Worabe Comprehensive Specialized Hospital ወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ እስፔሻላይዝድ ሆስፒታል

  • Home
  • Worabe Comprehensive Specialized Hospital ወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ እስፔሻላይዝድ ሆስፒታል

Worabe Comprehensive Specialized Hospital ወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ እስፔሻላይዝድ ሆስፒታል health information

"ጳጉሜ 4 የህብር ቀን" በማስመልከት የኢትዮጵያ ማንሰራራት በሚል መሪ ቃል በስልጤ ዞን ወራቤ ከተማ ላይ በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ይገኛል።በማስ ስፖርት እንቅስቃሴው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ...
09/09/2026

"ጳጉሜ 4 የህብር ቀን" በማስመልከት የኢትዮጵያ ማንሰራራት በሚል መሪ ቃል በስልጤ ዞን ወራቤ ከተማ ላይ በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ይገኛል።

በማስ ስፖርት እንቅስቃሴው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ አንተነህ ፍቃዱ ፣ የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪና የሆስፒታሉ የስራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ እና የክልል እና የዞን ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣

እንዲሁም የወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ እስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ስራ አስኪያጅ ዶ/ር ካሊድ ሸረፋ፣ ሜዲካል ዳይሬክተሩ ዶ/ር ሙሂዲን ዑመር፣ የማኔጅመንት አካላት እና ባልደረቦች ተሳትፈዋል።

"ጳግሜ 4 የህብር ቀን" ምክንያት በማድረግ በወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የሚገኙ ታማሚዎችን በመጠየቅ ጉብኝት ተካሂዷል።በጉብኝቱ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተ...
09/09/2026

"ጳግሜ 4 የህብር ቀን" ምክንያት በማድረግ በወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የሚገኙ ታማሚዎችን በመጠየቅ ጉብኝት ተካሂዷል።

በጉብኝቱ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ አንተነህ ፍቃዱ ፣ የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪና የሆስፒታሉ የስራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ እና የክልል እና የዞን ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ተሳትፈዋል።

በጉብኝቱ በተለያዩ የህክምና ክፍሎች ህክምናቸውን እየተከታተሉ የሚገኙ ታካሚዎችን በመጎብኘት ስጦታዎችን አበርክተዋል።

በዚህም መራመድ ለማይችል ታካሚ የዊልቸር ድጋፍ እና ሌሎች ታካሚዎችምንም በመጠየቅ እና በማበርታት እንዲሁ የተለያዩ ድጋፎችን አድርገዋል።

ጎብኚዎቹ በሆስፒታሉ የሚገኘውን የህክምና ኦክስጂን ማምረቻ ፣ በመጠናቀቅ ላይ የሚገኘውን ባለ አራት ወለል የሀኪሞችን መኖሪያ ቤት፣ በዝግጅት ላይ የሚገኘውን የደም ባንክ እና ሌሎች ልዩ ልዩ ተግባራትን ተመልክተዋል።

የሆስፒታሉ ዋና ስራ አስኪያጅ ዶ/ር ካሊድ ሸረፋ እንግዶቹን በመቀበል አስጎብኝተዋል።

ጳጉሜ 4/2018 የሕብር ቀን “ብዝኃነት የኢትዮጵያ ጌጥ!” በሚል መሪ ቃል በደማቅ ሁኔታ እየተከበረ ይገኛል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሳይንስና ቴክኖሎጂ ቢሮ ወራቤ ኮምፕረሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ታካሚዎችን ጎበኙ።በጉብኝታቸው ተኝተው ህክምና ለሚያገኙ ታካሚዎች የተለያዩ ንፅህና መጠበቂያ ቁሳቁ...
08/09/2026

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሳይንስና ቴክኖሎጂ ቢሮ ወራቤ ኮምፕረሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ታካሚዎችን ጎበኙ።

