አዛዥ፣የከተማው ፀጥታ ዩኚቲ አመራር አካላት የከተማው ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ጽ/ቤት ኃላፍ ገነነ ጌታሁን ጨምሮ የከተማው በጎ ፌቃድ ወጣቶች አስተባባሪዎች ተሳትፈዋል ።

#በጀግንነት መጠበቅ፤በሰብአዊነት ማገልገል!!

ወጣቱን ያሳተፈ የማታ ሮንድ ጥበቃ ስራ ፖሊስና የማህበረሰቡን እየሰራ መሆኑ ተገለጸወላይታ ሶዶ ነሐሴ 1/2018 ዓ/ም ሰላምና ደህንነት ለመጠበቅ ፖሊስ ከኅብረተሰቡ ጋር እየሰራ መሆኑን የገሱ...
07/08/2026

ወጣቱን ያሳተፈ የማታ ሮንድ ጥበቃ ስራ ፖሊስና የማህበረሰቡን እየሰራ መሆኑ ተገለጸ

ወላይታ ሶዶ ነሐሴ 1/2018 ዓ/ም
ሰላምና ደህንነት ለመጠበቅ ፖሊስ ከኅብረተሰቡ ጋር እየሰራ መሆኑን የገሱባ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ኢ/ር ጳዉሎስ ገልጸዋል።

የከተማውን ሠላምና ደኅንነት ለማረጋገጥ ወጣቱ የክረምት በጎ ፌቃድ አገልግሎት አካል የሆነዉን የአካባቢ ማታ ሮንድ ሥራ እየሰሩ መሆናቸዉ ተገልጸዋል።

በከተማው የማታ ሮንድ ጥበቃ ስራውን በማጠናከር አካባቢውን ከስርቆትና ሌሎችም ስጋቶች ነፃ በማድረግ የሰላም ዘብ ሆኖ እንዲሰራ እየተደረገ መሆኑም ተናግረዋል።

በመጨረሻም የገሱባ ከተማ ፖሊስ ከወጣቶች ክንፍ እና ፍትሕና ጸጥታ ክላስተር ጋር በመሆን የማታ ሮንድ ተግባራትን በመከናወን ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል ።

#በጀግንነት መጠበቅ፤በሰብአዊነት ማገልገል!!

የወላይታ ዞን ፖሊስ መምሪያ ዋና አዛዥ ኮ/ር ንጋቱ ጌታቸው በአረካ ከተማ ወቅታዊ የፀጥታ ሁኔታ ጨምሮ አጠቃላይ የተቋሙን ተግባር በመገምገም ቀጣይ አቅጣጫ አስቀመጡ።ወላይታ ሶዶ፤ሐምሌ 30/2...
06/08/2026

የወላይታ ዞን ፖሊስ መምሪያ ዋና አዛዥ ኮ/ር ንጋቱ ጌታቸው በአረካ ከተማ ወቅታዊ የፀጥታ ሁኔታ ጨምሮ አጠቃላይ የተቋሙን ተግባር በመገምገም ቀጣይ አቅጣጫ አስቀመጡ።

ወላይታ ሶዶ፤ሐምሌ 30/2018 ዓ.ም የወላይታ ዞን ፖሊስ መምሪያ ዋና አዛዥ ኮ/ር ንጋቱ ጌታቸው በአረካ ከተማ ወቅታዊ የፀጥታ ሁኔታ ጨምሮ አጠቃላይ የተቋሙን ተግባር በመገምገም ቀጣይ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

ሰላም ለሁሉ መሠረት በመሆኑ የወንጀል መከላከል ሥራ የሁሉ ፖሊስ አመራርና አባል ሥራ ሊሆን እንደሚገባ ነው ኮማንደሩ አበክረው ያሳሰቡት።

ህብረተሰቡን የሰላሙ ባለቤት በማድረግ የወንጀል መከላከል ሥራ የፖሊስ አባላት ከህብረተሰቡ ጋር ተቀናጅቶ መሥራት እንደሚገባም አመላክተዋል።

