የማረቃ ወረዳ መንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Waka
  • የማረቃ ወረዳ መንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት

የማረቃ ወረዳ መንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ግልጽነትን ለማስፈን እና በእውነተኛ መረጃ የበለፀገ ማህበረሰብ በማፍራት ሀገራዊ አንድነትን እና የጋራ መግባባትን ለማምጣት እንሰራለን !

‎አመራሩ ፈተናዎችን በማሸነፍ፣ የፓርቲና የመንግሥት ተልዕኮዎችን በትጋት በመፈጸም የሕዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት መሥራት አለበት፦ አቶ ዳዊት ወንድሙ‎‎በዳውሮ ዞን ማረቃ ወረዳ ...
14/04/2026

‎አመራሩ ፈተናዎችን በማሸነፍ፣ የፓርቲና የመንግሥት ተልዕኮዎችን በትጋት በመፈጸም የሕዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት መሥራት አለበት፦ አቶ ዳዊት ወንድሙ

‎በዳውሮ ዞን ማረቃ ወረዳ እና ዋካ ከተማ አስተዳደር የመራጮች ምዝገባ አፈጻጸም፣ የመንግስት መደበኛና ወቅታዊ ተግባራት አፈጻጸም ላይ ያተኮረ የውይይትና ግምገማ መድረክ ተካሂዷል።

‎መድረኩን በጋራ ያስጀመሩት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ሥራና ክህሎት ቢሮ ም/ኃላፊና የሥራ ዕድል ፈጠራ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ዳዊት ወንድሙ እና የክልሉ ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ አክልሉ ለማ ናቸው።

‎በመድረኩ ዋና ትኩረት የተሰጠው የመራጮች ምዝገባ አፈጻጸም፣ የዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ ሂደት፣ መደበኛ ተግባራትና ሌሎች ወቅታዊ ጉዳዮች ሲሆኑ፣ በእነዚህ ጉዳዮች ላይ ዝርዝር ውይይትና ግምገማ ተካሂዶ ለቀጣይ ግልጽ አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል።

‎በግምገማው መሠረት የመራጮች ምዝገባ ሂደት ከታቀደው ደረጃ እንዳይደርስ ያደረጉ እንቅፋቶች ተለይተው በአጭር ጊዜ ውስጥ መፍትሔ በመስጠት ውጤታማ አፈጻጸም ማሳካት እንደሚገባ ተገልጿል። በተለይም የአመራር ቁርጠኝነት፣ አቀናጅቶ መምራት እና የጊዜ አጠቃቀም በውጤታማነት ላይ ከፍተኛ ሚና እንዳላቸው ተጠቅሰዋል።

‎እንዲሁም የዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ ሂደት ላይ ያሉ ችግሮች በግልጽ ተለይተው በቴክኖሎጂ አጠቃቀም ለማሻሻል፣ በተጨማሪም “ዲጂታል ኢትዮጵያ” ራዕይን ለማሳካት ትኩረት ተሰጥተው እንዲሠራ ተጠይቋል። ይህም ሁሉንም ዜጎች ወደ ዘመናዊ አገልግሎቶች በእኩልነት ለማድረስ ያግዛል ተብሏል።

‎በአካባቢው የሚታዩ ችግሮችን በተቀናጀ መንገድ በመፍታት እና ሕዝቡን በንቁ ተሳትፎ በማሳተፍ አደረጃጀቶችን በቀበሌ ደረጃ ማጠናከር እንደሚገባ ተገልጿል። ይህም የሥራ ቅንጅትን በማጠናከር ለቀጣይ ሀገራዊ ምርጫ ሂደት ውጤታማ አፈጻጸም ለማስመዝገብ እንደሚያግዝ ተገልጿል።

‎ከመድረኩ የተነሱ ዋና ሐሳቦች መካከል አመራሩ ፈተናዎችን በማሸነፍ፣ የፓርቲና የመንግሥት ተልዕኮዎችን በታማኝነትና በብቃት በመፈጸም እስከ ታችኛው ደረጃ ድረስ ውጤት ማምጣት እና የሕዝቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ የአመራር ዋና ኃላፊነት መሆኑ በአንክሮ ተገልጿል።

