Gurage Zone Revenue Department

Gurage Zone Revenue Department Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Gurage Zone Revenue Department, Government Organization, Welkite, Welk'it'e.

የክልሉ ገቢዎች ቢሮ በጉራጌ ዞን የገቢ አሰባሰብ ስራዎች ድጋፍና ክትትል እያደረገ ይገኛል።(ነሀሴ 27/2018) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ ምክትል ቢሮ ሀላፊ አቶ ተስፋዬ አሰፋ ...
02/09/2026

የክልሉ ገቢዎች ቢሮ በጉራጌ ዞን የገቢ አሰባሰብ ስራዎች ድጋፍና ክትትል እያደረገ ይገኛል።

(ነሀሴ 27/2018) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ ምክትል ቢሮ ሀላፊ አቶ ተስፋዬ አሰፋ በጉራጌ ዞን አበሽጌ ወረዳ የገቢ አፈጻጸም ስራዎችና የቀጣይ ገቢ አሰባሰብ ላይ የድጋፍና ክትትል ሥራ አካሂዷል።

በዞኑ በሁሉም መዋቅር የበጀት ዓመቱን የገቢ ዕቅድ እስከ ጳጉሜ 03/2018 ድረስ 18.4 በመቶ ለማድረስ በተያዘው ዕቅድ መሰረት በዛሬው ዕለትም የገቢ አሰባሰብ ስራዎችን ከዞኑ ገቢዎች መምሪያ እና ከአበሽጌ የገቢ ማኔጅመንት ጋር በመሆን የአፈጻጸም ሂደትን በጥልቀት ገምግመዋል።

ምክትል ቢሮ ሀላፊ አቶ ተስፋዬ አሰፋ እንደገለጹት የተቀመጠው የገቢ ግብ እንዲሳካ በተቋሙ የተቀመጡ የገቢ አሰባሰብ የአሰራር ስርአቶች በመከተል መስራት ይገባል ብለዋል።በዚህ መሰረት የደረሰኝ ቁጥጥር ስርዓትን ማጠናከር፣ የኦዲት ግኝት ገቢዎችን መሰብሰብ፣ የማዘጋጃ ቤት የበረትና የመደብ ገቢ አሰባሰብን በማሳደግ የተያዘው እቅድ ለማሳካት ርብርብ እንዲደረግ አሳስበዋል።

የገቢ አማራጮችን በመፈለግ የተሻለ ገቢ በመሰብሰብ የኢኮኖሚ አቅም ለማጎልበት በቅንጅትና በትጋት መስራት እንደሚገባ ገልጸዋል።

የጉራጌ ዞን ገቢዎች መምሪያ ሀላፊ አቶ ሚነወር ሀያቱ በበኩላቸው በሁሉም ዘርፍ ገቢን አሟጦ መሰብሰብ ለህብረተሰቡ መልካም አስተዳደር ጥያቄዎች መመለስና የአመቱን ዕቅድ ለማሳካት መስራት እንደሚገባ ጠቅሰው ትኩረት ይሻሉ ባልዋቸው የሮያሊቲ ገቢ አሰባሰብ፤የጫት ቀርጥ ስራን፤የግል ድርጅቶች የደሞዝ ስራ ግብርና የተጨማሪ እሴት ታክስ ገቢ እንዲጠናከር ብለዋል።

በውይይቱ የአበሽጌ ወረዳ ገቢ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ፋንታሁን የወረዳው ፖቴንሽያ አሟጠን ገቢ በመሰብሰብ የወረዳችን ልማት እንዲውል እንሰራለን ብለዋል።

የታክስ አለመግባባትን በመስማማት ስለመፍታትነሐሴ 27/2018 ዓ.ም (የገቢዎች ሚኒስቴር) በተሻሻለው የፌዴራል ታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1434/2018 አንቀጽ 61 የታክሱ ባለስልጣን የ...
02/09/2026

