Yeki Woreda Communications

Yeki Woreda Communications Teppi

በድጋሚ የተሰጠ መግለጫየኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ከማለዳ 12:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ምሽት 12:00 ሰዓት የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ የማስ...
01/06/2026

በድጋሚ የተሰጠ መግለጫ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ከማለዳ 12:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ምሽት 12:00 ሰዓት የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ የማስፈጸም ሂደት ላይ እንደነበር ይታወቃል። ቦርዱ በሥምሪት ላይ ያለው የክትትል ቡድኑ ያቀረበለትን ሪፖርት ተመልክቶ የሚከተለውን ወሥኗል።

በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር ዐዋጅ 1162/2011 አንቀጽ 49(4) መሠረት ቦርዱ የምርጫው ነፃና ፍትሐዊነት ይበልጥ ያሰፍናል ብሎ ካመነ የድምፅ መስጫ ሰዓቱን ሊያራዝም እንደሚችል በግልጽ ይደነግጋል። በመሆኑም የድምፅ መስጫ ሂደት ባልተጠናቀቀባቸው የምርጫ ጣቢያዎች ላይ ድምፅ የመስጠት ሂደቱ እስከ ዕኩለ ለሊት 6:00 ሰዓት ድረስ የተራዘመ መሆኑን ቦርዱ ያሳውቃል።

ማሳሰቢያ: የተመዘገቡ መራጮች መርጠው የተጠናቀቁባቸው ጣቢያዎች ላይ አስፈጻሚዎች የድምፅ ቆጠራ ሂደቱን እንዲያከናውኑ ቦርዱ ያስታውሳል።

በሸካ ዞን በቴፒ የምርጫ ክልል የሚገኙ የተፎካካሪ ፓርቲ ተወካዮች በተለያዩ የምርጫ ጣቢያዎች ተገኝተው ድምጽ ሰጥተዋል።የኢዜማ፣የነጻነትና እኩልነት ፓርቲ እንዲሁም የሰላም ለጥምረት ተወካዮች ...
01/06/2026

በሸካ ዞን በቴፒ የምርጫ ክልል የሚገኙ የተፎካካሪ ፓርቲ ተወካዮች በተለያዩ የምርጫ ጣቢያዎች ተገኝተው ድምጽ ሰጥተዋል።

የኢዜማ፣የነጻነትና እኩልነት ፓርቲ እንዲሁም የሰላም ለጥምረት ተወካዮች ድምጻቸውን ሰጥተዋል።

SZC

‎ነፃ፣ዲሞክራሲያዊና፣ፍትሐዊ እንዲሁም ሰላማዊ ምርጫ እያካሄድን ነው ሲሉ በሸካ ዞን ቴፒ ምርጫ ክልል የሚገኙ የተፎካካሪ ፓርቲዎች ገለፁ።‎‎በ7ተኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ በቴፒ ምርጫ ክልል ...
01/06/2026

‎ነፃ፣ዲሞክራሲያዊና፣ፍትሐዊ እንዲሁም ሰላማዊ ምርጫ እያካሄድን ነው ሲሉ በሸካ ዞን ቴፒ ምርጫ ክልል የሚገኙ የተፎካካሪ ፓርቲዎች ገለፁ።

‎በ7ተኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ በቴፒ ምርጫ ክልል አምስት የተፎካካሪ ፓርቲዎች የሚገኙ ሲሆን የብልፅግና፣ሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት ፣ኢዜማ፣ ነፃነት እና እኩልነት ፓርቲ እንዲሁም ወሎ ህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ፓርቲዎች ይገኙበታል ።

‎ተፎካካሪ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አቋቁመው ነፃ ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ ምርጫ ለማድረግ ከገዥው ፓርቲ ጋር እየሰሩ መቆየታቸውን የሚናገሩት ተፎካካሪዎቹ ፍፁም ሰላማዊ ፣ነፃ፣ዲሞክራሲያዊ ምርጫ እያካሄዱ መሆናቸውን ገለፀዋል ።

‎የተፎካካሪ ፓርቲዎች ለሀገር ግንባታ እኩል ተሳታፊ በመሆን ሀሳባቸውን ማቅረብ እንዲችሉ መደረጉ እንዲሁም አሁን ላይ ያለምንም የፀጥታ ችግር ምርጫው እየተካሄደ መሆኑና አሳታፊ የፖለቲካ ምህዳር መፈጠሩ ልዩ ያደርገዋል ብለዋል።

‎የህዝብ ድምፅ በማክበር የምርጫ ውጤት በሰላማዊ መንገድ ለመቀበል ዝግጁ መሆናቸውንም ተፎካካሪዎች ገልፀዋል

ሸካ ቲቪ


የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት ዋና አፌ ጉባኤ  አቶ ወንድሙ ኩርታ በሸኮ ከተማ 01 ቀጠና በሸኮ ልዩ ምርጫ ጣቢያ  በመገኘት ጽምጽ ሰጡ።አፌ ጉባኤዉ በሂደቱም ውጤቱ ኢትዮ...
01/06/2026

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት ዋና አፌ ጉባኤ አቶ ወንድሙ ኩርታ በሸኮ ከተማ 01 ቀጠና በሸኮ ልዩ ምርጫ ጣቢያ በመገኘት ጽምጽ ሰጡ።

አፌ ጉባኤዉ በሂደቱም ውጤቱ ኢትዮጵያ የምታሸንፍበት ምርጫ እየተካሄደ መሆኑን ተመልክቻለሁ ብለዋል።

ዋና አፌ ጉባኤ አቶ ወንድሙ ኩርታ በሸኮ ልዩ ምርጫ ክልል የክልል ምክር ቤት ዕጩ ተወዳዳሪ የሆኑት በሸኮ ከተማ 01 ቀጠና የሸኮ ልዩ ምርጫ ጣቢያ በመገኘት ጽምጽ ሰጥተዋል።