የሚፈጠሩ ጉዳዮችን በማጤን ወንጀልን ቀድሞ መከላከል የፖሊስ ቀዳሚ ተግባር መሆኑን ያነሱት ዋና አዛዡ የከተማውን አስተማማኝ ሰላም ለማረጋገጥ የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ እንዲቀጥል አመላክተዋል።

የፖሊስ ተቋም ከሌሎች ፍትህ ተቋማት ጋር በመቀናጀት የተግባራት ውጤታማነት ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት መሥራት እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

የፖሊስ አባላትና አመራሮች ህዝብን በቅንነትና በታማኝነት በመገልገል የተጣለባቸውን ኃላፊነት በተገቢው እንዲወጡም አሳስበዋል።

በተቋሙ አጠቃላይ ተግባራትን ከመፈጸምና ከማስፈጸም አኳያ የታየው ለውጥ ተጠናክሮ እንዲቀጥል አመላክተዋል።

የተቋሙ አጠቃላይ ተግባራትን በጥልቀት የገመገሙት ኮ/ር ንጋቱ በጥንካሬ የታዩ ጉዳዮች እንዲጎለብቱ ፥አንዳንድ ማስተካከያ የሚፈልጉ ጉዳዮች ለቀጣይ እንዲታረሙ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

በተቀመጠው ግብረ-መልስ መነሻ የነበሩ ጥንካሬዎችን በማስቀጠል ፥ጉድለቶችን በፍጥነት በማረም ቀጣይ የተቋሙን አጠቃላይ ተግባራትን በተጨባጭ ውጤት ለመፈጸም ዝግጁ መሆናቸውን የተናገሩት የአረካ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ኢ/ር እሸቱ ፎላ ናቸው።

በተላይ የከተማችን አስተማማኝ ሰላም ለማረጋገጥ የሚደረገው ርብርብ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑንም አዛዡ ተናግረዋል።

አያይዘውም ወንጀልን ቀድሞ በመከላከል ህዝባችን በሰላም ወጥተው በሰላም የሚገባበት አከባቢ የመፍጠር ጉዳይ ከምንም በላይ ቅድሚያ ተሰጥቶ እየተሠራ መቆየቱንም ገልጸዋል።

በመድረኩ የወላይታ ዞን ፖሊስ መምሪያ ሰው ሀብት አስተዳደር ዲቪዥን ኃላፊ ኮ/ር ጋረደው መድህን፣የወላይታ ዞን ፖሊስ መመሪያ መረጃ ኢንተለጀንስ ዲቪዥን ኃላፊ ኢ/ር አበበ ማሞ እና የተቋሙ አመራሮችና አባላት ተገኝተዋል።
#በጀግንነት መጠበቅ በሰብዊዓነት ማገልገል

ዳሞት ሶሬ ውሎ ሰላም ስሆን ሳምንታዊ ቡና ጠጡ ፕሮግራም በአካባቢው ሰላምና ጸጥታ ዙሪያ በጥልቀት በመመካከር ቀጣይ በትኩረት በሚሰሩ አጀንዳዎች ላይ በጋራ ለመግባባት አንድነትና ቅንጅት የሚፈ...
06/08/2026

ዳሞት ሶሬ ውሎ ሰላም ስሆን ሳምንታዊ ቡና ጠጡ ፕሮግራም በአካባቢው ሰላምና ጸጥታ ዙሪያ በጥልቀት በመመካከር ቀጣይ በትኩረት በሚሰሩ አጀንዳዎች ላይ በጋራ ለመግባባት አንድነትና ቅንጅት የሚፈጥር ነው፦አቶ ገለቱ ገዙሜ

