08/09/2026
ጳጉሜ 3 "የፅናት ቀን" በሚል መሪ ሐሳብ በወላይታ ሶዶ ማዕከል በልዩ ልዩ መርሃ ግብሮች እየተከበረ ይገኛል
ጳጉሜ 3/2018 ዓ.ም
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ በተገኙበት ጳጉሜ 3 "የፅናት ቀን" በሚል መሪ ቃል በወላይታ ሶዶ ማዕከል በልዩ ልዩ መርሃ ግብሮች እየተከበረ ይገኛል።
የ2018 የጳጉሜ ቀናት በተለያዩ ስያሜዎች እና በልዩ ልዩ ዝግጅቶች በመላው ሀገሪቱ የኢትዮጵያን የትግል፣ የፅናትና የተስፋ ታሪክ በማስታወስ የተሻለ ነገን ለመገንባት የጋራ ኃላፊነት ለማጠናከር ታስቦ ነው እየተከበረ የሚገኘው።
"የጽናት ቀን" በሀገራችን ብሎም በክልላችን ውስጥ በየቀኑ የሚታዩትን የማይናወጡ የቁርጠኝነትና የመስዋዕትነት ታሪኮች የምናስብበት ልዩ ዕለት መሆኑ ተመላክቷል።
የመርሃ ግብብሩ አካል የሆነው የእግር ጉዞ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ እና የክልሉ መንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ገብረመስቀል ጫላ እንዲሁም የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽነር ፍሰሃ ጋረደው ፣ የክልል የወላይታ ዞን እና የሶዶ ከተማን አመራሮችና የፀጥታ አካላት በተገኙበት እየተካሄደ ይገኛል።