‎በተጨማሪም 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ሰላማዊ፣ ፍትሐዊ እና ዲሞክራሲያዊ እንዲሆን የሁሉም አካላት ተባብረው በኃላፊነት መሥራት እንደሚገባ በግልጽ ተጠናክሮ ተገልጿል። በመጨረሻም ሁሉም አካላት ተግባራቸውን በቅንጅት በመፈጸም ወደ ውጤት ማሻገር እንዳለባቸው አቅጣጫ ተቀምጦ መድረኩ ተጠናቀቋል።

‎ዘገባው፡ የማረቃ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ነው።

‎በJHU ስልጠና ወስደው ወደ ሥራ የሚሸጋገሩ ወጣቶች በማረቃ ወረዳ በየአካባቢያቸው በጎ ተግባራትን በተጠናከረ ሁኔታ በመፈጸም ማህበረሰቡን እያገለገሉ ይገኛሉ።‎‎በዳውሮ ዞን ማረቃ ወረዳ፣ ከ...
11/04/2026

‎በJHU ስልጠና ወስደው ወደ ሥራ የሚሸጋገሩ ወጣቶች በማረቃ ወረዳ በየአካባቢያቸው በጎ ተግባራትን በተጠናከረ ሁኔታ በመፈጸም ማህበረሰቡን እያገለገሉ ይገኛሉ።

‎በዳውሮ ዞን ማረቃ ወረዳ፣ ከJHU ግብር ሰናይ ድርጅት ስልጠና የወሰዱና ወደ ሥራ የሚሸጋገሩ ወጣቶች፣ የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ በየአካባቢያቸው ለአቅመ ደካማ ወገኖች የተለያዩ ድጋፎችን በመስጠት የማህበረሰብ አንድነትና ርህራሄ በተግባር እያሳዩ ይገኛሉ። ይህም የስልጠናው ተፅእኖ ከንግግር ወደ ተግባር መተላለፉን በግልጽ ያሳያል።

‎በገንዶ ባቾ ማዘጋጃ ማዕከል ያሉ እነዚህ ወጣቶች፣ ለአንዲት አቅመ ደካማ እናት 33 ቅጠል ቆርቆሮ ቤት በመገንባት በተጨማሪም፣ ከሙሉ የቤት ቁሳቁስና አልባሳት ጋር በማስረከብ የተሟላ ድጋፍ አድርገዋል። በቦታውም የማዘጋጃ ቤቱ ሥራ አስኪያጅና የበጎ አድራጊ ወጣቶች ተወካዮች በመገኘት ቁልፉንና ቁሳቁሶቹን በአንድነት አስረክበዋል። ይህ ተግባር ለእናቱ የተሻለ የኑሮ ሁኔታ ለመፍጠር ከፍተኛ ድጋፍ ሲሆን፣ የወጣቶችን አንድነትና ማህበራዊ ኃላፊነት የሚያሳይ ግልጽ ምሳሌ ነው።

‎በተመሳሳይ ሁኔታ፣ በባላ ዮዮ ቀበሌ ያሉ ከJHU ስልጠና የወሰዱና ወደ ሥራ የሚሸጋገሩ ወጣቶችም ለሦስት አቅመ ደካማ እናቶች የትንሳኤ በዓልን በደስታ እንዲያከብሩ የገንዘብ ድጋፍ አድርገዋል። የተሰበሰበው ድጋፍም በወጣቶቹ ተወካዮችና በቀበሌ አስተዳደር ኃላፊዎች በጋራ ተሰጥቶ ተጠናቋል። ይህም የማህበረሰቡን መረዳዳትና አንድነት መንፈስ በተግባር እየጠናከረ መሆኑን ያሳያል።

‎እነዚህ በJHU ስልጠና የተሳተፉ ወጣቶች ያከናወኑት በጎ ተግባራት በተለይም በበዓል ወቅት ድጋፍ ለሚፈልጉ ወገኖች ትልቅ እገዛ ሲሆኑ፣ የህብረተሰቡን አንድነት፣ መተጋገዝና ርህራሄ የሚያበረታቱ ናቸው። እንዲሁም ወጣቶቹ ይህን ዓይነቱን ተግባር በቀጣይነት ለማስፋፋት እቅድ እንዳላቸው ገልጸው፣ ቁርጠኝነታቸውን አሳይተዋል።

‎ዘገባው፡ የማረቃ ወረዳ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ነው።

የዳውሮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳዊት ገበየሁ የትንሳኤ (ፋሲካ) በዓልን ምክንያት በማድረግ በታርጫ ማረሚያ ተቋም የሚገኙ ታራሚዎችን በመጎብኘት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።...
11/04/2026

የዳውሮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳዊት ገበየሁ የትንሳኤ (ፋሲካ) በዓልን ምክንያት በማድረግ በታርጫ ማረሚያ ተቋም የሚገኙ ታራሚዎችን በመጎብኘት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ዋና አስተዳዳሪው በጉብኝታቸው ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት፤ መንግስት ታራሚዎች በማረሚያ ቤት ቆይታቸው ከጥፋታቸው ታርመው፣ በስነ-ምግባር ታንፀውና በሙያ በልፅገው እንዲወጡ በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

ታራሚዎች ያገኙትን ሰብዕና እና ሙያዊ ስልጠና በመጠቀም ወደ ህብረተሰቡ ሲቀላቀሉ አምራችና ሰላማዊ ዜጋ መሆን እንዳለባቸውም አቶ ዳዊት አሳስበዋል።

ዋና አስተዳዳሪው አክለውም፣ ታራሚዎቹ በዳውሮ ባህል አዳራሽ ግንባታ ላይ ካበረከቱት አስተዋጽኦ ባለፈ የዳውሮን ታሪክ በመፃፍ ረገድ ያሳዩትን ጥረት በማስታወስ ምስጋና አቅርበዋል።

በዓሉን አስመልክቶ ታራሚዎች ከቤተሰቦቻቸው ተለይተው መሆናቸውን እንዳይሰማቸውና በዓሉን በደስታ እንዲያሳልፉ በዞኑ መንግስት ስም ለታራሚዎቹ የበሬ ስጦታም አበርክተዋል።

ዋና አስተዳዳሪው በዕለቱ ከበዓል መርሃ-ግብሩ ጎን ለጎን በማረሚያ ተቋሙ ውስጥ የሚከናወኑ የተለያዩ የልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል።

አቶ ዳዊት በጉብኝታቸው ወቅት እንደገለጹት፤ እነዚህ የልማት ስራዎች ተቋሙ ራሱን በምግብ እንዲችል ከማገዛቸው ባለፈ፣ ታራሚዎች ወደ ማህበረሰቡ ሲመለሱ በራሳቸው ስራ ፈጥረው እንዲተዳደሩ ትልቅ መሰረት የሚጥሉ ናቸው ስሉ ገልጸዋል።

በጉብኝቱ የተደሰቱት ታራሚዎች በሰጡት አስተያየት፤ የዞኑ ከፍተኛ አመራሮች በበዓል ቀን መጥተው መጎብኘታቸው ብቸኝነት እንዳይሰማቸውና የሞራል ጥንካሬ እንደሆናቸውም ገልጸዋል።

አስተያየት ሰጪዎቹ አክለውም፣ ተቋሙ ከቅጣት ይልቅ ለለውጥና ለትምህርት ትኩረት መስጠቱ ለነገ መልካም ህይወታቸው ተስፋ እንደሰጣቸው ተናግረዋል።

በተለይም የተበረከተላቸው የበሬ ስጦታ መንግስት ለታራሚዎች ያለውን አክብሮት የሚያሳይ መሆኑን ጠቅሰው ለተደረገላቸው ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

በመጨረሻም ለመላው ታራሚዎችና ለተቋሙ ሰራተኞች እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው በሰላም አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል ስል የዘገበው የዞኑ ኮሙኒኬሽን ነው።

‎የማረቃ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አክልሉ አስፋው ለትንሣኤ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ‎‎የማረቃ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አክልሉ አስፋው ለመላው የክርስትና እምነት ተ...
11/04/2026

‎የማረቃ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አክልሉ አስፋው ለትንሣኤ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

‎የማረቃ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አክልሉ አስፋው ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች “እንኳን ለጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የትንሣኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን” በማለት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

‎ዋና አስተዳዳሪው በመልዕክታቸው፣ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰውን ለማዳን ከሰማይ ወደ ምድር መጥቶ መስቀልን በመሸከም መሞቱና በሦስተኛው ቀን ከሙታን መነሳቱ ለሰው ልጆች የሕይወት፣ የተስፋና የድኅነት ታላቅ መልእክት መሆኑን ገልጸዋል። ትንሣኤ የፍቅር፣ የሰላም፣ የአንድነትና የመተሳሰብ እሴቶችን የሚያጠናክር ከፍተኛ መንፈሳዊና ማህበራዊ ዋጋ ያለው በዓል መሆኑን አመልክተዋል።