በጉብኝታቸው ተኝተው ህክምና ለሚያገኙ ታካሚዎች የተለያዩ ንፅህና መጠበቂያ ቁሳቁሶችን ድጋፍ አድርገዋል።

አቶ ሙህዲን ሁሴን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሳይንስና ቴክኖሎጂ ቢሮ ምክትል ቢሮ ሃላፊ እንዳሉት የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት አካል የሆነውን ድጋፍ በወራቤ ኮምፕረሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በማድረጋችን እጅጉን ደስተኞች ነን ብለዋል።

ቢሮው በክልሉ በተለያዩ አካባቢዎች በርካታ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎትን ተግባራዊ በማድረግ ላይ እንደሚገኝ የገለፁት አቶ ሙህዲን በሆስፒታሉ የሚያደርጉት ድጋፍ ቀጣይነት እንደሚኖረው ተናግረዋል።

የወራቤ ኮምፕረሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ክሊኒካል ሰርቪስ ዳይሬክተር ዶ/ር ሙስጠፋ ሙሃመድ ቢሮው በሆስፒታሉ በመገኘት የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት አካል የሆነውን ድጋፍ ለታካሚዎች በማድረግ ስለጎበኟቸው ምስጋናቸውን ቸረዋል።

በጉብኝታቸውም በተኝቶ ህክምና ላይ ለሚገኙ ታካሚዎች የተለያዩ የንፅህና መጠበቂያ ቁሳቁሶችንና ለስላሳ መጠጦችን አበርክተዋል ።

በጉብኝቱ ወቅት የዋና ስራ አስኪያጅ ፅ/ቤት ሃላፊ ዶ/ር ጀማል በድሩን ጨምሮ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላትም ተገኝተዋል።

🩸 ታላቅ የደም ልገሳ ፕሮግራም‼️ ታላቅ የደም ልገሳ ፕሮግራም በወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ እስፔሻላይዝድ ሆስፒታል‼️  🩸 ደም በመለገስ በደም እጦት ለሚሰቃዩ ህጻናትና እናቶች እንድረስላቸው!🩸 የ...
08/09/2026

🩸 ታላቅ የደም ልገሳ ፕሮግራም‼️

ታላቅ የደም ልገሳ ፕሮግራም በወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ እስፔሻላይዝድ ሆስፒታል‼️

🩸 ደም በመለገስ በደም እጦት ለሚሰቃዩ ህጻናትና እናቶች እንድረስላቸው!🩸

የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት አካል የሆነው የህብር ቀን አንድ ሀገር፣ አንድ ቀን፣ አንድ ጤና /one nation, one day, one health/ በሚል መሪ ቃል ጷግሜ 4 2018 በተለያዩ መርሃ ግብሮች እንደ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በወራቤ ኮምፕረንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ይከበራል።

በእለቱ ማስ ስፖርት ፣ የጤና ምርመራና የደም ልገሳ ፕሮግራም ይካሄዳል።

በዚሁ እለት በወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ እስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በመገኘት ደም በመለገስ ህይወት ይታደጉ ዘንድ ተጋብዘዋል ።

🩸 የእርሶ አንድ ከረጢት ደም በህመም የሚሰቃዩ ህጻናት፣ እናቶች እና አደጋ ያጋጠማቸውን ወገኖች ህይወት ይታደጋል!

የወራቤ ከተማና አካባቢዋ

🩸 ወጣቶች
🩸 አመራሮች
🩸 የመንግስት ሠራተኞች
🩸 የጤና ባለሙያዎች
🩸 የፀጥታ አካላት
🩸 ተማሪዎች
🩸 አጠቃላይ ነዋሪዎች በዚህ ታላቅ ፕሮግራም በመገኘት ደም እንለግስ ህይወት እንታደግ ‼️

በዕለቱ በመገኘት ከስጦታዎች ሁሉ ልዩ ስጦታ የሆነውን ደም በመለገስ የሰው ሂወት ያድኑ!