ወላይታ ሶዶ፤ ሐምሌ 30/2018 ዓ.ም

በወላይታ ዞን የዳሞት ሶሬ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት በአንጩቾ ማዘጋጃ ከተማ ከወረዳውና ከጉኑኖ ሐሙስ ከተማ ፖሊስ አባላት እና ና ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር የቡና ጠጡ መርሃ ግብር አካሂዷል።

በመርሃ ግብሩ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የወረዳው ብልጽግና ፓርቲ ፖለቲካና ሕዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ገለቱ ገዙሜ ሳምንታዊ ቡና ጠጡ ፕሮግራም በአካባቢው ሰላምና ጸጥታ ዙሪያ በጥልቀት በመመካከር ቀጣይ በትኩረት በሚሰሩ አጀንዳዎች ላይ በጋራ ለመግባባት አንድነትና ቅንጅት የሚፈጥር ነው ሲሉ ገልጸዋል።

መርሃ ግብሩ የፖሊስ አባላት እና የህብረተሰቡ እርስ በእርስ መቀራረብን የሚያጠናክር መሆኑን ተናግረው፥ ዘላቂ ሰላም በአካባቢው እንዲሰፍን የላቀ ሚና አለውም ብለዋል።

ቡና ጠጡ ፕሮግራም ሁሌም ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የጠቀሱት አቶ ገለቱ፥ በሁሉም አካባቢዎች ተደራሽ እንዲሆን እና አሳታፊ ለሆን እንደሚያስፈልግ አንስተዋል።

ህብረተሰቡ በየደረጃው ከተሰማሩ የጸጥታና ፖሊስ አባላት ጋር በመሆን ወንጀሎችን ለመከላከልና ሰላምን ለማስቀጠል ሊሰሩ እንደሚያስፈልግም አሳስበዋል።

የወረዳው ፖሊስ አዛዥ የሆኑት ረ/ኢ/ር ትዕዛዙ እስራኤል የፖሊስ አባላት ቡና ጠጡ ፕሮግራም የአባላቱን የተግባርና የአመለካከት አንድነት ለማጠናከር ያለመ ነው ሲሉ ገልጸዋል።

ፕሮግራሙ ወንጀልን ለመከላከልና ሰላምን ለማጽናት አስተዋጽኦ የላቀ መሆኑን አስረድተው፥ በጋራ ተቀናጅቶና ተናቦ በመሥራት ህዝቡ ተጠቃሚነት ተጠቃሚ እንዲሆን ያደርጋል ሲሉም ተናግረዋል።

አያይዘውም ህብረተሰቡ ለአካባቢው ዘላቂ ሰላም ከጸጥታ አካላት ጋር ጠንካራ ቅንጅት በማድረግ መንቀሳቀስ እንደሚገባ አሳስበዋል።

የአንጩቾ ማዘጋጃ ከተማ ሥራ አስኪያጅ አቶ አዲሱ ኩታፎ በበኩላቸው የቡና ጠጡ ፕሮግራም አብሮነትን የሚያጠናክር መሆኑን ገልጸው፥ በአካባቢው ጸጥታ ዙሪያ ውይይት ለማድረግ አውድ የሚፈጥር እንደሆነ ተናግረዋል።
በጀግንነት መጠበቅ በሰባዓነት ማገልገል
መልካም ምሸት ፡

የጉኑኖ ሐሙስ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ም/ኮማንደር ተስፋዬ ምስጋናው ጨምሮ የከተማው ፖሊስ አባላት በክረምት በጎ ፈቃድ ስራ የደም ልገሳ አደረጉ።ወላይታ ሶዶ፤ ሐምሌ 30/2018 ዓ.ም የክረምት በ...
06/08/2026

የጉኑኖ ሐሙስ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ም/ኮማንደር ተስፋዬ ምስጋናው ጨምሮ የከተማው ፖሊስ አባላት በክረምት በጎ ፈቃድ ስራ የደም ልገሳ አደረጉ።

ወላይታ ሶዶ፤ ሐምሌ 30/2018 ዓ.ም

የክረምት በጎ ፈቃድ መርሃ ግብር ውስጥ ከተያዙ 18 የበጎ ፈቃድ ዘርፎች አንዱ የደም ልገሳ በመሆኑ ዛሬ የጉኑኖ ሐሙስ ከተማ ፖሊስ ጽ/ቤት የከተማው ፖሊስ አባላት ደም ለግሰዋል።

በደም ልገሳ ላይ የከተማው ፖሊስ አዛዥ ም/ኮማንደር ተስፋዬ ምስጋናው እንደገለፁት ፖሊስ ከሚሰጠው ሁሉአቀፍ የማህበረሰብ አገልግሎቶች ባሻገር እንዲህ ያሉ የነፍስ አድነሰ ስራዎች የሚበረታቱ መሆኑን ገልፀዋል።

ም/ኮማንደር ተስፋዬ ምስጋናው አያይዘውም የደም ባንክ አስተባባሪዎችና ለተደረገው ሰብአዊ ድጋፍ ለአመራሩንና አባላትን ምስጋና አቅርበዋል።

በመርሃ ግብሩ ላይ የከተማው ፖሊስ አዛዥ ም/ኮማንደር ተስፋዬ ምስጋናው፣ የከተማው ማህበረሰብ አቀፍ ወንጀል መከላከል ዘርፍ ኃላፊ ረ/ኢ/ር አለሙ አሳሌ፣ የከተማው ፖሊስ አመራሮች እና አባላት በንቃት ተሳትፈዋል።

በጀግንነት መጠበቅ፣ በሰብዓዊነት ማገልገል !!

የአካባቢውን ሰላም ለማስጠበቅ ከህብረተሰቡ ጋር  በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ የሁምቦ ክላስተር ፖሊስ አባላት ገለፁ ። ፋራቾ፦ ሐምሌ 30/2018 ዓ.ም የአበላ አባያ ወረዳ፣ የሁምቦ ወረዳ  እና ...
06/08/2026

የአካባቢውን ሰላም ለማስጠበቅ ከህብረተሰቡ ጋር በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ የሁምቦ ክላስተር ፖሊስ አባላት ገለፁ ።

ፋራቾ፦ ሐምሌ 30/2018 ዓ.ም የአበላ አባያ ወረዳ፣ የሁምቦ ወረዳ እና የጠበላ ከተማ አስተዳደር የሦስቱ መዋቅር ፖሊስ ጽ/ቤት በወቅታዊ የአካባቢ ጸጥታ በሚመለከትና ቀጣይ በትኩረት በሚከናወኑ ሥራዎች ዙሪያ ከፖሊስ አመራርና አባላት ጋር የውይይት መድረክ አካሂዷል ።

በመድረኩ የወላይታ ዞን ፖሊስ መምሪያ ታክቲክ ምርመራ ድቭዥን ኃላፊ ኮ/ር አሽናፍ አድሱ እንደተናገሩት የሦስቱ መዋቅር ፖሊስ አመራር አካላት እና አባላት በጋራ በመሆን ወንጀል መከላከል ስራን በተጠናከረ መልኩ ይዞ መቀጠል እንዳለበት ተናግረዋል ።

‎በየትኛውም ቦታ ወንጀልን ለመከላከል ገደብ አለመኖሩን እና በየትኛውም ቦታ ህግን የማስከበር ስልጣን የተሰጠ መሆኑ መታወቂያችን በግልጽ የሚያስረዳ ስሆን ተግባራችንን ከዚህ ውይይት በኋላ ከወትሮው የበለጠ የወንጀል መከላከልም ሆነ የአንድነት ስራን በማጠናከር መቀጠል ያስፈልጋል ብለዋል ።