‎በዓሉ የመጋራት ባህላችንንና የወንድማማችነት ፍቅርን የሚያጠናክር መሆኑን ጠቅሰው፣ በዓሉን ስናከብር በተለይ አቅመ ደካሞችን፣ ችግረኞችን፣ አረጋውያንንና ሕፃናትን በመርዳት የበዓሉን እውነተኛ ክብር ማሳየት ማሳለፍ እንደሚገባ አሳስበዋል። በዓሉ የግል ደስታ ብቻ ሳይሆን ለሌሎችም ደስታ መሆን እንዳለበት አጽንኦት ሰጥተዋል።

‎እንዲሁም በዓሉን ስናከብር የሰላምና የህብረት እሴቶችን በመጠበቅ፣ ከግጭትና ከሕገ-ወጥ ድርጊቶች በመቆጠብ ለዘላቂ ሰላም ሁሉም ዜጎች ሃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል። ይህ በዓል ከመንፈሳዊ እሴቱ ባሻገር የማህበራዊ አንድነትና የተስፋ ብርሃን የያዘ መሆኑን ገልጸዋል።

‎በተጨማሪም፣ ዋና አስተዳዳሪው ትንሣኤ የሞት ላይ የሕይወት ድል የያዘ መሆኑን በመጥቀስ፣ ይህ የድል መንፈስ በቀጣይ በሀገራችን በሚካሄደው ምርጫ ሂደት ውስጥም ሊንጸባረቅ እንደሚገባ ገልጸዋል። ምርጫ ማለት ሕዝብ የራሱን መሪ በሰላማዊ መንገድ የሚመርጥበትና ፍላጎቱን የሚገልጽበት ዴሞክራሲያዊ ሂደት መሆኑን ጠቅሰው፣ እንደ ትንሣኤ ሁሉ ምርጫም ተስፋን፣ አዲስ መነሻንና ለተሻለ ነገ ዕድል እንደሚሰጥ አመልክተዋል።

‎በዚህ መሠረት፣ በምርጫ ወቅት ፍቅርን፣ መተሳሰብን፣ አንድነትንና ሰላምን ማዕከል ማድረግ፣ ከጥላቻና ከግጭት መራቅ፣ እንዲሁም ሕገ-ወጥ ድርጊቶችን መከላከል የእያንዳንዱ ዜጋ ሃላፊነት መሆኑን አሳስበዋል።

‎በመጨረሻም፣ የትንሣኤ በዓል ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም፣ ፍቅርና አንድነት እንዲሆን፣ ለሕዝቡም ደስታ፣ ጤናና በረከት እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል። ምርጫውም ለዘላቂ ሰላምና ለበለጠ እድገት በር የሚከፍት እንዲሆን ሁላችንም በትንሣኤው መንፈስ ተመስጠን ሃላፊነታችንን እንድንወጣ ጥሪ አቅርበዋል።

‎እንኳን አደረሳችሁ አደረሰን!

‎ዘገባው፡ የማረቃ ወረዳ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ነው።

የዳውሮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳዊት ገበየሁ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች የትንሳኤ በዓል ምክንያት በማድረግ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።ዋና አስተዳዳሪው ለመላው የ...
11/04/2026

የዳውሮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳዊት ገበየሁ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች የትንሳኤ በዓል ምክንያት በማድረግ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ዋና አስተዳዳሪው ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ብለዋል።

በዓሉ ከጨለማ ወደ ብርሃን፣ ከሞት ወደ ሕይወት መሸጋገርን ስለሚያመለክት፣ አሁን ዓለምን ያጋጠማትን ፈተና በጋራ ለመሻገር ተስፋ እንዲሰንቅ ያደርጋልም ብለዋል።

ፋሲካ በዓል ከመንፈሳዊ ይዘቱ ባለፈ፣ ቤተሰብና ዘመድ አዝማድ የሚገናኙበት፣ የተጣሉ የሚታረቁበትና የተቸገሩ የሚረዱበት ዕለት ነው ህዝቡ በአቅሙ ያለውን ለሌለው በማካፈል፣ የታመሙትን በመጠየቅና በጋራ ማዕድ በመጋራት ማህበራዊ አንድነቱን ያጠናከር እንዳለበትም ጠቁመዋል።