የበጎ ምንዳም ተቋዳሽ ይሁኑ!!!

የወራቤ ሆስፒታል አይሲቲ ዳይሬክቶሬት ለብቃትና የሰው ሀይል ፣ ለፋይናንስ፣ ለንብረት አስተዳደር እና ለመሰረታዊ አገልግሎት የስራ ክፍሎች ሠራተኞች የመሰረታዊ የኮምፒዩተር ስልጠና እየሰጠ ነው...
06/09/2026

የወራቤ ሆስፒታል አይሲቲ ዳይሬክቶሬት ለብቃትና የሰው ሀይል ፣ ለፋይናንስ፣ ለንብረት አስተዳደር እና ለመሰረታዊ አገልግሎት የስራ ክፍሎች ሠራተኞች የመሰረታዊ የኮምፒዩተር ስልጠና እየሰጠ ነው።

የወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የኢንፎርሜሽንና ኮሚኒኬሽን ቴክኖሎጂ (ICT) ዳይሬክቶሬት ለሆስፒታሉ የብቃትና የሰው ሀይል፣ ለፋይናንስ፣ ለንብረት አስተዳደር እና ለመሰረታዊ አገልግሎት ክፍሎች ሠራተኞች የመሰረታዊ የኮምፒዩተር ክህሎት ስልጠና እየሰጠ ይገኛል።

ስልጠናው ሠራተኞች በየዕለት የሥራ እንቅስቃሴያቸው የዲጂታል ቴክኖሎጂን በብቃትና በተገቢው መንገድ እንዲጠቀሙ የሚያስችላቸውን መሰረታዊ የኮምፒዩተር እውቀትና ተግባራዊ ክህሎት ለማሳደግ ያለመ ነው።

በስልጠናው የኮምፒዩተር መሰረታዊ አጠቃቀም፣ የሰነድ አያያዝና አደረጃጀት፣ የመረጃ አያያዝ እና ከሠራተኞቹ የዕለት ተዕለት ሥራ ጋር የተያያዙ ሌሎች መሰረታዊ የICT ክህሎቶች ትኩረት ተሰጥቷቸዋል።

ይህ የአቅም ግንባታ ስልጠና የሠራተኞችን የዲጂታል ክህሎት በማሳደግ የሥራ ቅልጥፍናን፣ ትክክለኛነትንና ምርታማነትን ለማሻሻል ከፍተኛ አስተዋፅዖ ያበረክታል ተብሏል።

የሆስፒታሉ አይሲቲ ዳይሬክቶሬት በተለያዩ የአቅም ግንባታ ሥራዎች ሠራተኞች የዲጂታል ሥርዓቶችን በብቃት እንዲጠቀሙ በማስቻል፣ የሆስፒታሉን የዲጂታል ሽግግር ለማፋጠን የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑም የሚታወቅ ነው።

የወራቤ ሆስፒታል ጤና እግር ኳስ ቡድን የወራቤ ዩኒቨርሲቲ አቻውን በመርታት ወደ ፍፃሜ ውድድር ተሸጋገረ!በወራቤ ከተማ የበ2018 የክረምት የጤና እግር ኳስ ውድድር የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ፤ የወ...
06/09/2026

የወራቤ ሆስፒታል ጤና እግር ኳስ ቡድን የወራቤ ዩኒቨርሲቲ አቻውን በመርታት ወደ ፍፃሜ ውድድር ተሸጋገረ!