የወላይታ ዞን ፖሊስ መምሪያ የልማት ዕቅድና ኢኮኖሚ ልማት ድቭዥን ኃላፊ የሆኑት ኢ/ር ፍሬሕይወት ሰማ እንደገለፁት የህዝቡ መሰረታዊ ፍላጎት የሆነው ሰላም በየደረጃው እንዲረጋገጥ የፖሊስ ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልጸው፥ ለዚህም የአባላቱ መቀናጀት ወሳኝ እንደሆነ ገልጸዋል።

በአጎራባች አካባቢዎች ሊከሰቱ የሚችሉ ወንጀሎችንና ህገወጥነቶችን ለመቆጣጠር ፖሊስ ከህብረተሰቡ እና ከሌሎች ባለድርሻዎች ጋር በየወቅቱ እየተናበበ መስራት እንደሚገባም አሳስበዋል ።

የወላይታ ዞን ፖሊስ መምሪያ ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ማስተባባሪያ ኃላፊ ኢ/ር አበበች ሞጋ
በበኩላቸው ህገ-ወጥነትንና ስርዓት አልበኝነትን ለመከላከልና ህጋዊነት ለማጎልበት እና ህግና ስርዓትን ለማስከበር እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ይበልጥ መጠናከር እንደሚገባ ተናግረዋል ።

ወንጀል መከላከል ላይ ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶ መሰራት እንዳለበት እና ድንገተኛ ፍተሻ በሁሉም መገቢያና መውጫ መንገዶች ላይ ማደረግ እንዲሁም በሥጋት ቀጠናዎች ላይ ቋሚና ተንቀሳቃሽ ጥበቃ ፖሊስ በመመደብ ጠንካራ የመረጃ ሥርዓትን በመዘርጋት የውስጥ አንድነት ከወትሮ በተለየ መልኩ ማጠናከር እና የአከባቢውን ሠላምና ደህንነት ማረጋገጥ እንዳለባቸው አሳስበዋል።

በመድረኩ የወላይታ ዞን ፖሊስ መምሪያ ታክቲክ ምርመራ ድቭዥን ኃላፊ ኮ/ር አሽናፍ አድሱ፣ የወላይታ ዞን ፖሊስ መምሪያ የልማት ዕቅድና ኢኮኖሚ ልማት ድቭዥን ኃላፊ የሆኑት ኢ/ር ፍሬሕይወት ሰማ፣ የወላይታ ዞን ፖሊስ መምሪያ ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ማስተባባሪያ ኃላፊ ኢ/ር አበበች ሞጋ፣የሦስቱ መዋቅር ፖሊስ ጽ/ቤት ዋና አዛዦች እና የሦስቱ ፖሊስ ጽ/ቤት አባላቶች ተገኝቷል።

በወላይታ ዞን ፖሊስ ማምሪያ የአረካ  ከተማ ፖሊስ አመራር እና አባላት የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ስፖርት  አደረገ ወላይታ ሶዶ ሐምሌ 29/2018 ዓ/ም  የአረካ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ፅ/ቤ...
05/08/2026

በወላይታ ዞን ፖሊስ ማምሪያ የአረካ ከተማ ፖሊስ አመራር እና አባላት የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ስፖርት አደረገ

ወላይታ ሶዶ ሐምሌ 29/2018 ዓ/ም የአረካ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ፅ/ቤት
👉​ፖሊስ ካለበት አገራዊና አካባቢያዊ የሰላምና የደህንነት ጥበቃ ተልዕኮ አንጻር፣ የአባላቱ የአካልና የአዕምሮ ብቃት መጎልበት ወሳኝ በመሆኑ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ አድርገዋል።እንፔክተር እሸቱ ፎላ የአረካ ከተማ ፖሊስ አዛዥ

ከመደበኛ የሥራ ኃላፊነታቸው ጎን ለጎን ጤንነታቸውን እንዲጠብቁና ለተልዕኮ ዝግጁ እንዲሆኑ ትልቅ አቅም ስለደሚፈጥር ተጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል ተብሏል።