በዓሉ የሰላም፣ የፍቅርና የአንድነት እንዲሆን ተመኝተው፤ በዞኑ የተጀመሩ የልማት ስራዎች እንዲሳኩ ሁሉም የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያደርግ ጥሪም አቅርበዋል።

ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ ለትንሳኤ በዓል መልዕክት አስተላለፉየደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ፣ የክርስትና እምነት ተከ...
11/04/2026

ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ ለትንሳኤ በዓል መልዕክት አስተላለፉ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ፣ የክርስትና እምነት ተከታዮች የሚያከብሩትን የትንሳኤ በዓል አስመልክተው ባስተላለፉት መልዕክት፤ በስቅለት መታሰቢያ ዕለት የታየው መሥዋዕትነትና ጽናት ለሀገራዊና ክልላዊ የብልጽግና ጉዞ እንደ ትልቅ የሥራ መመሪያ ሊወሰድ ይገባል ብለዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ በመልዕክታቸው፣ የስቅለት ዕለት የፍቅር፣ የመሥዋዕትነት እና የሰው ልጅ ክብር በላቀ ደረጃ የተገለጠበት መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህም ለዘመኑ ትውልድ ከፍ ያለ መንፈሳዊና ማኅበራዊ ፋይዳ እንዳለው ገልጸዋል። በተለይም ጽኑ ዓላማን አንግቦ እስከ መጨረሻው ድረስ በታማኝነት መጓዝ የሚለውን አስተምሮ፣ አሁን ላይ ክልሉ ለጀመራቸው ሁለንተናዊ የልማት ሥራዎች እንደ ግብዓት ሊጠቀሙበት እንደሚገባ አመልክተዋል።

መሥዋዕትነት በጽናት እና በታማኝነት እስከ መጨረሻ ድረስ ሊፈጸም እንደሚችል ከዕለቱ እንማራለን ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ በስቅለቱ የታየው ጽኑ ዓላማ፣ ትጋትና ትዕግስት ለእያንዳንዱ ዜጋ የሕይወት መመሪያ ሊሆን የሚችል ድንቅ ምሳሌ መሆኑን አስረድተዋል።

ዶ/ር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ አክለውም፣ ክልሉ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ እያስመዘገባቸው ያሉ ስኬቶችን ለማስቀጠል የሕዝቦች አንድነትና የሰላም መጠበቅ ወሳኝ መሆኑን አጽንዖት ሰጥተዋል። በማንኛውም ፈተና ውስጥ በጽኑ ዓላማ መቆየት ጠቃሚ መሆኑን ያስገነዘቡት ርዕሰ መስተዳድሩ፣ ሕዝቡ በልማት ሥራዎች ላይ ያለውን ተሳትፎ በማጠናከር የአካባቢውን ዕድገት እንዲያፋጥን ጥሪ አቅርበዋል።

ክልላችንም ሆነ ሀገራችን ከፊት የሚጠብቃቸውን ግዙፍ የብልጽግና ትልሞች ለማሳካት፦ጽኑ ዓላማ፣የማይነጥፍ ትጋት እና የጋራ ኃላፊነት ከሁሉም ዜጋ እንደሚጠበቅም መልዕክት አስተላልፈዋል።

በመጨረሻም፣ በዓሉ የፍቅር፣ የሰላም እና የበረከት እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን እየገለጹ፤ በበዓል ወቅት የሚታየው የመረዳዳትና የአብሮነት እሴት ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

‎የማረቃ ወረዳ የፀጥታ ምክር ቤት የስቅለትና ትንሳኤ በዓል በሰላም እንዲከበር የውይይት መድረክ አካሂደዋል።‎በዳውሮ ዞን‎ የማረቃ ወረዳ የፀጥታ ምክር ቤት በቀጣይ ቀናት የሚከበረውን የኢየሱ...
09/04/2026

‎የማረቃ ወረዳ የፀጥታ ምክር ቤት የስቅለትና ትንሳኤ በዓል በሰላም እንዲከበር የውይይት መድረክ አካሂደዋል።

በዳውሮ ዞን‎ የማረቃ ወረዳ የፀጥታ ምክር ቤት በቀጣይ ቀናት የሚከበረውን የኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለትና ትንሳኤ በዓል በሰላም እና ያለ ማንኛውም የፀጥታ ስጋት እንዲከበር ቅድመ ዝግጅቶችና አስፈላጊ ጉዳዮች ላይ የውይይት መድረክ አካሂደዋል።