በወራቤ ከተማ የበ2018 የክረምት የጤና እግር ኳስ ውድድር የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ፤ የወራቤ ሆስፒታል እግር ኳስ ቡድን አስደናቂ የበላይነት በማሳየት የወራቤ ዩኒቨርሲቲ አቻውን 3 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል።

እሁድ ጷግሜ 1 ቀን 2018 በሀይረንዚ ትምህርት ቤት ሜዳ በተካሄደው በዚህ ወሳኝ ፍልሚያ፣ የሆስፒታሉ ቡድን ከተፎካካሪው በላይ ጠንካራ የሜዳ ላይ እንቅስቃሴ በማድረግ የበላይነት ማሳየት ችሏል። በጨዋታው ልዩ የሜዳ ላይ ብቃቱን ያሳየውና የቡድኑን ማሸነፍ ያረጋገጠው ፈቴ የጨዋታው ኮከብ (Player of the Match) በመባል ተመርጧል።

ይህንን ታላቅ ድል ተከትሎ ወ/ኮ/ስ ሆስፒታል የውድድሩን የዋንጫ ፍልሚያ የተቀላቀለ ሲሆን፣ በታላቁ የፍፃሜ ጨዋታ ከዞን ፖሊስ ጋር የሚጫወት ይሆናል።

ቡድናችንን እንኳን ደስ አላችሁ እያልን፣ በታላቁ የፍፃሜ ጨዋታም መልካም ዕድል እንመኛለን!

የወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የህክምና አገልግሎት ማሳለጥ ዳይሬክቶሬት፣ የተሃድሶና የፊዚዮቴራፒ ዳይሬክቶሬት እና የባዮሜዲካል ዳይሬክቶሬት የ2019 የስራ ማስጀመሪያና የ2018...
05/09/2026

የወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የህክምና አገልግሎት ማሳለጥ ዳይሬክቶሬት፣ የተሃድሶና የፊዚዮቴራፒ ዳይሬክቶሬት እና የባዮሜዲካል ዳይሬክቶሬት የ2019 የስራ ማስጀመሪያና የ2018 በጀት አመት የማትጊያ ፕሮግራም አካሂዷል።

‎በፕሮግራሙ ባለፍው በጀት አመት የተሻለ አፈፃፀም ላስመዘገቡ ባለሙያዎች እና የስራ ክፍሎች የእውቅና ሰርተፍኬት ተበርክቶላቸዋል።

‎በፕሮግራሙ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር ዶ/ር ሙሂዲን ዑመር በስራ ክፍሎቹ በተጠናቀቀው በጀት አመት የተሰላጠ አገልግሎት መስጠታቸውን በማንሳት በተለይ በአገልግሎት አሰጣጥ ወቅት የገጠመን ችግር ለመፍታት የተኬደው ርቀት እና የተገኘው ውጤት የሚያስመሰግን መሆኑን ገልጸዋል።

የህክምና አገልግሎት ማሳለጥ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዲንሰፋ አማን፣ የተሃድሶና የፊዚዮቴራፒ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሙሂዲን .... እና የባዮሜዲካል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ባዮሜዲካል ኢንጅነር ፋሪስ የዳይሬክቶሬታቸውን የ2018 በጀት አመት የእቅድ አፈጻጸም እና የ2019 እቅድ አቅርበዋል።

በቀረበው የስራ አፈጻጸም ሪፖርትም በአፈጻጸም ወቅት ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን፣ የተወሰደ የመፍትሄ አቅጣጫ እንዲሁም የተሰጠ የአገልግሎት መጠን ቀርቧል።

በቀጣይ የተሻለ ለመፈጸም ዝግጅት መደረጉንም እቅዳቸው ባቀረቡበት ወቅት አብራርተዋል።

በፕሮግራሙ የሆስፒታሉ ሜዲካል ዳይሬክተር ዶ/ር ሙሂዲን ዑመር፣ የአስተዳደርና ልማት ዳይሬክተሩ አቶ ያሲን አወል፣ የዋና ስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት ኃላፊ ዶ/ር ጀማል በድሩ እና የህክምና አገልግሎት ዳይሬክተሩ ዶ/ር ሙስጠፋ መሀመድ በመገኘት በዳይሬክቶሬቶቹ በአመቱ የተሻለ አፈጻጸም ለነበራቸው ባለሙያዎች የእውቅና ሰርተፍኬት አበርክተዋል።