የታክስ አለመግባባትን በመስማማት ስለመፍታት

ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም (የገቢዎች ሚኒስቴር)

በተሻሻለው የፌዴራል ታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1434/2018 አንቀጽ 61 የታክሱ ባለስልጣን የታክስ አለመግባባትን በመስማማት ለመፍታት ያለውን ስልጣን በተመለከተ የሚከተለውን ይላል፡-

👉 የታክሱ ባልስልጣን የታክስ አለመግባባቶችን በመስማማት የመፍታት ስልጣን ተሰጥቶታል።
👉 ማናቸውም በስምምነት የሚፈታ የታክስ ያለመግባባት በጽሁፍ የሚደረግ እና የተስማሚ ወገኖች ፊርማ ያረፈበት ሊሆን ይገባል።
👉 የታክስ አለመግባባቶችን በመስማማት የመፍታት ስልጣን የሰጠው ድንጋጌ ቢኖርም የሚከተሉት ሁኔታዎች ሲኖሩ ጉዳዩ በማስማማት ሊታይ አይችልም፦
1. የታክስ ማጭበርበር ወይም ሆን ተብሎ የተደረገ ታክስን የመሰወር ድርጊት መኖሩ ወይም ሌላ ከታክስ ጋር የተገናኘ ወንጀል መኖሩ ሲጠረጠር፤
2. በማስማማት የሚደረግ ስምምነት ከኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ-መንግሥት እና ከሚመለከታቸው የታክስ ሕጎች ጋር የሚጋጭ ሲሆን፤
3. ከሁለቱ ወገኖች አንዱ በሽምግልና ሂደት ውስጥ ለመሳተፍ ፈቃደኛ ካልሆነ።
👉 ሚኒስቴሩ የአስማሚውን የትምህርት እና ሙያ ደረጃን ጨምሮ የመስማማት ሂደት የሚመራበትን ሥርዓት የሚወስን ዝርዝር የአፈፃፀም መመሪያ ያወጣል፡፡

ከወልቂጤ ከተማ የእህል ንግድ ስራ ከሚሰሩ የደረጃ"ለ"ግብር ከፋዮች ጋር ውይይት ተደረገ!!!ነሀሴ 26/2018 የጉራጌ ዞን ገቢዎች መምሪያ እና የወልቂጤ ከተማ ገቢዎች ጽ/ቤት በጋራ በመሆን ...
01/09/2026

ከወልቂጤ ከተማ የእህል ንግድ ስራ ከሚሰሩ የደረጃ"ለ"ግብር ከፋዮች ጋር ውይይት ተደረገ!!!

ነሀሴ 26/2018 የጉራጌ ዞን ገቢዎች መምሪያ እና የወልቂጤ ከተማ ገቢዎች ጽ/ቤት በጋራ በመሆን በከተማው በእህል ንግድ ስራ ከተሰማሩ የደረጃ"ለ"ግብር ከፋዮች ጋር ውይይት አደረጉ።

በውይይቱ እድል ወስደው ሀሳብ ያነሱ ግብር ከፋዮች በበኩላቸው ያለአግባብ የግብር ውሳኔ የተጣለባቸው መሆኑን ገልፀው ሊስተካከልላቸው እንደሚገባ አንስተዋል።
የጉራጌ ዞን ገቢዎች መምሪያ ሀላፊ አቶ ሚነወር ሀያቱ በተነሱ ሀሳቦች ላይ በሰጡት ምላሽ በማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ የ2018 የግብር ዘመን የደረጃ"ለ"ግብር ከፋዮች የገቢ ግብር አዋጅ ለማሻሻል በወጣው አዋጅ ቁጥር 39/2018 መሰረት ግብር ለማስከፈል የሚያስችል የዋጋ ግሽፕት ማስተካከያ ማስፈፀሚያ ሰነድ መነሻ በማድረግ የተወሰነላቸው መሆኑን ገልፀውላቸዋል።

