Yeki Woreda Communications

Yeki Woreda Communications Teppi

በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት 309 ሚልዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ መቻሉን በሸካ ዞን የየኪ ወረዳ ገቢዎች ባለስልጣን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ገለፀ። የየኪ ወረዳ ገቢዎች ባለስልጣን ቅርንጫፍ...
03/09/2026

በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት 309 ሚልዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ መቻሉን በሸካ ዞን የየኪ ወረዳ ገቢዎች ባለስልጣን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ገለፀ።

የየኪ ወረዳ ገቢዎች ባለስልጣን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሰለሞን ደረሻ በበጀት ዓመቱ ገቢን አሟጦ በመጠቀም "የውስጥ ወጪን በውስጥ ገቢ መሸፈን" በሚል መሪ ሐሳብ 70 በ 30ን ተግባራዊ በማድረግ የዕቅዱን 95 በመቶ ማሳካት መቻሉን ነው የተናገሩት።

በዚህም በተገባደደው በጀት ዓመት ከመደበኛና ከማዘጋጃ ቤት 323 ሚልዮን 9መቶ 38ሺ 5መቶ ብር ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ 309 ሚልዮን 9መቶ 77ሺ 8መቶ ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ መቻሉን ተናግረዋል።

ይህም ከአለፈው በጀት ዓመት ገቢ ሲነፃፀር የተሻለ ውጤት መሆኑን የገለፁት ሃላፊው በዚህም 95በመቶ ማሳካት ተችሏል ብለዋል።

ለሥራው መሳካት ትኩረት ተደርጎ መሰራቱን ጠቅሰው መቶ በመቶ እንዳይሳካ ተግዳሮት የሆነው የባለድርሻ አካላት ቅንጅታዊ አሰራር ማነስና የህገወጥ ነጋደ መስፋፋት እንደክፍተት የተመዘገበ መሆኑን ተናግረዋል።

የ2019 ገቢ ጠቅላላ እቅድ በተመለከተ ከመደበኛና ከማዘጋጃ ቤት 573ሚልዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ ስራዎች መጀመራቸውን የገለፁት ኃላፊው እቅዱ እንዲሳካ ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

በቀጣይም የተሻለ አፈፃፀም ለማስፈፀም ባለድርሻ አካላት ቅንጅታዊ አሰራር እንደሚያስፈልግና ግብር ከፋዩ ህብረተሰብም በተሰጠው የጊዜ ገደብ ከቅጣት ነፃ በመሆን ግብሩን ሊከፍል እንደሚገባ ጥሪ አስተላልፈዋል።

Sheka Tv

መጪዎቹ የጳጉሜን ቀናት "የኢትዮጵያ ማንሰራራት" በሚል መሪ ሀሳብ ይከበራሉ መጪዎቹ የጳጉሜን ቀናት "የኢትዮጵያ ማንሰራራት" በሚል መሪ ሀሳብ በተለያዩ ስያሜዎች ይከበራሉ አለ የመንግሥት ኮሙ...
02/09/2026

መጪዎቹ የጳጉሜን ቀናት "የኢትዮጵያ ማንሰራራት" በሚል መሪ ሀሳብ ይከበራሉ

መጪዎቹ የጳጉሜን ቀናት "የኢትዮጵያ ማንሰራራት" በሚል መሪ ሀሳብ በተለያዩ ስያሜዎች ይከበራሉ አለ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት፡፡

የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ከበደ ዴሲሳ በዛሬው ዕለት በሰጡት መግለጫ፥ የተገባደደው ዓመት የኢትዮጵያን የማንሰራራት ጉዞ ጅማሮ የሚያመላክቱ ስኬቶች የተመዘገበበት ነው ብለዋል፡፡

በዚህም ምክንያት መጪዎቹ የጳጉሜን ቀናት "የኢትዮጵያ ማንሰራራት" በሚል መሪ ሀሳብ በተለያዩ ስያሜዎች እንደሚከበሩ አመልክተዋል፡፡

ጳጉሜን 1 - የእመርታ ቀን - ኢትዮጵያ ከአዝጋሚ እድገት ተላቅቃ ወደ ፈጣንና እመርታዊ የእድገት ምህዋር መግባቷን የምናሳይበት ቀን ነው ብለዋል፡፡