‎በህዝበ ክርስቲያን ዘንድ በታላቅ ክብርና ድምቀት የሚከበረው ይህ መንፈሳዊ በዓል በሰላም እንዲያልፍ በቂ ቅድመ ዝግጅት መደረጉን እና የወንጀል መከላከል ሥራ በተጠናከረ መልኩ መካሄዱ በውይይቱ ተገልጿል።

‎የማረቃ ወረዳ ዋና አስተዳደሪ አቶ አክልሉ አስፋው እንደገለፁት፣ በዓሉ በሰላም እንዲከበር ሁሉም ባለድርሻ አካላት በተባበረ እና በትጋት መስራት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል፤ በተለይም ለፀጥታ ኃይሎች ያላቸው ሚና ከፍተኛ መሆኑን አስታውቀዋል።

‎በበዓል ወቅት ከሌሎች አካባቢዎች የሚመጡ ሰዎች ቁጥር ሊጨምር ስለሚችል፣ እንዲሁም የሐሰተኛ ብር ኖቶች ሊዘዋወሩ ስለሚችሉ፣ ህብረተሰቡ በግብይት ጊዜ ጥንቃቄ እንዲያደርግ ተጠይቋል። ከዚህ በተጨማሪም የሃይማኖት ተቋማት በመቻቻል፣ በፍቅር እና በመከባበር በዓሉን እንዲያከብሩ ጥሪ ቀርቧል።

‎የማረቃ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ ረ/ኢንስፔክተር ዘላለም ማሞ በበኩላቸው፣ በወረዳው ውስጥ ያሉ የስጋት ቦታዎች ተለይተው ቅድመ የወንጀል መከላከል ሥራ በተጠናክረ ሁነታ እየተሰራ መቆየቱን ገልጸዋል። እንዲሁም ፖሊስ አባላት ከህብረተሰቡ ጋር በቅርብ ትብብር እንዲሰሩ እና የፀጥታ ግንዛቤን እንዲያጠናክሩ መመከሩንም ተናግረዋል።

‎በመጨረሻም ህብረተሰቡ ማንኛውንም የሚጠረጠር እንቅስቃሴ በፍጥነት ለፖሊስ ማሳወቅ እንዳለበት በግልፅ ተገልጿል፤ ይህም የስቅለትና ትንሳኤ በዓል በሰላም እንዲከበር ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው ተጠቅሟል።

ዘገባው፡ የማረቃ ወረዳ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ነው።

‎በማረቃ ወረዳ የ50ኛ ዓመት የሴቶች ቀን (March 8) በድምቀት ተከበረ‎‎“የሴቶች ድምፅ ለእኩልነትና ለበለጸገች ኢትዮጵያ” በሚል መሪ ቃል፡ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ115ኛ፡ በሀገራችን ለ...
07/04/2026

‎በማረቃ ወረዳ የ50ኛ ዓመት የሴቶች ቀን (March 8) በድምቀት ተከበረ

‎“የሴቶች ድምፅ ለእኩልነትና ለበለጸገች ኢትዮጵያ” በሚል መሪ ቃል፡ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ115ኛ፡ በሀገራችን ለ50ኛ ጊዜ የሚከበረው ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን (March 8) በዳውሮ ዞን ማረቃ ወረዳ በዛሬው ዕለት በድምቀት ተከብሯል።

‎በዓሉ በተለያዩ ዝግጅቶች የተከበረ ሲሆን፣ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የሴቶች፣ ሕጻናት፡ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች እንዲሁም ሌሎች የሥራ ባለድርሻ አካላት በመገኘት አክብረዋል።

‎በመድረኩ ላይ በመገኘት የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የማረቃ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊና የመንግሥት ረዳት ተጠሪ ወ/ሮ መሰለች ባሳ እንዳሉት፣ ሴቶች ከ“አትችልም” ከሚለው ከቀድሞ አስተሳሰብ ተላቀው ዛሬ “እችላለሁ” በማለት እስከ ሀገር መምራት ደረጃ ደርሰዋል። በሀገራችን የሴቶች መብትና እኩልነት እየተረጋገጠ መምጣቱን አስታውሰው፣ ይህን ሂደት በማጠናከር በሁሉም ዘርፎች የሴቶች ተሳትፎ እንዲጨምር ጥሪ አቅርበዋል። በተለይም በሚቀጥለው ሀገራዊ ምርጫ ሴቶች በንቃት እንዲሳተፉ አሳስበዋል።

