23/05/2025
የኢንዱስትሪና የግብርና ምርቶች ላይ ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ እንዳይደረግ የክትትልና ቁጥጥር ስራ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ።
የኢንዱስትሪና የግብርና ምርቶች ላይ ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ እንዳይደረግ የክትትልና ቁጥጥር ስራ እየተሰራ መሆኑን የልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 04 ንግድ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አሳየ አየነው ገለፀዋል።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የምርት አቅርቦት ችግር ሳይኖር ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ እየተስተዋለ ነው ያሉት ሃላፊው የክትትልና ቁጥጥር ስራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥልና እርምጃ እንደሚወሰድም ተናግረዋል።
ህብረተሰቡ ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ ሚያደርጉ አካላትን በማጋለጥ ለወረዳው ንግድ ጽ/ቤት ጥቆማ እንዲሰጡ አቶ አሳየ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።