ይህ ዕለት በሁሉም ዘርፍ የተሰሩ ሥራዎችን እመርታዊ ለውጥ የምናስገነዝብበት ይሆናል ነው ያሉት፡፡

ጳጉሜን 2 - የማንሰራራት ቀን - 2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ ከአዝጋሚ እድገት ወደ ሁለንተናዊ ከፍታ መሸጋገር የጀመረችበት ዓመት በመሆኑ ዕለቱ የማንሰራራት ቀን የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡

ጳጉሜን 3 - የጽናት ቀን በሚል ስያሜ ይከበራል፤ ኢትዮጵያ ለዘመናት ጠብቃው የኖረችውን ነጻነትና ሉዓላዊነት ማስቀጠል የዛሬው ትውልድ ኃላፊነት መሆኑን ለማስገንዘብ ዕለቱ የጽናት ቀን የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል ብለዋል፡፡

ጳጉሜን 4 - የኅብር ቀን

ኢትዮጵያ የብዝሃ ማንነቶች ሀገር እንደመሆኗ ብዝሃነት ጌጣችንና ኅብረታችን ነው፤ ኅብረታችን ደግሞ የአንድነትና የጥንካሬያችን ምንጭ መሆኑን በማውሳት፤ ዕለቱ የኅብር ቀን መባሉን አስረድተዋል፡፡

ጳጉሜን 5 - የነገ ቀን የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡ ዓላማውም ኢትዮጵያ ነገዋን ዛሬ እየሰራች እንደምትገኝ ማስገንዘብ መሆኑን አመልክተዋል፡፡

የየኪ ወረዳ የ2018 የበጀት አመት የአፈጻፀም ግምገማና የአመራር ምዘና መድረክ መካሄድ ጀመረ።የኪ ወረዳ፣ነሀሴ፣27/2018(መ.ኮ) "ከምርጫ ድል ማግስት ጠንካራ መንግስት!!" በሚል መሪ ቃ...
02/09/2026

የየኪ ወረዳ የ2018 የበጀት አመት የአፈጻፀም ግምገማና የአመራር ምዘና መድረክ መካሄድ ጀመረ።

የኪ ወረዳ፣ነሀሴ፣27/2018(መ.ኮ) "ከምርጫ ድል ማግስት ጠንካራ መንግስት!!" በሚል መሪ ቃል የየኪ ወረዳ የ2018 የበጀት አመት ማጠቃለያ የአፈጻፀም ግምገማና የአመራር ምዘና መድረክ በቴፒ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል ።

በምዘና መድረኩ የሸካ ዞን ትራንስፖርት መንገድ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ ሀብታሙ ሀራ የበጀት ዓመቱን አፈጻጸም በጥልቀት በመፈተሽ በጥንካሬ የተመዘገቡትን አጠናክሮ ለማስቀጠል፣ ድክመቶችን ለማረም እና አመራሩን ለቀጣይ ተልዕኮዎች በብቃት እንዲወጣ ዝግጁ እንዲሆን ለማድረግ ወሳኝ መሆኑን አመላክተዋል ።

በመድረኩ ላይ የወረዳው አጠቃላይ አመራር እየተሳተፉ ሲሆን የግምገማና ምዘና መድረኩ ለተከታታይ ሦስት ቀናት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተመላክቷል።

የግምገማውን መድረክ የሸካ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ እምሩ ወየሳ እና የሸካ ዞን ትራንስፖርት መንገድ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ ሀብታሙ ሀራ በጋራ እየመሩት የግምገማና የምዘናው መድረክ ለተከተከታታይ ሦስት ቀናት ይዘልቃል።

✍️ በታደለ ሙላቱ

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተሉን 👇👇👇

‎📌በፌስቡክ፦https://www.facebook.com/share/1KGkocwz6c/
‎📌በቴሌግራም፦https://t.me/+4cC0zGkM4SU4NTg0

የክልሉ መስተዳድር ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 53ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የመስተዳድር ምክር ቤት  በዛሬው ዕለት...
01/09/2026

የክልሉ መስተዳድር ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 53ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የመስተዳድር ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 53ኛ መደበኛ ስብሰባው በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አስተላልፏል ፡፡

በዚህም መሠረት መስተዳድር ምክር ቤቱ የክልሉ መንግስት የካፒታል ፕሮጀክቶች በጀት አመዳደብ ላይ ተወያይቶ አቅጣጫ አስቀምጧል።

በሁለተኛ አጀንዳነት ምክር ቤቱ የቀረቡ የኢንቨስትመንት ጥያቄዎች ላይ ተወያይቶ የተለያዩ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸውን በግብርና 30፣ በአገልግሎት 7 በአጠቃላይ 4 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ 37 የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ጥያቄዎችን መርምሮ ወደ ስራ እንዲገቡ ወስኗል።