‎የማረቃ ወረዳ የሴቶች፣ ሕጻናት፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ጽሕፈት ቤት ዋና ኃላፊ ወ/ሮ በላይነሽ ተፈራ በበኩላቸው እንደገለጹት፣ የሴቶች ተሳትፎ ሀገርን ለመገንባት ያለው ሚና ከፍተኛ ነው። በወረዳችንም ሴቶች በኢኮኖሚ፣ በማህበራዊ እንዲሁም በፖለቲካዊ ዘርፎች ትልቅ አስተዋጽኦ እያደረጉ የሚታይ ለውጥ እያመጡ መሆኑን ጠቁመው፣ ይህን ተሳትፎ ማጠናከር እንደሚገባ አሳስበዋል።

‎በተጨማሪም የጽሕፈት ቤቱ ምክትል ኃላፊ ወ/ሪት አስራት አስፋው “በኢትዮጵያ የሴቶች የ50 ዓመታት የለውጥ ጉዞና የመጋቢት 8 ታሪካዊ ፋይዳ” በሚል ርዕስ የተዘጋጀውን የውይይት ሰነድ በንባብ አቅርበዋል። በሰነዱም ሴቶች ከአገልጋይነት ወደ ባለቤትነት እየተሸጋገሩ መሆናቸውን እንዲሁም በሀገር አቀፍ ደረጃ እያበረከቱ ያሉትን አስተዋጽኦ አብራርተዋል።

‎በመጨረሻም፣ በቀረበው ሰነድ ዙሪያ ከተሳታፊዎች ጥያቄዎችና አስተያየቶች ተንሥተው በቂ ውይይት ተደርጎ፣ ምላሽ ተሰጥቶ መድረኩ ተጠናቋል።

‎“የሴቶች ድምፅ ለእኩልነትና ለበለጸገች ኢትዮጵያ!”

‎ዘገባው፡ የማረቃ ወረዳ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ነው።

‎በማረቃ ወረዳ የማህበረሰብ አቀፍ የወንጀል መከላከልና ፓትሮል ቅኝት አባላት ምረቃ ለ8ኛ ዙር በባቶ ቃልቦ ቀበሌ ተካሄደ‎‎በዳውሮ ዞን ማረቃ ወረዳ በተጠናከረ ሁነታ እየተካሄደ ያለው የማህበ...
06/04/2026

‎በማረቃ ወረዳ የማህበረሰብ አቀፍ የወንጀል መከላከልና ፓትሮል ቅኝት አባላት ምረቃ ለ8ኛ ዙር በባቶ ቃልቦ ቀበሌ ተካሄደ

‎በዳውሮ ዞን ማረቃ ወረዳ በተጠናከረ ሁነታ እየተካሄደ ያለው የማህበረሰብ አቀፍ የወንጀል መከላከልና የፓትሮል ቅኝት አባላት ምረቃ እንዲሁም የነጭ ስንደቃለማ ማውለብለብ ሥነ ሥርዓት ለስምንተኛ ዙሩ ዛሬ በባቶ ቃልቦ ቀበሌ በደማቅ ሁኔታ ተካሂዷል።

‎በዚህ መድረክ ላይ የተገኙት የማረቃ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ ረ/ኢንስፔክተር ዘላለም ማሞ ንግግራቸው፣ ሰላም አንድ ማህበረሰብ ሊያድግ፣ ኢኮኖሚ ሊበለጽግ እና ትውልድ ሊጠበቅ የሚገባው መሠረታዊ ሁኔታ መሆኑን ጠቁመዋል። አድስ የተመረቁ አባላትም ሕግን በማክበር ማህበረሰቡን ከወንጀል ጥቃት ለማዳን ቆራጥነት እንዲኖራቸው አሳስበዋል።

‎በመቀጠልም የማረቃ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት ማ/አ/ወ/መ/ ማስተባበሪያ ኃላፊ ም/ኢ/ር አጥናፉ አባቴ በበኩላቸው፣ ወንጀል በማህበረሰቡ ላይ የሚያደርሰው ጉዳት ከፍተኛ ነው፤ በንብረትም ሆነ በሰው ሕይወት ላይ የማይመለስ ኪሳራ ያስከትላል። የማህበረሰብ አቀፍ ፓትሮል ቅኝት ደግሞ ወንጀል ከመከሰቱ በፊት ለመከላከል እና ህገወጦችን ለማጋለጥ ጠቃሚ መሳሪያ ነው። ስለዚህ አባላቱ የተሰጣቸውን ሃላፊነት በታማኝነት እንዲወጡ አሳስበዋል።

