07/08/2026
በምቤ ከተማ አስ/ር ወጣቶች እና አጋዥ ኃይሎች ከፖሊስ ጋር የማታ ሮንድ ሥራ ሠሩ
ወላይታ ሶዶ ነሐሴ 01/2018 ዓ/ም የከረምት በጎ ፊቃድ አገልገሎት አካል የሆነው የማታ ሮንድ ሥራ በበጎ ፊቃደኛ ወጣቶች እና አጋዥ ኃይሎች ተከናውኗል።
የመታ ሮንድ ሥራ በአከባቢው አስተማማኝ ሠላምን ለማረጋገጥ እና ወንጀልን ለመከላከል የሚያግዝ መሆኑ ተገልጿል።
በመረሀግብሩ የተሳተፉት የቦምቤ ከተማ አስ/ር ብልጽግ ፓርቲ ፖለቲካና ሕዝብ ግኙነት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ዘሪሁን ዲካ:-የወጣቶቾ ተሳትፎ በከተማው ሠላምና ፀጥታ ላይ ያለው አስዋፅኦ ከፍተኛ መሆኑ ገልጸው በከረምት በጎ ፊቃድ አገልገሎት የሚካሄዱ መሰል ተግባራት እንደ ሚጠናከሩ ተናግረዋል ።
የቦምቤ ከተማ አስ/ር ፖሊስ አዛዥ የሆኑት ም/ኢ/ር ደረሰ ዳርጮ የማታ ሮንድ ሥራ በማህበርሰብ ውሰጥ የሚፈጠሩ ማናቸውም ፀጥታ ሥጋቶቾ በፍጥነት በመለየት ተገቢውን ሚላሽ ለመስጠት ይረዳል ብለዋል ።
የቦምበ ከተማ አስ/ር ፖሊስ /ጽ/ቤት ማ/አ/ወ/መ/መስተባበሪያ ኃላፊ ዋ/ሣጅን ጳውሎስ ዳካ የማህበረሰብ ፓትሮል ቅኝት ሥራ በአከባቢው ሠላምና የፀጥታ ሁነታን ለማጠናከር እና ወንጀልን ለመከላከል የሚያግዝ መሆኑ ገልፀዋል ።
በማታ ሮንድ የፀጥታ ሥራ ላይ የተሳተፉት ወጣቶች ከፀጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት የአከባቢው ሠላም ለመጠበቅ ቁርጠኛ መሆናቸዉን ተናግረዋል
በመረሀግብሩ የቦምቤ ከተማ አስ/ር ብልጽግና ፓርቲ ፖለቲካና ሕዝብ ግኙነት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ዘሪሁን ዲካ፣ የከተማው ፖሊስ አዛዥ፣የከተማው ፀጥታ ዩኚቲ አመራር አካላት የከተማው ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ጽ/ቤት ኃላፍ ገነነ ጌታሁን ጨምሮ የከተማው በጎ ፌቃድ ወጣቶች አስተባባሪዎች ተሳትፈዋል ።
#በጀግንነት መጠበቅ፤በሰብአዊነት ማገልገል!!