Gesuba town administration office

Gesuba town administration office Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Gesuba town administration office, Government Organization, Sodo.

~~~~~~ ~~~~~~~ ~~~~~
A view of the overall activities of Gesuba city administration!
~~~~~~ ~~~~~~~ ~~~~~
Gessuba is located in the middle of the border areas around Ofa Woreda, Selamber, Bayra Koish

እንኳን ደስ ያላችሁ እንኳን ደስ ያለን !!የገሱባ ከተማ አስተዳደር መሬት አስተዳደር በደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግሥት መሬት አስተዳደር ቢሮ የመሬት ይዞታ መረጃና ምዝገባ ዘርፍ በከተማችን ...
31/08/2026

እንኳን ደስ ያላችሁ እንኳን ደስ ያለን !!
የገሱባ ከተማ አስተዳደር መሬት አስተዳደር በደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግሥት መሬት አስተዳደር ቢሮ የመሬት ይዞታ መረጃና ምዝገባ ዘርፍ በከተማችን ያለውን የቁራሽ መሬት ማረጋገጥና መመዝገብ በስኬት በመጠናቀቁ የዕውቀትና ሠርተፍኬት ተበርክቶልናል ።

ገሱባ ነሐሴ 25/2018 ዓ.ም የገሱባ ከተማ አስተዳደር መሬት አስተዳደር በደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግሥት መሬት አስተዳደር ቢሮ የመሬት ይዞታ መረጃና ምዝገባ ዘርፍ በከተማችን ያለውን የቁራሽ መሬት ማረጋገጥና መመዝገብ በስኬት በመጠናቀቁ የዕውቀትና ሠርተፍኬት ተበርክቶልናል ።

በዘንድሮው በጀት ዓመት በከተማችን በተለያዩ ዘርፎች በተደጋጋሚ እየተመዘገበ የሚገኘው እመርታ የተቋማት የአፈጻጸም ውጤት ማሳያ ነው ።

በመሆኑም በመሬት አስተዳደር የተከናወኑ በርካታ ሥራዎች አመርቂ ውጤት በማስመዝገብ ለሽልማት ዳርጎውናል ።

የገሱባ ከተማ አስተዳደር በ2018 በጀት ዓመት በመደበኛ እና በማዘጋጃ ገቢ አፈጻጸም በወላይታ ዞን አንደኛ በመሆን የዋንጫ ተሸላሚ ሆኗል። እንኳን ደስ አላችሁ/አለን።
20/08/2026

የገሱባ ከተማ አስተዳደር በ2018 በጀት ዓመት በመደበኛ እና በማዘጋጃ ገቢ አፈጻጸም በወላይታ ዞን አንደኛ በመሆን የዋንጫ ተሸላሚ ሆኗል። እንኳን ደስ አላችሁ/አለን።

የገሱባ ከተማ ምክር ቤት የ2019 በጀት 673,372,720 (ስድስት መቶ ሳባ ሶስት ሚሊዮን ሶስት መቶ ሳባ ሁለት ሺህ ሰባት መቶ ሃያ ብር በማጽደቅ ተጠናቀቀ። ‎‎ገሱባ ከተማ፤ ነሐሴ 13/...
19/08/2026

የገሱባ ከተማ ምክር ቤት የ2019 በጀት 673,372,720 (ስድስት መቶ ሳባ ሶስት ሚሊዮን ሶስት መቶ ሳባ ሁለት ሺህ ሰባት መቶ ሃያ ብር በማጽደቅ ተጠናቀቀ።

‎ገሱባ ከተማ፤ ነሐሴ 13/2018ዓ/ም በወላይታ ዞን የገሱባ ከተማ ምክር ቤት የ2019 በጀት 673,372,720 (ስድስት መቶ ሳባ ሶስት ሚሊዮን ሶስት መቶ ሳባ ሁለት ሺህ ሰባት መቶ ሃያ ብር) በማጽደቅ ተጠናቋል ።

