Gozamin woreda communication affairs

Gozamin woreda communication affairs ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃ ለሁሉም እናደርሳለን

‎‎በምስራቅ ጎጃም ዞን በጎዛምን  ምርጫ ክልል ለ7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ መራጮች በተለያዩ የምርጫ ጣቢያዎች በነቂስ ወጥተው ድምጻቸውን እየሰጡ ነው።።ለበለጠ መረጃ የጎዛምን ወረዳ  ኮሙዩ...
01/06/2026


‎በምስራቅ ጎጃም ዞን በጎዛምን ምርጫ ክልል ለ7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ መራጮች በተለያዩ የምርጫ ጣቢያዎች በነቂስ ወጥተው ድምጻቸውን እየሰጡ ነው።።

ለበለጠ መረጃ የጎዛምን ወረዳ ኮሙዩኒኬሽንን ይወዳጁ
‎ቲክቶክ : tiktok.com/
‎ቴሌግራም : https://t.me/+0lEq6W4-HkxjMzBk
‎ዩቲዩብ :https://youtube.com/?si=q5oxnXn3EmC4ABrq

🗳️ 🇪🇹በደብረ ማርቆስ ከተማ የምርጫ ክልል የምርጫ ቁሳቁስ ተሠራጭቶ ተጠናቅቋል። በደብረ ማርቆስ ከተማ አሥተዳደር ምርጫ ክልል  በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች አስፈላጊ የምርጫ ቁሳቁሶች በአግባቡ...
31/05/2026

🗳️ 🇪🇹በደብረ ማርቆስ ከተማ የምርጫ ክልል የምርጫ ቁሳቁስ ተሠራጭቶ ተጠናቅቋል።

በደብረ ማርቆስ ከተማ አሥተዳደር ምርጫ ክልል በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች አስፈላጊ የምርጫ ቁሳቁሶች በአግባቡ መሰራጨታቸውን የደብረ ማርቆስ ከተማ ምርጫ ክልል አስተባባሪ አንሙት መንግሥት ተናግረዋል፡፡

በከተማ አሥተዳደሩ በአራቱም ክፍለ ከተሞች በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች የምርጫ ቁሳቁስ ስርጭት መከናወኑን ነው የገለጹት፡፡

ምርጫው በተሳካ ሁኔታ እንዲከናወን የሚያስችሉ አስፈላጊ የቅድመ ዝግጅት ተግባራት መጠናቀቃቸውን የገለጹት አስተባባሪው የምርጫ አስፈጻሚዎች፣ ታዛቢዎች እና ቅሬታ ሰሚዎች በአግባቡ ኀላፊነታቸውን ለመወጣት ዝግጁ መኾናቸውንም አብራርተዋል፡፡

ግንቦት 24/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 12፡00 ጀምሮ ድምጽ የመስጠት ሂደቱ እንደሚጀመርም ተናግረዋል።

አሚኮ

በአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር  ከ11 ሚሊየን 860 ሽህ  በላይ ችግኞችን ለመትከል የቅድመ ዝግጅት ስራዋች እየተሰሩ መሆናቸው  ተገለጸ።  ግንቦት 21/2018 ዓ.ም (ጎዛምን ኮሙኒኬሽን )በ...
29/05/2026

በአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ከ11 ሚሊየን 860 ሽህ በላይ ችግኞችን ለመትከል የቅድመ ዝግጅት ስራዋች እየተሰሩ መሆናቸው ተገለጸ።

ግንቦት 21/2018 ዓ.ም (ጎዛምን ኮሙኒኬሽን )

በምስራቅ ጎጃም ዞን የጎዛምን ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከ 11 ሚሊዮን 860 ሽህ በላይ ዘርፈ ብዙ ጥቅም ያላቸው ችግኞችን በ1ሽህ 931 ሄ/ር መሬት ላይ ለመትከል በዝግጅት ላይ መሆኑን አስታወቀ።

የወረዳው ግብርና ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ሀብታሙ ይታይህ ለወረዳው የመንግስት ኮሙኒኬሽን በሰጡት መግለጫ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ - ግብር የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም፤ የሙቀት መጠንን ለመቀነስና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን አስረድተዋል።

ሀላፊው አያይዘውም ከችግኝ ዝግጅት በተጨማሪ ለመርሀ ግብሩ ሌሎች የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ማለትም የጉድጓድ ቁፋሮ እና ተግባሩን ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ ለመምራት የካርታ ስራ እየተሰራ መሆኑን ጠቁዋል።

