12/08/2026
የስልጤ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ዋና ሀላፊ አቶ ሙበራ ከማል በአልቾ ውሪሮ ወረዳ የገጠር ኮሪደር የክላስተር ፍራፍሬ ልማትን በይፋ አስጀመሩ
ቃዋቆቶ ነሀሴ 6/2018 {አልቾ ኮሙኒኬሽን}
የስልጤ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ዋና ሀላፊ አቶ ሙበራ ከማል ከመምሪያው ምክትል ሀላፊዎችና ከአልቾ ውሪሮ ወረዳ ከፍተኛ አመራሮች በጋራ በመሆን በወረዳው የገጠር ኮሪደር የክላስተር ፍራፍሬ ልማትን በወሻኖ እና ቀረሶ ቀበሌ በይፋ አስጀምረዋል።
በማስጀመሪያው መረሀ-ግብር የስልጤ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የግብና መምሪያ ዋና ሀላፊ አቶ ሙበራ ከማል፣ የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ወ/ሮ መህዲያ ሀሰን የስልጤ ዞን ግብርና መምሪያ ምክትልና የእርሻ ዘርፍ ሀላፊ አቶ ሳዲቅ አህመዲን የቡናና ቅመማ-ቅመም ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ቶፊቅ ኑሪ እንዲሁም የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ሙዘይን መሀመድ ምክትል አስተዳዳሪ እና የግብርና ጽ/ቤት ዋና ሃላፊ አቶ ሱልጣን በርጋ ረዳት የመንግስት ተጠሪ አቶ ሙባረክ አሊ እንዲሁም ሌሎች የወረዳ አመራሮች እና የአከባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል።