02/06/2026
የገሱባ ከተማ ከንቲባ ክቡር አቶ ዴማ ኃይሌ 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በሠላም መጠናቀቁን አስመልክተው መላውን የከተማው ህዝብን አመሰገኑ
ግንቦት 25/2018 ዓ.ም. የገሱባ ከተማ ከንቲባ ክቡር አቶ ዴማ ኃይሌ 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በሠላም መጠናቀቁን አስመልክተው መላውን የከተማው ህዝብን አመሰግኗል።
"ለሁሉም የጋራ የሆነችሁ ሃገራችን ኢትዮጵያ መርጣለች አሸንፋለችም!"
ክቡር ከንቲባው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ዴሞክራሲያዊና ተአማኒነት ያለው ምርጫ እንደሆነና እንዴ ከተማችንና እንዴ አከባቢያችን ፍፁም ሠላማዊ በሆነ መንገድ መጠናቀቁን ገልጿል።
ለነገው ትውልድ ምቹ ሀገር ለመፈጠር ሁሉም የከተማችን ህዝብ ሠላማዊ በሆነው መንገድ ምርጫውን በመምረጥ የዛሬውን ሳይሆን የነገው ሰንቃቸው በመታጠቅ፣የጸና ሀገር በቀል ጽናትን ማሳየት ችሏል ብሎዋል።
የከተማችን ህዝቦች በአጠቃላይ አረጋዎያን፣ ሴቶች ህጻናትን ተሸክሞ በመዉጣት፣ ወጣቶች፣ አካል ጉዳተኞች፣ ነፍሰ ጡር እናቶች እና አቅመ ደካሞችን ጨምሮ ከጠዋቱ 12፡00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ምሽቱ 6፡00 ሰዓት ድረስ በመውጣት ለዚህ ታሪካዊ ምርጫ የራሳቸውን የዜግነት ግዴታቸውን ሰላማዊ በሆነ መንገድ መጠናቀቁን ከንቲባው አመስግነዋል።
ከንቲባው እንደገለፁት በከተማችን አጠቃላይ 13 የምርጫ ጣቢያዎች በሁሉም ምርጫው ሙሉ በሙሉ ሰላማዊ፣ ነጻና ያለምንም የጸጥታ ችግር እንዲጠናቀቅ ታላቅ ሚና ለተጫወቱት ለተከበረው የከተማችን ህዝብን ታላቅ ምስጋና አቅርቧል።
በተጨማሪ ለተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ላሳዩት ሰላማዊና ህጋዊ የፉክክር መንፈስ፣ ብረዱን ተቋቁመው እየሠሩ ያሉ የምርጫ አስፈጻሚዎችና የሚዲያ ባለሙያዎች እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካለት ላሳያችሁት ቁርጠኝነትና የስራ ተነሳሽነት ፣ በየደረጃው ለሚገኙ የጸጥታ አካላት ሌሊትና ከቀን በመትጋት አስተማማኝ ሰላም በመፍጠራቸው፣ የአስተዳደር መዋቅሮች፣ የህዝብ ተወካዮች፣ ታዛቢዎችን፣ የሀገር ሸማገልዎች፣ የሀይማኖት መሪዎች ለምርጫው ሰላም ስትጸልዩ የቆያችሁ ምዕመናን ጨምሮ ፣ ያለውን ላቅ ያለ ክብርና ልባዊ ምስጋና አቅርቧል።
ከንቲባው በመጨረሻ እንደገለፁት በየምርጫ ጣቢያ ጊዜያዊ የምርጫ ውጤት የተለጠፈ ሰሌሆና የኢትዮጵያ ብሐራዊ ምርጫ ቦርድ ውጤት ይፋ እሰከሚደረገ ደረሰ በትዕግስት እንድተጠባበቁ አሳስበዋል።
ክቡር አቶ ዴማ ኃይሌ
የየገሱባ ከተማ ከንቲባ
ግንቦት 25፣ 2018 ዓ.ም