ማህበረሰቡ ችግኝ መትከል የሚያስገኘውን ዘላቂና ዘርፈ ብዙ ጥቅም በመረዳት የሚተከሉ ችግኞችን በአግባቡ መንከባከብ ያለበት መሆኑን እና ሌሎች ባለድርሻ አካላትም ሚናቸውን መወጣት ያለባቸው መሆኑን አቶ ሀብታሙ አክለው ገልፀዋል።

ለበለጠ መረጃ የጎዛምን ወረዳ ኮሙዩኒኬሽንን ይወዳጁ
‎ቲክቶክ : tiktok.com/
‎ቴሌግራም : https://t.me/+0lEq6W4-HkxjMzBk
‎ዩቲዩብ :https://youtube.com/?si=q5oxnXn3EmC4ABrq

የጥሞና ጊዜ ነገ ግንቦት 20 ቀን 2018 ዓ.ም ይጀምራል።የኢትዮጵያ  ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ!
27/05/2026

የጥሞና ጊዜ ነገ ግንቦት 20 ቀን 2018 ዓ.ም ይጀምራል።

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ!

ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. የድምፅ መስጫ ቀንን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫየኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም.  የ7ተኛው...
27/05/2026

ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. የድምፅ መስጫ ቀንን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. የ7ተኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ አሰጣጥ እንዲከናወን መወሠኑ ይታወቃል።

በዚህም መሠረት በመራጭነት የተመዘገቡ ዜጎች ሁሉ በዕለቱ ድምፃቸውን ለመስጠት ይችሉ ዘንድ እና የደምፅ አሰጣጥ ሂደቱ ያለምንም የፀጥታ ችግር ይከናወን ዘንድ ቦርዱ የሚከተሉት ተግባራዊ እንዲሆኑ የምርጫ የፓለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና ሥነ-ምግባር ዐዋጅ 1162/ 2011 አንቀጽ 161 የመተባበር ግዴታ መሠረት ለመንግሥታዊ እና ለማንኛውም መንግሥታዊ ላልሆኑ ተቋማት ያሳውቃል።

በዚህም መሠረት:-
- ዜጎች ዕለቱን ለድምፅ መስጫ ብቻ መጠቀማቸው ስለሚያስፈልግ የፌዴራል እና የክልል መንግሥታዊ ተቋማት ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ሥራ ዝግ እንዲያደርጉ፣

- ዜጎች ዕለቱን ለድምፅ መስጫ ብቻ መጠቀማቸው ስለሚያስፈልግ በፌዴራል እና በክልሎች የሚገኙ ማንኛውም መንግሥታዊ ያልሆኑ እና የግል ተቋማት በተመሳሳይ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ዝግ እንዲያደርጉ እያሳወቀ፤

- የአስቸኳይ ጊዜ አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማት፣ ሆስፒታሎች፣ የዕለት ተዕለት አገልግሎት ሰጪዎችም (ሆቴሎች፣ ሬስቶራንቶች፣ የትራንስፓርት አገልግሎት) በዝግ ቀናት የሚያደርጉትን አገልግሎት በተመሳሳይ የሚያከናውኑ ሲሆን፤ የመተባበር ግዴታው እነዚህን ተቋማት እንቅስቃሴ መዘጋት አያስገድድም።

- የትራንስፓርት አገልግሎት በተለመደው መንገድ የሚቀጥል ቢሆንም፤ ዜጎች ድምፅ ከመስጠት ውጪ ከፍተኛ እንቅስቃሴን የሚፈልጉ ሁነቶችን እና ዕቅዶችን እንዳይይዙ እና እንቅስቃሴያቸውን ድምፅ ለመስጠት ብቻ እንዲያደርጉ ቦርዱ ያበረታታል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
ግንቦት 19 ቀን 2018 ዓ.ም.

"ከሞፈር ወደ ትራክተር!"በምስራቅ ጎጃም ዞን በጎዛምን ወረዳ በተለያዩ ቀበሌዋች  "ከሞፈር ወደ ትራክተር " በሚል እሳቤ የትራክተር እርሻ ተጠናክሮ ቀጥሏል።ለበለጠ መረጃ የጎዛምን ወረዳ  ኮ...
27/05/2026

"ከሞፈር ወደ ትራክተር!"