‎በመጨረሻም የነጭ ስንደቃለማ ማውለብለብ ሥነ ሥርዓት ተፈጽሞ፣ የተመረቁት አባላት ማህበረሰቡን በቅንነት ለማገልገል ቃል መዓላ ፈጽመዋል። ይህ ሥነ ሥርዓት በወረዳው የሰላም እና የፀጥታ ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የሚያሳይ ማሳያ መሆኑን አስረድተዋል።

‎ዘገባው፡ የማረቃ ወረዳ መንግሥት ኮሙኒኬሽን ነው።

‎በማረቃ ወረዳ ከ1203 በላይ ወጣቶች በJHU/CCP ስልጠና ወስደው ወደ ሥራ ሽግግር ለመግባት ተዘጋጁ‎‎በዳውሮ ዞን ማረቃ ወረዳ ከ26/7/2018 ዓ.ም እስከ 28/7/2018 ዓ.ም ድረስ ...
06/04/2026

‎በማረቃ ወረዳ ከ1203 በላይ ወጣቶች በJHU/CCP ስልጠና ወስደው ወደ ሥራ ሽግግር ለመግባት ተዘጋጁ

‎በዳውሮ ዞን ማረቃ ወረዳ ከ26/7/2018 ዓ.ም እስከ 28/7/2018 ዓ.ም ድረስ ለሶስት ቀናት ለስራ ፈላጊ ወጣቶች እየተሰጠ የቆየው በJHU/CCP የተዘጋጀ ስልጠና በዛሬው ዕለት በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል።

‎በዚህም ስልጠና 535 ወጣቶች የመጀመሪያ ዙር የማህበረሰብ አገልግሎት (Free Community Service) ስልጠና እንዲሁም 668 ወጣቶች Pose & Reflection ስልጠና ተሳትፈው በአጠቃላይ 1203 ሥራ ፈላጊ ወጣቶች ተጠቃሚ ሆነዋል።

‎በተጨማሪም ቀደም ብለው በማህበረሰብ አገልግሎት የተሳተፉ ከአምስቱ ቀበሌዎች (ባላ ዮዮ፣ ማይዲ ኢየሱስ፣ ማዳ ኩይሊ፣ ያማላ ሜሶና እና ያማላ ጋራ) የተወጣጡ ወጣቶች የAgro-Business ስልጠና በመውሰድ ለማህበረሰቡ ያከናወኑትን ስራ በመግለፅ የመጨረሻ ዙር ስልጠናቸውን በዛሬው ዕለት ወስደዋል።

‎ስልጠናው ዋና ዓላማ ወጣቶችን በመጀመሪያ በማህበረሰብ አገልግሎት ማሳተፍ፣ ከዚያም በAgro-Business ክህሎት ስልጠና በመስጠት ወደ ራስ-ስራ እንዲገቡ ለማበረታታት ነው። ተሳታፊዎቹም በግና ፍየል ማሙከት፣ ዶሮ እና ንብ ማርባት ያሉ የግብርና ዘርፎችን በመምረጥ በብድር ድጋፍ በመታገዝ ወደ ተግባራዊ ሥራ መግባት እንደምችሉ ተገልፀዋል።

‎የማረቃ ወረዳ ስራና ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ታረቀኝ ተፈራ በቦታው ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት፣ ወጣቶች ያገኙትን ክህሎት በተግባር በመዋል ራሳቸውን እና ማህበረሰቡን እንዲጠቅሙ ምክርና ሀሳብ ሰጥተዋል።

‎በአጠቃላይ ይህ ስልጠና የወጣቶችን ክህሎት በማጠናከር ወደ ራስ-ስራ መግባትን ለማበረታታት እና ኢኮኖሚያዊ ተሳትፎአቸውን ለማሻሻል ከፍተኛ ሚና እንዳለው ተገልጿል።

‎ዘገባው፡ የማረቃ ወረዳ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ነው።

Address

B52
Waka
SWEPR,DAWUROZONEMAREKAWEREDA

Telephone

+251976984842

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የማረቃ ወረዳ መንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to የማረቃ ወረዳ መንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት:

Shortcuts

Share