‎የ2019 ዓ.ም በጀት ድልደላ በከተማው ፋይናንስና ፕላን ልማት ዩኒቲ አስተባባሪ አቶ ተረፈ ኃይሌ በኩል ለም/ቤት ግልጽ በሆነ መንገድ እንደሚከተለው የቀረበ ስሆን
‎የ2019 ዓ.ም በጀት በተመለከተ
‎ ✍️ከመንግስት ግምጃ ቤት= 183,738,060
‎✍️ከከተማው ውስጥ ገቢ = 349,086,219
‎✍️ከማዘጋጃ ቤት ገቢ =121,560,102
‎✍️ከትምህርት ቤቶች ገቢ =4,067,381
‎✍️የጤና ተቋማት /መ/ደ/ሆስፒታል ውስጥ ገቢ= 14,920,958

‎ጠጠቅላላ ድምር =673,372,720 (ስድስት መቶ ሳባ ሶስት ሚሊዮን ሶስት መቶ ሳባ ሁለት ሺህ ሰባት መቶ ሃያ ) ብር ቀርቦ በም/ቤቱ አባላት በሙሉ ድምጽ አፅድቋል።

በመጨረሻም ላለፉት አምስት ዓመታትን በኦፋ ምርጫ ክልል የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት በምርጫ ክልሉ የህዝብ ውክልና በመውሰድ በታማኝነትና በቅንነት ያገለገሉት ክብርት ወ/ሮ መሰለች አቱሞ የስንብትና የእውቅና ሰርተፍኬት በመስጠት መድረኩ ተጠናቅቋል ።

‎ #ገሱባ ከተማ አስ/ር 🙏🙏🙏🙏‎አጠቃላይ የከተማው ህብረተሰብ በሙሉ እንኳን ደሰ አላችሁ  ደስ አለን  አግልግሎት መሰጠት ጀምሯል ።‎‎በህብረተሰቡ ዘንድ የልማት ጥያቄ ሆኖ የቆየው ዘመናዊ ...
17/08/2026

‎ #ገሱባ ከተማ አስ/ር 🙏🙏🙏🙏
‎አጠቃላይ የከተማው ህብረተሰብ በሙሉ እንኳን ደሰ አላችሁ ደስ አለን አግልግሎት መሰጠት ጀምሯል ።

‎በህብረተሰቡ ዘንድ የልማት ጥያቄ ሆኖ የቆየው ዘመናዊ የገሱባ ከተማ አስ/ር የመንገድ ዳር መብራት በታቀደው ጊዜ ገደብ ሥራው ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት በዛሬው ዕለት በይፋ መጀመሩ ገሱባ ከተማ ከንቲባ ክቡር አቶ ዴማ ኃይሌ ገለፁ

‎ገሱባ ፤ ነሐሴ 11 /2018 ዓ.ም በወላይታ ዞን የገሱባ ከተማ አስተዳደር የመንገድ ዳር መብራት በዛሬው ዕለት አግልግሎት መሰጠት በይፋ ጀምረዋል።

‎ከገሱባ ከተማ አስተዳደር የከተማ መንገድ ዳር መብራት በዛሬው መጀመሩን መላው የገሱባ ከተማ ነዋሪዎች ትልቅ ደስታ መፈጣራቸውን ገልጸዋል ።

‎የመንገድ ዳር መብራት የከተማውን ውብት ጎላ አድርገው የሚያሳይ እና እንድሁም ለከተማው ሌላ ገጽታውን የሚያበረክት በመሆኑ በመላው በከተማ ህዝብ ልዩ ደስታውን በውስጡ የጫረ መሆኑን ከህብረተሰቡ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል ።

‎ ይህ የመንገድ ዳር መብራት ከተቋራጭ ድርጅት ጋር ውል በተገባው መሰረት የከተማው አስተዳደር ልዩ ድጋፍ እና ክትትል በማድረግ የህብረተሰቡ ተጠቃሚነት እንድረጋገጥ የከተማው ፊት አመራሮች እና ባለድርሻዎች ሚና ከፍተኛ ነው ።

‎በከተማው ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርግ ከዘርፈ ብዙ ፕሮጀክቶች መሐል አንዱ የሆነው ዘመናዊ የመንገድ ዳር መብራት ስሆን በቀሪ ልማት ያልደረሱ አከባቢዎች ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ይታመናል።

‎ !!