በምስራቅ ጎጃም ዞን በጎዛምን ወረዳ በተለያዩ ቀበሌዋች "ከሞፈር ወደ ትራክተር " በሚል እሳቤ የትራክተር እርሻ ተጠናክሮ ቀጥሏል።

ለበለጠ መረጃ የጎዛምን ወረዳ ኮሙዩኒኬሽንን ይወዳጁ
‎ቲክቶክ : tiktok.com/
‎ቴሌግራም : https://t.me/+0lEq6W4-HkxjMzBk
‎ዩቲዩብ :https://youtube.com/?si=q5oxnXn3EmC4ABrq

 #በምስራቅ ጎጃም ዞን #በጎዛምን ወረዳ  #በማይ አንገታም ቀበሌ በ2ኛ ዙር መስኖ እየለማ  ያለ በቆሎ ከፊል ገፅታለበለጠ መረጃ የጎዛምን ወረዳ  ኮሙዩኒኬሽንን ይወዳጁ‎ቲክቶክ : tiktok...
27/05/2026

#በምስራቅ ጎጃም ዞን
#በጎዛምን ወረዳ
#በማይ አንገታም ቀበሌ በ2ኛ ዙር መስኖ እየለማ ያለ በቆሎ ከፊል ገፅታ

ለበለጠ መረጃ የጎዛምን ወረዳ ኮሙዩኒኬሽንን ይወዳጁ
‎ቲክቶክ : tiktok.com/
‎ቴሌግራም : https://t.me/+0lEq6W4-HkxjMzBk
‎ዩቲዩብ :https://youtube.com/?si=q5oxnXn3EmC4ABrq

በጎዛምን ወረዳ በተቀናጀ የግብርና ልማትና ቴክኖሎጅ ሽግግር ማዕከል ሲከናወን የቆየው የዓሳ ሀብት ልማት ተስፋ ሰጭ ውጤት ማሳየቱ ተገለፀ።ግንቦት 18/2018 ዓ.ም (ጎዛምን ኮሙዩኒኬሽን ) ...
26/05/2026

በጎዛምን ወረዳ በተቀናጀ የግብርና ልማትና ቴክኖሎጅ ሽግግር ማዕከል ሲከናወን የቆየው የዓሳ ሀብት ልማት ተስፋ ሰጭ ውጤት ማሳየቱ ተገለፀ።

ግንቦት 18/2018 ዓ.ም (ጎዛምን ኮሙዩኒኬሽን ) በምስራቅ ጎጃም ዞን በጎዛምን ወረዳ የተቀናጀ የግብርና ልማትና የቴክኖጅ ሽግግር ማዕከል ከዶሮ እና ከአትክልት ልማት ጋር ተቀናጅቶ ሲለማ የቆየውን የዓሳ ሀብት ከኩሬ የማውጣት ስራ ተሰርቷል።

በዚህ ኩሬ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የዓሳ ምርት ማምረት የተቻለ ሲሆን ዓሳው ከኩሬ በሚወጣበት ጊዜ በስራው ከፍተኛ ተሳትፎ ለነበራቸው ሙያተኞች ምስጋና ቀርቦላቸዋል።

የወረዳው የእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ካሳሁን አድማስ ከዚህ በፊት በወንዞችና በሀይቆች ተወስኖ የቆየውን የዓሳ ሀብት ልማት በማዕከሉ በሰው ሰራሽ ኩሬ ማልማት የተጀመረ መሆኑን ገልፀው ይህም በአነስተኛ ቦታ ከፍተኛ ምርት ለማግኘት የሚያስችል መሆኑን አመላክተዋል።

በቀጣይም ይህንን ተሞክሮ ለማስፋት ወጣቶችን በዘርፉ በማደራጀት ፣ስልጠና በመስጠትና አስፈላጊ ግብዓቶችን በማሟላት በዘርፉ ለማሰማራት እንደሚሰራ ሀላፊው አክለው ገልፀዋል።

የወረዳው የዓሳ ሀብት ልማት ባለሙያ የሆኑት ወ/ሮ ንግስት ስራው በበኩላቸው በወረደው ከ34 በላይ የሰው ሰራሽ የዓሳ ኩሬ የተዘጋጀ መሆኑን ጠቅሰው ከዚህም ከፍተኛ ምርት አየተገኘ መሆኑን ተናግረዋል።

ዓሳ ከፍተኛ ፕሮቲን፣ ቫይታሚንና ማዕድናት የያዘ በመሆኑ ከገቢ ማስገኛነቱ በተጨማሪ ለትውልድ ግንባታና ለምግብ ዋስትና መረጋገጥ ሚናው የጎላ መሆኑን ወ/ሮ ንግስት ጠቅሰዋል::

‎ለበለጠ መረጃ የጎዛምን ወረዳ ኮሙዩኒኬሽንን ይወዳጁ
‎ቲክቶክ : tiktok.com/
‎ቴሌግራም : https://t.me/+0lEq6W4-HkxjMzBk
‎ዩቲዩብ :https://youtube.com/?si=q5oxnXn3EmC4ABrq