በማከልም በ2015 ተደርጎ በነበረው የቀን ገቢ ግመታ አመታዊ ሽያጭ መሰረት አዋጁን ለማሻሻል በወጣው አዋጅ ቁጥር 39/2018 አንቀፅ 14 መሰረት የደረጃ ለ ግብር ከፋዮች አመታዊ ጠቅላላ ሽያጫቸው በሚወድቅበት የገቢ ማእቀፍ መሰረት ከ2 እስከ 9 በመቶ ግብር እንደተወሰነላቸው ያብራሩ ሲሆን በእህል ንግድ ዘርፍ የሚሰሩ ነጋዴዎች ቀደም ሲል በነበሩ አመታት አነስተኛ ግብር ይከፍሉ ስለነበረ በተሻሻለው የገቢ ግብር መሰረት ለተወሰነው ግብር አሰባሰብ ላይ ተፅእኖ አሳድሯል ብለዋል። አሁን በተደረሰበት በአጠቃላይ የታክስ ውሳኔው ላይ በቂ ተግባቦት የተፈጠረ ስለሆነ ፈጥነው ግብራቸውን እንዲከፍሉ አሳስቧል።

የወልቂጤ ከተማ ገቢዎች ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ይድረሱ ተስፋዬ እንደገለጹት በከተማችን የታክስ አወሳሰን እና አከፋፈል በመመሪያና በአሰራሩ መሰረት በጥንቃቄ የተሰራ መሆኑን ገልፀው ዳግም የእያንዳንዱ ቅሬታ ያቀረቡ የደረጃ ለ ግብር ከፋዬች ፋይል እንዲታይ ተደርጓል ብለዋል።በማከልም አብዛኞቹ የከተማችን ግብር ከፋዮች ግብራቸውን የከፈሉ ስለሆነ ያልከፈላቹ ግብር ከፋዮች ካለአስፈላጊ ቅጣቶች እራሳቹህን እንድትጠብቁና ከወዲሁ ግብራቹ እንድትከፍሉ በማለት አሳስበዋል።

በመጨረሻም አብዛኞቹ ግብር ከፋዮች በተደረገው ውይይት ከታክስ አወሳሰኑ ጋር የነበረባቸው ብዥታ የጠራላቸው መሆኑና የግብር ውሳኔው ይበልጥ ግልፅ የሆነላቸው መሆኑን በመግለፅ ግዴታቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል።በመድረኩ የቀበሌ ጽ/ቤት ገቢ ሀላፊዎችም ተገኝተው የየጽ/ቤታቸው ግብር አከፋፈል ማብራሪያ ሰጥተዋል።

በወልቂጤ ከተማ ለደረጃ “ሀ” ግብር ከፋዮች የክህሎት ስልጠና ተሰጠ(ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም) የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ጽ/ቤት በወልቂጤ ዪንቨርስቲ  የተጨማሪ እሴት ታክስ የተመዘገ...
01/09/2026

በወልቂጤ ከተማ ለደረጃ “ሀ” ግብር ከፋዮች የክህሎት ስልጠና ተሰጠ

(ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም) የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ጽ/ቤት በወልቂጤ ዪንቨርስቲ የተጨማሪ እሴት ታክስ የተመዘገቡ ለአገልግሎት ሠጪ ማህበራት የክህሎትና የግንዛቤ ስልጠና ሰጠ።

በስልጠናው የሂሳብ መዝገብ አያያዝ፣ የደረሰኝ አጠቃቀም እንዲሁም የሪፖርት አደራረግ እና የመረጃ አደረጃጀት ላይ ስልጠና የተሠጠ ሲሆን ማህበራቶቹ ም ለተጨማሪ እሴት ታክስ ደረሠኝ አጠቃቀም አዲስ እንደመሆናቸው ያነሷቸው ቴክኒካል ጥያቄዎች እና ተያያዥ ጉዳዮችን አንስተዋል።