በሶስተኛ አጀንዳነት በተለያዩ ረቂቅ ደንቦች ላይ የተወያየ ሲሆን በዚህም የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የአደጋ ጊዜ ዝግጁነት፣ምላሽና መልሶ ማቋቋሚያ ፈንድን እንደገና ለማሻሻል እና የክልሉ ሰነዶች ማረጋገጥና ምዝገባ አገልግሎት ክፍያ ደንብን መርምሮ አጽጽቋል ሲል የክልሉ ኮሙኒኬሽን ዘግቧል።

ላለፉት ተከታታይ አራት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የሸካ ዞን የ2018 በጀት ዓመት ማጠቃለያ የአመራር ግምገማና ምዘና መድረክ ተጠናቋልበመድረኩ ማጠቃለያ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የክልሉ ር...
01/09/2026

ላለፉት ተከታታይ አራት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የሸካ ዞን የ2018 በጀት ዓመት ማጠቃለያ የአመራር ግምገማና ምዘና መድረክ ተጠናቋል

በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ልዩ አማካሪ አቶ ሰብስቤ ሻወኖ፤ በግምገማና ምዘናው በጉድለት የተነሱ ጉዳዮችን ማረምና ውጤታማ አፈጻጸሞችን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ ገልጸዋል።

​አመራሩ ለህዝብ ተጠቃሚነት መስራት እንዳለበት ያሳሰቡት አቶ ሰብስቤ፣ በተቋማት የሚስተዋሉ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮችን ማረም እንደሚገባም አሳስበዋል።

የፓርቲ ኢኒሼቲቮችንና ተቋማዊ ተልዕኮን በውጤታማነት መፈጸም እንዲሁም የህዝብ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጡ ተግባራትን በቁርጠኝነት መፈጸም ይገባል ብለዋል።

​ዞኑ ሰፊ እምቅ አቅም ያለው በመሆኑ፣ ያለውን አቅምና ሀብት በማቀናጀት ለህዝብ ተጠቃሚነት ማዋል እንደሚገባም ጠቁመው፣ ገቢን አሟጦ በመሰብሰብ የህዝብ ጥያቄዎችን መመለስ እንደሚገባ አንስተዋል።

በከተማና በገጠር የሚታዩ ህገወጥነትና ብልሽቶችን በፍጥነት ማረም፣ የህግ የበላይነትን ማረጋገጥና ተጠያቂነትን ማስፈን እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

​በዞኑ በየደረጃው የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ የልማት ፕሮጀክቶችን በቅንጅት ማስቀጠልና የሚታዩ የአፈጻጸም ጉድለቶችን በወቅቱ በመፈተሽ ውጤታማነትን ማረጋገጥ እንደሚገባ ገልጸዋል።

በየደረጃው የድጋፍና ክትትል ሥራዎችን በማጠናከር የፕሮጀክቶችን ውጤታማ አፈጻጸም ማረጋገጥ እንደሚገባም ጠቁመዋል።

​በተቋማት የአሰራር ሥርዓትን መዘርጋትና አመራሩ የፓርቲና የመንግሥት ተልዕኮዎች በውጤታማነት መፈጸም እንዳለበትም አሳስበዋል።

አመራሩ በተመደበበት የሥራ ኃላፊነት ላይ በቁርጠኝነትና በኃላፊነት ስሜት በመሥራት፣ በሥነ-ምግባር የታነፀና ከብልሹ አሠራር የጸዳ ሆኖ መምራት እንዳለበትም አስገንዝበዋል።

​የክልሉ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ም/ኃላፊ አቶ ጫናቸው ወንድሙ በበኩላቸው፤ አመራሩ የአስተሳሰብና የተግባር አንድነትን በማረጋገጥ ለህዝብ ተጠቃሚነት መስራት እንዳለበት ገልጸዋል።

የሥነ-ምግባር ብልሽቶች መታረም እንዳለባቸው ያሳሰቡት አቶ ጫናቸው፣ በብልሹ አሠራር ውስጥ ያሉ አመራሮችን የማረምና የአሠራር ሥርዓት መዘርጋት እንደሚገባ አመላክተዋል ።