#በጀግንነት መጠበቅ በሰብዊዓነት ማገልገል

በወጣቱ ትውልድ አዕምሯዊ እና አካላዊ ጉዳት የሚያስከትለውን አደንዛዥ ዕጽ ማስወገዱን የአረካ ከተማ ፖሊስ ጽ/ቤት አስታወቀ።ወላይታ ሶዶ፤ሐምሌ 27/2018 ዓ.ም በወጣቱ ትውልድ አዕምሯዊ እና...
03/08/2026

በወጣቱ ትውልድ አዕምሯዊ እና አካላዊ ጉዳት የሚያስከትለውን አደንዛዥ ዕጽ ማስወገዱን የአረካ ከተማ ፖሊስ ጽ/ቤት አስታወቀ።

ወላይታ ሶዶ፤ሐምሌ 27/2018 ዓ.ም በወጣቱ ትውልድ አዕምሯዊ እና አካላዊ ጉዳት የሚያስከትለውን አደንዛዥ ዕጽ ማስወገዱን የአረካ ከተማ ፖሊስ ጽ/ቤት አስታውቋል።

የከተማው ፖሊስ ጽ/ቤት ዋና አዛዥ ኢ/ር እሽቱ ፎላ እንዳስታውቁት በወጣቱ ትውልድ ላይ ትልቅ ጉዳት የሚያስከትለውን ማንኛውም አደንዛዥ ዕጽ ለማስወገድ በትኩረት እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል።

ወጣቱን በእጅጉ እየቀጠፈ ያለፈውን ማንኛውም አደንዛዥ ዕጽ በማስወገድ ትውልድን ለመታደግ ከምንም ጊዜ በላይ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝም ጠቁመዋል።

ከተማችን ከአደንዛዥ ዕጽ ነጻ በማድረግ ከሚያስከትለው አዕምሯዊና አካላዊ ጉዳት ለማዳን የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑንም አክለዋል።

በከተማ አስተዳደሩ በተደረገው ድንገተኛ ፍተሻ በርካታ ቁጥር ያላቸው የሺሻ ዕቃዎች ከነዕጹ ተይዞ መወገዳቸውን ተናግረዋል።

ድንገተኛ ፍተሻው ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ያነሱት አዛዡ በተጠቃዋሚዎች ሆነ ሺሻውን በቤታቸው አስቀምጦ የሚሰሩ አካላት ላይ ህጋዊ እርምጃ የሚወሰድ መሆኑን ጠቁመዋል።

ለፀጥታ ሥራ የህብረተሰብ ተሳትፎ ወሳኝ በመሆኑ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ከፀጥታ አካላት ጎን እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል።

ዳሞት ሶሬ ወረዳ ዘላቂ ሰላምና ጸጥታ ለማረጋገጥ የፖሊስ አመራር እና አባላት በተሰማራበት ቁርጠኛ ሆኖ መሥራት አለበት። ረ/ኢ/ር ትዕዛዙ እስራኤልወላይታ ሶዶ፤ ሐምሌ 27/2018በወላይታ ዞን...
03/08/2026

ዳሞት ሶሬ ወረዳ ዘላቂ ሰላምና ጸጥታ ለማረጋገጥ የፖሊስ አመራር እና አባላት በተሰማራበት ቁርጠኛ ሆኖ መሥራት አለበት። ረ/ኢ/ር ትዕዛዙ እስራኤል

ወላይታ ሶዶ፤ ሐምሌ 27/2018በወላይታ ዞን የዳሞት ሶሬ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት በወቅታዊ የአካባቢ ጸጥታ በሚመለከትና ቀጣይ በትኩረት በሚከናወኑ ሥራዎች ዙሪያ ከፖሊስ አመራርና አባላት ጋር የውይይት መድረክ አካሂዷል።