በባለሙያዎችና በአመራሮች ማብራሪያ በመሰጠቱ የስልጠና መድረኩ ተጠናቀቀ።

01/09/2026
በወልቂጤ ከተማ ለደረጃ “ሀ” ግብር ከፋዮች የክህሎት ስልጠና ተሰጠ(ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም) የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ጽ/ቤት ለደረጃ “ሀ” ግብር ከፋዮች የክህሎትና የግንዛቤ ስል...
01/09/2026

በወልቂጤ ከተማ ለደረጃ “ሀ” ግብር ከፋዮች የክህሎት ስልጠና ተሰጠ

(ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም) የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ጽ/ቤት ለደረጃ “ሀ” ግብር ከፋዮች የክህሎትና የግንዛቤ ስልጠና ሰጠ።

በስልጠናው የሂሳብ መዝገብ አያያዝ፣ የደረሰኝ አጠቃቀም፣ በተሻሻለው የገቢ ግብር አዋጅ ቁጥር 1395 ላይ የተደረጉ ማሻሻያዎች፣ የVAT ደረሰኝ አቆራረጥ እና ደረሰኝ ካለመስጠት ጋር ተያይዘው ስለሚወሰዱ አስተዳደራዊ ቅጣቶች ገለጻ ተደርጓል።

ግብር ከፋዮችም የQR ኮድ ደረሰኝ ህትመት መዘግየት፣ በግዢ ወቅት የአ.አ ደረሰኝ አለማግኘትን ጨምሮ ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮችን አንስተዋል።

በባለሙያዎችና በአመራሮች ማብራሪያ በመሰጠቱ የስልጠና መድረኩ ተጠናቋል።

የጉራጌ ዞን ምክር ቤት በ4ኛ ዙር 13ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 31ኛ መደበኛ ጉባኤው ለ2019 በጀት ዓመት ከ10 ቢሊየን 788 ሚሊየን 612 ሺ በላይ ብር በጀት ረቂቅ አዋጅ አጽድቋል።
28/08/2026

የጉራጌ ዞን ምክር ቤት በ4ኛ ዙር 13ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 31ኛ መደበኛ ጉባኤው ለ2019 በጀት ዓመት ከ10 ቢሊየን 788 ሚሊየን 612 ሺ በላይ ብር በጀት ረቂቅ አዋጅ አጽድቋል።

«ሲሸጡ ደረሰኝ ይስጡ፣ ሲገዙ ደረሰኝ ይቀበሉ!» የሚለው መልዕክት የወቅታዊ ግብይት መመርያ ብቻ ሳይሆን ህጋዊና ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ያለው አሰራር ነው።ለገዢው:- የገዙት እቃ ህጋዊ ባለቤት መሆ...
28/08/2026

«ሲሸጡ ደረሰኝ ይስጡ፣ ሲገዙ ደረሰኝ ይቀበሉ!» የሚለው መልዕክት የወቅታዊ ግብይት መመርያ ብቻ ሳይሆን ህጋዊና ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ያለው አሰራር ነው።

ለገዢው:- የገዙት እቃ ህጋዊ ባለቤት መሆንዎን ያረጋግጣል፤ እቃው ቢበላሽ ወይም ጉድለት ቢኖረው ለመቀየርና ዋስትና ለመጠየቅ ማስረጃ ይሆናል።

ለሻጩ:- ትክክለኛና ህጋዊ ነጋዴ መሆንዎን ያሳያል፤ በሂሳብ አያያዝ ወቅት ከታክስ አካላት ጋር የሚኖርን ግንኙነት ጤናማነት ያደርጋል።

ለሀገር:- ተገቢው ግብር ለሀገር ገቢ እንዲሆን በማድረግ የልማት ስራዎችን ያፋጥናል።

ህጋዊ አሰራርን በመከተል ደረሰኝ ቀመስጠትና በመቀበል ራሳችንንም ሆነ ሀገራችንን እንጠብቅ!

Address

Welkite
Welk'it'e

Telephone

+251113302254

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gurage Zone Revenue Department posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share