​በተቋም ደረጃም የፓርቲ አደረጃጀትን በማጠናከር የተቀናጀና ውጤታማ አፈጻጸምን ማረጋገጥ እንደሚገባ አቶ ጫናቸው አሳስበው የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ማሳደግ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

​የመድረኩ ተሳታፊ አመራሮች በበኩላቸው፤ በበጀት ዓመቱ የታቀዱ የፓርቲና የመንግሥት ተግባራትን በተሻለ ውጤት ለመፈጸም ቁርጠኛ መሆናቸውን ገልጸዋል። የግምገማና ምዘናው በቀጣይ ተልዕኮዎችን በውጤታማነት ለመፈጸም አስተዋጽኦ እንዳለውም አንስተዋል ሲል የዞኑ ኮሙኒኬሽን ዘግቧል።

በአካባቢው በተለያዩ የግብርና ዘርፎች የተሰማሩ ባለሀብቶች የምርትን ጥራት ቁጥጥር ከማድረግ በተጨማሪ የመንግሥትን የልማት ሥራዎች እንዲደግፉ ተጠየቀ ።የየኪ ወረዳ አስተዳደር በቡናና በቅመማ ...
01/09/2026

በአካባቢው በተለያዩ የግብርና ዘርፎች የተሰማሩ ባለሀብቶች የምርትን ጥራት ቁጥጥር ከማድረግ በተጨማሪ የመንግሥትን የልማት ሥራዎች እንዲደግፉ ተጠየቀ ።

የየኪ ወረዳ አስተዳደር በቡናና በቅመማ ቅመም የእርሻ ዘርፍ ከተሰማሩ የግል ባለሀብቶችና ተወካዮች ጋር በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አካሂዷል ።

ውይይቱ በዋናነት ባለሀብቶቹ የምርታቸውን ጥራት ቁጥጥር እንዲያደርጉ፣ በሥራ ዕድል ፈጠራ ዘርፎች ላይ ትኩረት እንዲሰጡና የመንግሥትን የልማት ስራዎች እንዲደግፉ ዓላማ ያደረገ ነው ።

በየኪ ወረዳ በስፋት የሚመረተው የቡና ምርት ጥራቱን እንዲጠብቅና ከዘርፉ የተሻለ ገቢ እንዲገኝ የዘመኑ ቴክኖሎጅዎችን ተግባራዊ ከማድረግ በተጫማሪ ወቅቱን በሚመጥን መልኩ ምርቶችን መሰብሰብ ያስፈልጋል ተብሏል ።

በዜንድሮ የምርት ዘመን ጥራቱን በጠበቀ መንገድ የተሻለ የቡና ምርት ለማግኘት እየተሰሩ ባሉ ስራዎች ባለሀብቶቹ ጥራት ቁጥጥር ላይ ትኩረት በመስጠት የድርሻውን ለወጡ ይገባቸዋል ተብሏል ።

ኢንቨስትመንት በአካባቢው መኖር ለወጣቶች የሥራ ዕድሎች ከመፍጠር አኳያ ትልቅ ሚና እንዳለው የተነሳ ስሆን ባለሀብቶቹ ወጣቶችን ወደ ሥራ ከማስገባት አንፃር ትኩረት እንዲሰጡ ተነስቷል ።

በመንግሥትና እንዲሁም በህብረተሰቡ ተሳትፎ የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ከዳር እንዲደርሱ ባለሀብቶቹ የድርሻውን እንዲወጡም ጭምር ተጠይቋል ።

በኢንቨስትመንት አካባቢዎች ላይ ለሚነሱ የመልካም አስተዳደር ጉዳዮች መፍትሔ ለመስጠት የወረዳ መንግሥት ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን እንደሚሰራ አረጋግጧል ።

የምርት ጥራት ቁጥጥር ፣ለወጣቶች የሥራ ዕድሎችን ከመፍጠር አንፃር እንዲሁም የመንግሥትን የልማት ሥራዎች ለመደገፍ በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ ባለሀብቶቹ በበኩላቸው ገልፀዋል ።

ሀያ ስድስት መዳበሪያ ያልበሰለ እንጭጭ ቡና ማስወገዱን የየኪ ወረዳ ቡና ግብረ ሀይል ገለፀየኪ ወረዳ፣ነሀሴ 25/2018 ዓ.ም(መ.ኮ)የቡና ግብረ ሀይሉ በየኪ ወረዳ አቻኒ ቀበሌ ዮናስ ታረቀኝ...
31/08/2026