በገሱባ ከተማ አስተዳደር ህብረተሰብና በመንግስት ትብብር የተሰራ መንገድ ዳር መብራት@
17/08/2026

በገሱባ ከተማ አስተዳደር ህብረተሰብና በመንግስት ትብብር የተሰራ መንገድ ዳር መብራት
@

የጊፋታ ምሥጢር፦ ልብን በይቅርታ የሚያድሰው የወላይታ የጥበብ ማማወላይታ ሶዶ፦ነሀሴ 7/2018ዓ.ም(ወሬቴድ)ምድር ከክረምት አፈና ወጥታ በአደይ አበባ ወርቃማ ልብስ ስትሽሞነሞን፣ በወላይታ ም...
13/08/2026

የጊፋታ ምሥጢር፦ ልብን በይቅርታ የሚያድሰው የወላይታ የጥበብ ማማ

ወላይታ ሶዶ፦ነሀሴ 7/2018ዓ.ም(ወሬቴድ)

ምድር ከክረምት አፈና ወጥታ በአደይ አበባ ወርቃማ ልብስ ስትሽሞነሞን፣ በወላይታ ምድር ሌላ ትልቅ ተአምር ይጀምራል።

ይህ ተአምር ተራ የበዓል ዝግጅት አይደለም፤ የሰው ልጅ የውስጥ ማንነትን የማጠብ፣ የነፍስን ቆሻሻ የማስወገድ እና ፍቅርን በዙፋኑ ላይ የመመለስ ታላቅ የዕርቅና የሰላም መንፈሳዊ ጉዞ ነው—ጊፋታ!

በዚህ እጅግ ማራኪ ባህል ውስጥ፣ አዲሱን ዓመት ለመቀበል መጀመሪያ የልብን ደጅ ማንኳኳት ግድ ይላል።

በወላይታ ህግና ባህል፣ በአሮጌው ዘመን የተከፋ፣ የተቀያየመ ወይም ቂም የያዘ ሰው አዲሱን የጊፋታ ጨረቃ የማየት ሞራል የለውም።

ቂም ይዞ ወደ አዲስ ዘመን መሻገር እንደ ትልቅ ኃጢአትና ውርደት ይቆጠራል። ስለዚህም በዓሉ ከመድረሱ ቀናት ቀደም ብሎ፣ በመንደሩ ውስጥ የፍቅርና የሰላም አዋጅ ይታወጃል።

የአገር ሽማግሌዎች የከሰሉ ልቦችን ለማገዶ፣ የሻከሩ ግንኙነቶችን ለመፈወስ በእጃቸው የዕርቅን በትር ይዘው ይነሳሉ።

በደል ያደረገው በትሕትና ይንበረከካል፤ የተበደለው ደግሞ ይቅርታን እንደ ማር ያጣጥማል።

ያለምንም ቅድመ ሁኔታ፣ ያለ ምንም ቂም በቀል፣ ፍቅር በሽንገላ ሳይሆን በዕውነተኛ የልብ ስብራት ይነግሳል።

ወንድም ወንድሙን በትከሻው ያቅፋል፤ ጎረቤት ከጎረቤቱ ጋር በፍቅር ይሳሳማል።

ይህንን ትዕይንት ለታዘበ ሰው “ለመሆኑ የሰው ልጅ የሰላም ፍልስፍና መነሻውና መድረሻው ይህ አልነበረም ወይ?

ይህስ ጥበብ ለአለም ሁሉ ተርፎ የሰው ልጅን ግጭት በሙሉ እንዴት ባላከመው ነበር?” ብሎ ማሰቡና መቆጨቱ አይቀሬ ነው።

👉የዓለም ቅርስ መሆኑ የዘገየው ድንቅ ጥበብ

ጊፋታ የቆሰሉ ልቦችን እየጠገነ፣ የተሰበሩ ማህበራዊ ድልድዮችን እየገነባ የሚመጣ የፍቅር ጎርፍ ነው።

የሰው ልጅ በቴክኖሎጂ በረቀቀባት፣ ነገር ግን ሰላምን ባጣችባት በዚህች ዓለም ላይ፣ የወላይታ አባቶችና እናቶች ለዘመናት ጠብቀው ያቆዩት ይህ የእርቅ ፍልስፍና ልብን ሰቅዞ የሚይዝ የሞራል ልዕልና ማሳያ ነው።

ይህ ዓይነቱ የሰላም ጥበብ ዛሬ ላይ ሳይሆን ከዘመናት በፊት መላው ዓለም ሊማርበትና ሊቀስመው የሚገባው፣ የዓለም የሰላም መዝገብ ቀድሞ ሊያሰፍረው የሚገባ ታላቅ የሰው ልጅ ሀብት ነበር!