🍀🌍 🌴"የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ኢትዮጵያ ዓለም አቀፉን የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ እንድታስተናግድ ዕድል ሰጥቷል።የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ በመጭው ክረምት ለሚካሄደው የአረንጓዴ አሻራ...
26/05/2026

🍀🌍 🌴"የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ኢትዮጵያ ዓለም አቀፉን የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ እንድታስተናግድ ዕድል ሰጥቷል።

የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ በመጭው ክረምት ለሚካሄደው የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ዝግጁነት እና ቀጣይ ተግባራትን በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አካሂዷል።

​የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ኅላፊ ደረጀ ማንደፍሮ እንዳብራሩት ፤ መርሐ ግብሩ ከተጀመረበት ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ በክልሉ፦
☘️ ከ10 ነጥብ 4 ቢሊዮን በላይ ችግኞች ተተክለዋል
☘️ የደን ሽፋኑን ከ14 ነጥብ 6 በመቶ ወደ 18 ነጥብ 9 በመቶ ማሳደግ ተችሏል።

እንደ ሀገር መርሐ ግብሩ በተባበረ ክንድ በአንድነት በተሠራው ውጤታማ ሥራ ስኬት መመዝገቡን ገልጸዋል።

ይህ ስኬት ለአየር ንብረት ለውጥ መቋቋም፣ ለምግብ ዋስትና እና ለውኃ አቅም መጎልበት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱንም አንስተዋል።

​የዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ የሁለተኛው ምዕራፍ ማጠናቀቂያ መኾኑን እና ኢትዮጵያ በዘርፉ ባሳየችው ውጤት የዓለም የአየር ንብረት ጉባኤን (ኮፕ 32) እንድታዘጋጅ መመረጧን ኀላፊው ገልጸዋል። ተቋማት የተጀመሩ ሥራዎችን በባለቤትነት እንዲያስቀጥሉም አስገንዝበዋል።

የአማራ ክልል መሬት ቢሮ ምክትል ኅላፊ አዳነ መሐሪ (ዶ.ር) የችግኝ ተከላው በመሬት አጠቃቀም ዕቅድ መሠረት የተፋሰስ የማልማት ሥራ እየተሠራ ነው ብለዋል።

ለመጭው ክረምት የችግኝ ማፍላት እና ለተከላ መሬትን የመለየት ሥራዎች እየተከናወኑ መኾኑን አንስተዋል። ደኖችን በዘላቂነት ለማልማት እንደሚሠሩም ተናግረዋል።

የተከላውን የጽድቀት መጠን ከፍ እንዲያደርግ እና መሬት ሳይጎሳቆል ለሚቀጥለው ትውልድ እንዲተላለፍ አደራን መወጣት እንደሚገባም ተገልጿል። በክልሉ ለመጭው ክረምት በፍሬ ከ1 ነጥብ 7 ቢሊዮን በላይ ችግኝ ለተከላ ለማዘጋጀት ታቅዶ ተግባራት እየተከናወኑ መኾኑም ተገልጿል።

‎ #ኢትዮጵያ

የምክትል ጠቅላይ ሚነስትር ተመስገን ጥሩነህ መልዕክት******የተፈጥሮ እውነት ከታሪክ ክብር ጋር በተዋሃደባት፣ በጣና ሐይቅና በዓባይ ወንዝ በታጀበችው የውበት ማማዋ ባሕር ዳር ገብተናል።ባሕ...
25/05/2026

የምክትል ጠቅላይ ሚነስትር ተመስገን ጥሩነህ መልዕክት
******

የተፈጥሮ እውነት ከታሪክ ክብር ጋር በተዋሃደባት፣ በጣና ሐይቅና በዓባይ ወንዝ በታጀበችው የውበት ማማዋ ባሕር ዳር ገብተናል።

ባሕር ዳር ከተማ በልማት ጎዳና ላይ የምታሳየው መነቃቃት የነገ ተስፋችንን በተጨባጭ የሚያሳይ ነው።

ባሕር ዳር ደጃዝማች በላይ ዘለቀ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ስንደርስ፣ ፍቅርና አክብሮት በተሞላበት ሁኔታ ለተደረገልን ደማቅ አቀባበል ለአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር፣ ለክልሉና ለከተማዋ ከፍተኛ አመራሮች፣ በጸሎትና በምርቃታቸው ላልተለዩን የሃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች እንዲሁም ለመላው የባሕር ዳር ሕዝብ ከልብ የመነጨ ምስጋናዬን አቀርባለሁ።

Address

T'is Abay

Telephone

+251587713817

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gozamin woreda communication affairs posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Gozamin woreda communication affairs:

Share