ሀያ ስድስት መዳበሪያ ያልበሰለ እንጭጭ ቡና ማስወገዱን የየኪ ወረዳ ቡና ግብረ ሀይል ገለፀ

የኪ ወረዳ፣ነሀሴ 25/2018 ዓ.ም(መ.ኮ)የቡና ግብረ ሀይሉ በየኪ ወረዳ አቻኒ ቀበሌ ዮናስ ታረቀኝ ቡናና ቅመማ ቅመም ከተሰኘ የግል ድርጅት የቡና ማሳ በህገ ወጥ መንገድ የተሸመጠጠ 26 ማዳበሪያ ያልበሰለ እንጭጭ ቡና በህግ ቁጥጥር ስር በማዋል ማስወገዱን ገልጿል።

የየኪ ወረዳ ግብርና አካባቢ ጥበቃና ህብረት ስራ ጽ/ቤት ቡና ሻይ ቅመማ ቅመም ምርት ዝግጅትና ጥራት ቁጥጥር ቡድን መሪ አቶ አሳቀኝ አድራሮ እንደገለፁት ዮናስ ታረቀኝ ቡናና ቅመማ ቅመም ከተሰኘ የግል ድርጅት የቡና ማሳ ህገ ወጥ 26 ማዳበሪያ ያልበሰለ እንጭጭ ቡና በህግ ቁጥጥር ስር ውሎ በግብረ ሀይል መወገዱን ተናግረዋል።

ከዚህ ጋር በተያያዘ ከተወገደው ያልበሰለ ቡና በተጨማሪ በድርጅቱ የቡና አውድማ ላይ ተሰጥቶ የሚገኝ የጥራት ደረጃው የተጓደለ እንጭጭ ቡና በግብረ ሀይልና በፀጥታ አካላት አማካኝነት የማስወገድ ስራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል።

ድርጊቱ ከአንድ ትልቅ ኢንቨስትመንት ድርጅት የማይጠበቅ የወረዳውን ገፅታ የሚያበላሽ በመሆኑ የተወሰደው እርምጃ ለአርሶ አደሩ እና በቡና ላይ ለተሰማሩ ባለሀብቶች ማስተማሪያ መሆኑን ነው የገለፁት።

የወረዳው የቡና ደረጃ ባለፉት አመታት በጥራት ጉድለት ምክንያት ዩጂ እና ደረጃ አምስት ውስጥ የቆየ እንደነበር አስታውሰው በተገባደደው የበጀት አመት ግብረ ሀይሉ እና የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በሰሩት ሰፊ ስራ የወረዳው የቡና ደረጃ ደረጃ ሶስትና የታጠበ ቡና ደረጃ አንድ የወጣበት አግባብ መኖሩን ገልፀው የቡና ጥራት ቁጥጥር እና የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራው በ2019 የበጀት አመትም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ነው የተናገሩት።

አርሶ አደሩና የቡና አልሚ ድርጅቶች የወረዳውን የቡና ጥራትና ደረጃ ለማሻሻል በሚሰራው ዘርፈ ብዙ ስራ የበሰለ ቡና ብቻ በመልቀምና በጥራት በማዘጋጀት የበኩላቸውን ድርሻ ሊወጡ እንደሚገባ አቶ አሳቀኝ አድራሮ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

በመጨረሻም የወረዳው ግብረ ሀይል የሀገር የኢኮኖሚ ዋልታ በሆነው የቡና ጥራት ጉዳይ የማይደራደርና የቡና ጥራትን አጓድለው በሚገኙ አርሶ አደሮችና የቡና አልሚ ድርጅቶች ላይ በህግ አግባብ ተጠያቂ እንደሚያደርጋቸው ነው ያሳሰቡት።

✍️ በታደለ ሙላቱ

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተሉን 👇👇👇

‎📌በፌስቡክ፦https://www.facebook.com/share/1KGkocwz6c/
‎📌በቴሌግራም፦https://t.me/+4cC0zGkM4SU4NTg0

የየኪ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳዊት ተሰማ ሪቫን በመቁረጥ የኪ ቀበሌን የ24 ሰአት የመብራት አገልግሎት ተጠቃሚ መሆንዋን በይፋ አብስረዋል።የኪ ወረዳ፣ነሀሴ 24/2018 (መ.ኮ) በሸካ ዞ...
30/08/2026