በመድረኩ የማጠቃለያ ሃሳብ እና ቀጣይ አቅጣጫ ያስቀመጡት የወረዳው ፖሊስ አዛዥ ረ/ኢ/ር ትዕዛዙ እስራኤል ለህብረተሰቡ ዘላቂ ሰላምና ጸጥታ የፖሊስ አባልና አመራር በተሰማሩበት ቁርጠኛ ሆነው መሥራት እንደሚገባ አሳስበዋል።

የህዝቡ መሰረታዊ ፍላጎት የሆነው ሰላም በየደረጃው እንዲረጋገጥ የፖሊስ ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልጸው፥ ለዚህም የአባላቱ መቀናጀት ወሳኝ እንደሆነ ገልጸዋል።

በወረዳው ይሁን በአጎራባች አካባቢዎች ሊከሰቱ የሚችሉ ወንጀሎችንና ህገወጥነቶችን ለመቆጣጠር ፖሊስ ከህብረተሰቡ እና ከሌሎች ባለድርሻዎች ጋር በየወቅቱ እየተናበበ መስራት እንደሚገባም ተናግረዋል።

ፖሊስ ወንጀሎችን ለመከላከል ፈጣን ምላሽ እየሰጠ መሄድ እንዳለበት ጠቁመው፥ የተሰጠን ተልዕኮ በኃላፍነትና በባለቤትነት እንዲሁም በአገልጋይነት መንፈሰ መወጣት እንዳለብን አንስተዋል።

ህገወጥ ተግባራትን ለመከላከል እና እርምጃ ለመውሰድ በቅንጅት መንቀሳቀስ ያስፈልጋል ያሉት አዛዡ አባላቱ ተግባራትን በግንባር ቀደምነት ሊመሠሩ ያስፈልጋል ብለዋል።

በወረዳው በሁሉም አካባቢዎች የምሽት ሮንድ ጥበቃ በተለየ ትኩረት መከናወን እንደሚገባ ጠቅሰው ይህም ወንጀልን ለመከላከል ሚናው የጎላ ነው ሲሉ ተናግረዋል።

በሐጨረሻም ሰላም እና ጸጥታ በዘላቂነት እንዲረጋገጥ በሁሉም አካባቢዎች ሕዝቡን ማሳተፍ እና ባለቤት ማድረግ እንደሚገባም ረ/ኢ/ር ትዕዛዙ እስራኤል አሳስበዋል።

!

የወላይታ ዞን ዳ/ሶሬ ወረዳ ፖሊስ በቀን አመራርና አባላት ሰኞ የሣምንቱ መጀመሪያ ቀን ሥራ ከመጀመራቸዉ በፊት የሰልፍ ትርዕትና  የአለባበስ ሥነ ሥርዓት ቁጥጥር አካሄደ።ሰኞ የሣምንቱ ሥራ መ...
03/08/2026

የወላይታ ዞን ዳ/ሶሬ ወረዳ ፖሊስ በቀን አመራርና አባላት ሰኞ የሣምንቱ መጀመሪያ ቀን ሥራ ከመጀመራቸዉ በፊት የሰልፍ ትርዕትና የአለባበስ ሥነ ሥርዓት ቁጥጥር አካሄደ።

ሰኞ የሣምንቱ ሥራ መጀመሪያ ቀን የሰልፍ ትርዕት ላይ የወረዳው ፖሊስ ማኔጅሜንት አባላትን ጨምሮ አጠቃላይ የወረዳው ፖሊስ አባላት ተገኝተዋል።

በሥነ ሥርዓቱ ላይ በደንብ ልብስ አለባበስ ሞዴል የወረዳው አመራርና አባላት የተመሰገኑ ሲሆን ጉድለት የታየባቸዉ በቀጣይ እንዲታረሙ አስተያዬት ተሰጥቷል።

በጀግንነት መጠበቅ፤በሰብአዊነት ማገልገል!!

Address

South Ethiopia Wolaita Zone
Sodo

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Wolaita Zone Police Department new posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share