በምርጫው ሂደትና በውጤቱ ኢትዮጵያ እንድታሸንፍ ገዢውና ተፎካካሪ ፓርቲዎች በጋራ እየሰሩ እንደሚገኙም ክቡር አፌ ጉባኤ ተናግረዋል ሲል የቤንች ሸኮ ዞን ኮሙኒኬሽን ዘግቧል።

የሸካ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አበበ ማሞ፣ የኢዜማ ፓርቲ ዕጩ ተወዳዳሪዎች አቶ በላቸዉ አለሙና  ሮቤል በላይ በማሻ ምርጫ ክልል በተለያዩ ምርጫ ጣቢያ በመገኘት ድምጽ ሰጥተዋል።
01/06/2026

የሸካ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አበበ ማሞ፣ የኢዜማ ፓርቲ ዕጩ ተወዳዳሪዎች አቶ በላቸዉ አለሙና ሮቤል በላይ በማሻ ምርጫ ክልል በተለያዩ ምርጫ ጣቢያ በመገኘት ድምጽ ሰጥተዋል።

አቶ ዳዊት ተሰማን ጨምሮ ሌሎችም መራጮች በቴፒ ምርጫ ክልል አንድነት ምርጫ ጣቢያ!
01/06/2026

አቶ ዳዊት ተሰማን ጨምሮ ሌሎችም መራጮች በቴፒ ምርጫ ክልል አንድነት ምርጫ ጣቢያ!

በቴፒ የምርጫ ክልል የጻኑ ምርጫ ጣቢያ መራጮች
01/06/2026

በቴፒ የምርጫ ክልል የጻኑ ምርጫ ጣቢያ መራጮች

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ድምፃቸውን ሰጡየደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)...
01/06/2026

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ድምፃቸውን ሰጡ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በሚወዳደሩበት የምርጫ ክልል በመገኘት ድምፃቸውን ሰጥተዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ የገዥውን የብልፅግና ፓርቲን ወክለው ለክልሉ ምክር ቤት አባልነት እየተወዳደሩ እንደሚገኙ የታወቀ ሲሆን፣ ዛሬ ማለዳ ላይ በሚመረጡበት የምርጫ ክልል በመገኘት ነው የመምረጥ መብታቸውን የተጠቀሙት።

ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ድምፃቸውን ከሰጡ በኋላ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፤ የክልሉ ህዝቦች በነቂስ ወጥተው በያዙት የመራጭነት ካርድ ለቀጣይ የዕድገትና የተሻለች አገር የሚበጃቸውንና የሚወክላቸውን ፓርቲ እንዲመርጡ ጥሪ አቅርበዋል።

በክልሉ እየተካሄደ ባለው በዚህ ምርጫ ህዝቡ በከፍተኛ መነሳሳት ድምፅ እየሰጠ እንደሚገኝና ሂደቱም በሰላማዊ ሁኔታ እየተከናወነ መሆኑ ተገልጿል ሲል የዘገበው SWMN

24/09/2018 ዓ.ም በሸካ ዞን በየኪ ወረዳ ምርጫ ክልል በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች  ላይ መራጮች ማልደው በመነሳት ድምፅ እየሰጡ ነው፡፡‎የድምፅ አሰጣጡ ከማለዳ 12፡00 ሰዓት የጀመረው  ...
01/06/2026

24/09/2018 ዓ.ም በሸካ ዞን በየኪ ወረዳ ምርጫ ክልል በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች ላይ መራጮች ማልደው በመነሳት ድምፅ እየሰጡ ነው፡፡

የድምፅ አሰጣጡ ከማለዳ 12፡00 ሰዓት የጀመረው እስከ ምሽት 12፡00 ሰዓት ድረስ እንደሚቀጥል የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋ አድርጓል፡፡

‎ሸካ ቴቪ

በቴፒ ምርጫ ክልል ቴፒ ከተማና አካባቢዋ ባሉት የምርጫ ጣቢያዎች  መራጮች ድምፅ መስጠት ጀምረዋል።‎‎ሕዝቡ ከማለዳ ጀምሮ በመውጣት በምርጫው ተሳትፎ እያደረገ ሲሆን፥ የድምጽ መስጠት ሂደቱ የ...
01/06/2026

በቴፒ ምርጫ ክልል ቴፒ ከተማና አካባቢዋ ባሉት የምርጫ ጣቢያዎች መራጮች ድምፅ መስጠት ጀምረዋል።

‎ሕዝቡ ከማለዳ ጀምሮ በመውጣት በምርጫው ተሳትፎ እያደረገ ሲሆን፥ የድምጽ መስጠት ሂደቱ የምርጫ ታዛቢዎች በተገኙበት እየተካሄደ ይገኛል፡፡

‎በቴፒ ምርጫ ክልል ከሚገኙ 150 የምርጫ ጣቢያዎች የሚገኙ ሲሆን በምርጫ ጣቢያዎች መራጮች ድምፅ መስጠት ጀምረዋል።

‎በምርጫ ክልሉ 5 የተፎካካሪ ፓርቲዎች የሚወዳደሩ ሲሆን አምስት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አምስት እጩዎች እንዲሁም 37 የክልል ምክር ቤት እጩዎች አቅርበዋል ።

‎ሸካ ቲቪ

Address

Tepi

Telephone

+251984910016

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Yeki Woreda Communications posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share