የየኪ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳዊት ተሰማ ሪቫን በመቁረጥ የኪ ቀበሌን የ24 ሰአት የመብራት አገልግሎት ተጠቃሚ መሆንዋን በይፋ አብስረዋል።

የኪ ወረዳ፣ነሀሴ 24/2018 (መ.ኮ) በሸካ ዞን የኪ ወረዳ የኪ ቀበሌ ከ40 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት የ24 ሰአት የመብራት አገልግሎት ተጠቃሚ መሆን ችላለች።

ዋና አስተዳዳሪው አቶ ዳዊት ተሰማ በመብራት አገልግሎት ማስጀመሪያ የምረቃ ስነ ስርት ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር የኪ ቀበሌ የረጅም ጊዜ ታሪክ ያላት ቢሆንም ለዘመናት የመብራት አገልግሎት ሳታገኝ የቆየች ቢሆንም ዛሬ ላይ የመብራት አገልግሎት ማግኘት መቻሏ ለቀበሌው ህዝብ ታላቅ ደስታ የፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል።

ክልሉ የቀበሌው ህብረተሰብ የመብራት ጥያቄ በመረዳት የወረዳውንና የዞኑን ጥያቄ ተቀብሎ መደመር እሳቤ ምላሽ እንዲያገኝ ማድረጉ የቀበሌውን ህዝብን የመልማት ፍላጎት ምላሽ የሰጠ መሆኑን ገልፀዋል።

ብልፅግና በገባው ቃል መሰረት አርሶ አደሩ ባለበት የመብራት አገልግሎት ተጠቃሚ እንዲሆን ሰፊ ስራ ሲሰራ መቆየቱን አስታውሰው የመንገድ ጥገና ስራውም ጎን ለጎን እየተሰራ እንደሚገኝና የቀበሌውን የልማት ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት መንግስት ከፍተኛ ስራ እየሰራ እንደሚገኝ ገልፀዋል።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ሀገር አቀፍ የኤሌክትሪክ አቅርቦት ፕሮግራም ቢሮ ኃላፊው አቶ ክፍሌ አጭማቸው መብራት ቅንጦት ሳይሆን የዜጎች መሰረታዊ ፍላጎት ነው ብለዋል።

በክልሉ በተለያዩ ምክንያቶች ከ6 መቶ በላይ ቀበሌዎች የመብራት አገልግሎት ተደራሽ ያልሆኑባቸው መኖራቸውን አስታውሰው ከዚህም ውስጥ አንዷ የኪ ቀበሌ ስትሆን ዛሬ ላይ የመብራት ተጠቃሚ መሆን ችላለች ብለዋል።

መንግስተ ከህዝቡ ለሚነሱ የመብራት አገልግሎት ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተለያዩ አማራጮችና ፕሮግራሞችን በመጠቀም ምላሽ እየሰጠ ይገኛል ብለዋል።

የኪ ቀበሌ በ2018 የበጀት አመት በክልሉ የመንግስት መደበኛ በጀት እቅድ ከተያዙት ሶስት ቀበሌዎች ውስጥ አንዷ በመሆን የመብራት አገልግሎት ተጠቃሚ እንድትሆን መደረጉን ነው የገለፁት።

በዚህም ውስጥ የቀበሌው ህብረተሰብ ጉድጓዶችን በመቆፈርና ለመስመር ዝርጋታ ዛፎችን በማፅዳት በጉልበት ከፍተኛ ድጋፍ ማድረጉን ነው የተናገሩት።

በቀበሌው ከ6 መቶ በላይ ደንበኞች የአገልግሎት ክፍያ በመፈፀም የመብራት ተጠቃሚ ሲሆኑ ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች ክፍያ እየፈፀሙ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ይደረጋሉ ብለዋል።

በማስጀመሪያው ስነ ስርአቱ ላይ በክልሉ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ባለድርሻ አካላት፣የወረዳ አመራሮች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣የሀይማኖት መሪዎችና የቀበሌው አጠቃላይ ኗራዎች ታድመዋል።

✍️ በታደለ ሙላቱ

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተሉን 👇👇👇

‎📌በፌስቡክ፦https://www.facebook.com/share/1KGkocwz6c/
‎📌በቴሌግራም፦https://t.me/+4cC0zGkM4SU4NTg0