ጊፋታ ሲመጣ የዱር አበቦች ብቻ አይደሉም የሚፈኩት፤ የሰዎች ልቦችም ጭምር እንጂ። “ዮዮ ጊፋታ!” እየተባባሉ በፍቅርና በይቅርታ አዲሱን ዘመን የሚቀበሉ አባቶች፣ መጪው ትውልድ በቂም ጨለማ ውስጥ እንዳይኖር የብርሃን ችቦ ያበሩለታል።

ጊፋታ ማለት ይቅርታ ነው፤ ጊፋታ ማለት ፍቅር ነው፤ ጊፋታ ማለት የሰው ልጅ የታደሰ ነፍስ ውብ ዜማ ነው!

10/08/2026

በጊፋታ በዓል የሚታዩ አለባበሶች፣ ሃያያ ሌኬ ዜማዎች እና ባህላዊ ጭፈራዎች አንድነትን ለማጠናከር ትልቅ አቅም አላቸው፡፡



‎በወላይታ ዞን በገሱባ ከተማ አስተዳደር ሰብዓዊ ድጋፍ በራስ አቅም ለመሸፈን በልዩ ንቅናቄ እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ ።‎‎ሐምሌ 29/2018  "ከተረጂነት ወደ ምርታማነት" በሚል እሳቤ በካሳባ...
05/08/2026

‎በወላይታ ዞን በገሱባ ከተማ አስተዳደር ሰብዓዊ ድጋፍ በራስ አቅም ለመሸፈን በልዩ ንቅናቄ እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ ።

‎ሐምሌ 29/2018 "ከተረጂነት ወደ ምርታማነት" በሚል እሳቤ በካሳባና በጤፈ በዘር የመሸፈን ሥራዎች በተጠናከረ አግባብ ተጀምሯል ።

‎የገሱባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ደማ ኃይሌ በከተማችን ሰብዓዊ ድጋፍ በራስ አቅም ለመሸፈንና የምግብ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ ከ6 በላይ ሄክታር ማሳን በዘር ለመሸፈን እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል ።

‎ከተረጂነት ወደ ምርታማነት በሚል ዕሳቤ የምግብ ሉዓላዊነት በራስ አቅም ለመሸፈን የማሳ ዝግጅትና በዘር የመሸፈን ስራ ተጠናክሮ እየተሰራ እንደሚገኝም ተጠቅሷል ።

የገሱባ ከተማ አስተዳደር የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ምክር ቤት በከተማው የሰብዓዊ ድጋፍ ሉዓላዊነት ለማብሰር የተከናወኑ ተግባራትን በመገምገም አቅጣጫ አስቀመጠ‎‎ገሱባ ከተማ፤ሐምሌ 27/201...
03/08/2026

የገሱባ ከተማ አስተዳደር የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ምክር ቤት በከተማው የሰብዓዊ ድጋፍ ሉዓላዊነት ለማብሰር የተከናወኑ ተግባራትን በመገምገም አቅጣጫ አስቀመጠ

‎ገሱባ ከተማ፤ሐምሌ 27/2018 የገሱባ ከተማ አስተዳደር የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ምክር ቤት የሰብዓዊ ድጋፍ ሉዐላዊነት ለማብሰር የተከናወኑ ተግባራት አፈጻጸምን በመገምገም ቀጣይ አቅጣጫዎችን አስቀምጧል።

‎በከተማው የሰብዓዊ ድጋፍ ሉዓላዊነትን ለማብሰር የተከናወኑ ተግባራት አፈጻጸም ሪፖርት ለምክር ቤቱ በዝርዝር የቀረበ ስሆን ሰፊ ውይይት ተደርጎበታል።

‎የገሱባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባና የከተማው አደጋ ስጋት ስራ አመራር ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ዴማ ኃይሌ ህብረተሰቡ ከተረጂነት አስተሳሰብ እንዲወጣ ምርታማ እንዲሆን ማድረግ ያስፈልጋል

‎ከተረጂነት በመላቀቅ በራስ አቅም ሰብዓዊ ድጋፍን ለመሸፈን በሚደረገው እንቅስቃሴ ሁሉም ህብረተሰብ የበኩሉን ድጋፍ እንዲያደረግ ጥሪን አቅርበዋል።