የሸካ ዞን የ2018 የአመራር ግምገማና ምዘና መድረክ እየተካሄደ ነውየሸካ ዞን የ2018 በጀት ዓመት የአፈጻጸም ማጠቃለያ የአመራር ግምገማና ምዘና መድረክ በቴፒ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል። በ...
29/08/2026

የሸካ ዞን የ2018 የአመራር ግምገማና ምዘና መድረክ እየተካሄደ ነው

የሸካ ዞን የ2018 በጀት ዓመት የአፈጻጸም ማጠቃለያ የአመራር ግምገማና ምዘና መድረክ በቴፒ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።

በመድረኩ መክፈቻ ላይ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ የሺዋስ አለሙ፤ በበጀት ዓመቱ የመንግሥትና የፓርቲ ተልዕኮዎችን በተሻለ አቅም በማስኬድ የሕዝብን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በርካታ አበረታች ሥራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል።

አያይዘውም፣ አመራሩ በብልፅግና ፓርቲ መርሆዎችና ዕሴቶች ላይ የተመሠረተ፣ ተልዕኮውን በጥልቀት የተረዳ እና ጠንካራ ትግል ማድረግ እንደሚገባው አሳስበዋል።

​የዚህ የግምገማና ምዘና መድረክ ዋና ዓላማዎች ያሳካናቸውን ተግባራት ጥራትና ውጤታማነት በአግባቡ መገምገም፣ የውስጠ-ፓርቲ ጤንነትንና የዴሞክራሲያዊ ማዕከላዊነት መርህን በማክበር ጠንካራ የአመራር ሥርዓት መዘርጋት እንዲሁም በሂደቱ ላጋጠሙ ችግሮች ቆራጥ መፍትሔ ለመስጠት መሆኑን ገልጸዋል ።

ይህ የምዘና መድረክ የበጀት ዓመቱን አፈጻጸም በመፈተሽ ጥንካሬዎችን ለማጠናከር፣ ድክመቶችን ለማረም እና አመራሩ ለቀጣይ ተልዕኮዎች በብቃት ዝግጁ እንዲሆን ለማድረግ ወሳኝ መሆኑን አመላክተዋል ።

​የክልሉ መንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ የሺዋስ አለሙ እና የክልሉ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ጫናቸው ወንድሙ በጋራ እየመሩት በሚገኘው በዚህ መድረክ ላይ የሸካ ዞን አጠቃላይ አመራርና የወረዳ/ከተማ አስተባባሪ ኮሚቴ አባላት በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።

ይህ የግምገማና ምዘና መድረክ ለተከታታይ ሦስት ቀናት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተመላክቷል ሲል የዞኑ ኮሙኒኬሽን ዘግቧል።

በመስከረም ወር 2019 ዓ.ም በድምቀት ለሚከበረው ለሸካቾ ብሔረሰብ ዘመን መለወጫ በዓል ''ማሽቃሬ ባሮ '' የየኪ ወረዳ አስተዳደር አንድ ሚልዮን ብር ድጋፍ አደረገ ።በብሔረሰቡ ዘንድ በጉጉ...
29/08/2026

በመስከረም ወር 2019 ዓ.ም በድምቀት ለሚከበረው ለሸካቾ ብሔረሰብ ዘመን መለወጫ በዓል ''ማሽቃሬ ባሮ '' የየኪ ወረዳ አስተዳደር አንድ ሚልዮን ብር ድጋፍ አደረገ ።

በብሔረሰቡ ዘንድ በጉጉት የሚጠበቅው ''ማሽቃሬ ባሮ " ባህላዊና ታሪካዊ ይዘቱን ጠብቀው በተሳካ ሁኔታ እንዲከበር ወረዳ አስተዳደሩ 1ሚልዮን ብር ገቢ አድርጓል ።

የሸካቾ ብሔረሰብ ዘመን መለወጫ በዓል ('ማሽቃሬ ባሮ'' ) አሮጌው ዘመን አልፎ አዲሱን ዓመት የሚቀበሉበት ታሪካዊ በዓል ነው ።

ይህ በየአመቱ ለሚከበረው የሸካቾ ብሔረሰብ ዘመን መለወጫ በዓል የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች እንዲሁም የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በተገኙበት የሚከበር ይሆናል ።

Address

Tepi

Telephone

+251984910016

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Yeki Woreda Communications posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share