‎የገሱባ ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊና የምክር ቤቱ ም/ሰብሳብ አቶ ያኪኒ ማርቆስ ‎በከተማው የሚሰበሰበው እህል እና የመጠባበቂያ ፌንድ የተለዩ ተረጂዎችንና ድጋፍ የሚሹ ወገኖችን በአሠራር መሠረት ድጋፍ የሚደረግ እንደሆነም ገልፀዋል።

‎ለዚህ ዓላማ ህዝቡን የማስተባበር ስራ መሰራት ይገባል ያሉት ኃላፊው፥ ህብረተሰቡ ራሱን በራሱ የመደጋገፍና የመተጋገዝ ባህልን አጠናክሮ እንዲያስቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።

‎ጊፋታ የአለም ህዝቦች በጋራ የሚደምቁበትና የሚያከብሩበት በዓል ነው‎‎የወላይታ ብሔር ዘመን መለወጫ ጊፋታ በዓል የአለም ህዝቦች በጋራ የሚደምቁበትና የሚያከብሩበት በዓል ነው።‎‎"ጊፋታ" የ...
28/07/2026

‎ጊፋታ የአለም ህዝቦች በጋራ የሚደምቁበትና የሚያከብሩበት በዓል ነው

‎የወላይታ ብሔር ዘመን መለወጫ ጊፋታ በዓል የአለም ህዝቦች በጋራ የሚደምቁበትና የሚያከብሩበት በዓል ነው።

‎"ጊፋታ" የወላይታ ህዝብ ከአሮጌው ዓመት ወደ አዲሱ ዓመት መሻገርን የሚገልጽ፣ ዘመን ተሻጋሪ የምስጋና በዓል ነው።

‎መነሻውን ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወላይታ ብሔር ያደረገው የዘመን መለወጫ ጊፋታ በዓል መዳረሻውን የአለም ህዝቦች የጋራ እሴቶች መናገሻ ፓሪስ ካደረገ ሰንበትበት ብሏል።

‎በውስጡ አያሌ ማራኪ እና ብርቅዬ የብሔሩን ማንነት የሚያንጸባርቁ እሴቶችን ጭኖ በመንቀሳቀስ መዳረሻውን የአለም አደባባይ የሆነችውን የፈረንሳይ ዋና ከተማ ፓሪስ ያደረገው ጊፋታ ከማይዳሰሱ የአለማችን ብርቅዬ ቅርሶች ጎራ ተሰልፏል።

‎ባለቤትነቱ የወላይታ ህዝብ የሆነው ይህ የዘመን መለወጫ ጊፋታ በዓል በአለማችን ከሚገኙ ከማይዳሰሱ ባህላዊ ክብረ በዓላት መካከል አንዱ መሆኑን አረጋግጧል።

‎በዓሉ እጅግ ጠቃሚ ልምዶችን ልምምዶችን ወጎችን እና ጠቃሚ ቱርፋቶችን በውስጡ በማካተት ዘመናትን የዘለቀ ታሪካዊ በዓል በመሆኑ ልዩ ጥበቃ እና ክብካቤ እየተደረገለት ከአመታት ጉዞ በኋላ የአለም ህዝቦች የማይዳሰስ የጋራ ሀብት ወደመሆን ደርሷል።

‎በዓሉ በብሔሩ ህዝብ ባህል፣ ታሪክ፣ ቋንቋ እና ሌሎች ማንነቶችን ይበልጥ በማጉላት ረገድ የላቀ ሚና ሲጫወት ኖሯል።

‎ይህ በአለም አደባባይ በደማቅ ቀለም የተጻፈው የዘመን መለወጫ ጊፋታ በዓል በዩኔስኮ የተመዘገበበት ዓመት ከመሆኑ ጋር ተያይዞ የዘንድሮ የ2019 ዓም ካለፉት ጊዜያት በበለጠ መልኩ ከሌሎች የአለማችን ወንድምና እህትማማች ህዝቦች ጋር በሀያያ ለኬ በጋዜያ ጨዋታ እና ሌሎች የብሔሩ ድንቅ ባህላዊ ጨዋታዎች ደምቆ ሊከበር ዝግጅት እየተደረገለት ይገኛል።

‎👋👋Yoo yo Gifaataa!! 👋👋

‎🙏🙏Hashshu gattes 🙏🙏

Address

S**o

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gesuba town administration office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share