‎የተሰጠው እውቅና ከሰርተፍኬትነት ባለፈ የላቀ ትርጉም እንዳለው ያስታወሱት ዶ/ር ሙሂዲን ዑመር በቀጣይ እውቅና ያገኙትም ይሁን ሌሎች ባለሙያዎች የተሻለ አፈጻጸም ለማስመዝገብ መትጋት እንዳለባቸው በመዝጊያ ንግግራቸው ገልጸዋል።

የተያዘውን በጀት አመት አፈጻጸም የተሻለ ለማድረግም በጋራ በመተጋገዝ እንደሚሰራ ሜዲካል ዳይሬክተሩ ዶ/ር ሙሂዲን ዑመር አክለው ገልጸዋል።

እንኳን ደስ አላችሁ!
01/09/2026

እንኳን ደስ አላችሁ!

የወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከስልጤ ዞን ፖሊስ መምሪያ ጋር በመተባበር ለተቋሙ የጥበቃ ሰራተኞች በልዩ ልዩ የጥበቃና የደህንነት ቁጥጥር  ላይ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ሰጥቷል...
01/09/2026

የወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከስልጤ ዞን ፖሊስ መምሪያ ጋር በመተባበር ለተቋሙ የጥበቃ ሰራተኞች በልዩ ልዩ የጥበቃና የደህንነት ቁጥጥር ላይ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ሰጥቷል።

‎ስልጠናው የተገልጋዩን ማህበረሰብ ደህንነት ለማስጠበቅ ልዩ ትኩረት አድርጓል።

‎የወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከስልጤ ዞን ፖሊስ መምሪያ ጋር በመተባበር ለተቋሙ የጥበቃ ሰራተኞች በልዩ ልዩ የጥበቃና የደህንነት ቁጥጥር ላይ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ሰጥቷል።

‎የአቅም ማጎልበቻ ስልጠናው የስልጤ ዞን ፖሊስ መምሪያ የወንጀል መከላከል ትምህርትና ስልጠና ማስተባበሪያ ሀላፊ በሆኑት በምክትል ኢንስፔክተር ሁሴን ሞሳ እና የስልጤ ዞን ፖሊስ መምሪያ የህዝብ ግንኙነት ሚዲያ ጉዳዮች ዲቪዢን ቡድን መሪ በሆኑት በምክትል ኢንስፔክተር ነጅሙዲን ናስር ተሰጥቷል።

‎ስልጠናው በዋናነት የጥበቃ ሰራተኞችን የመፈጸም አቅም በማሳደግ የተቋሙን አጠቃላይ የጥበቃና ደህንነትን የማረጋገጥ ተግባራት ይበልጥ ለማጠናከር ያለመ መሆኑ ተመላክቷል።

‎​ስልጠናው ላይ የጥበቃ ሰራተኞች የተቋምን ንብረትና ደህንነት በመጠበቅ ተቋማዊ ግብ እንዲሳካ ቁልፍ ሚና እንዳላቸው ተነስቷል።

‎በስልጠናው ወቅት የሆስፒታሉ የጥበቃ ሰራተኞች ከፖሊስ አባላትና ከሌሎች ሥራ ክፍሎች ጋር በመቀናጀት የተሰጣቸውን ኃላፊነት በብቃት መወጣት እንዲችሉ ገለጻና ማብራሪያ ተሰጥቷል።

‎​በዚህም በሆስፒታሉ ግቢ ውስጥ ሊገጥሙ ስለሚችሉ የጸጥታ ችግሮች፣ ሰራተኞቹ ሊከተሏቸው ስለሚገቡ ጥብቅ የፍተሻ ስርዓቶች፣ እርስ በርስ ስለሚኖር የመረጃ ልውውጥ፣ ከፖሊስ ጋር ሊኖር ስለሚገባ የስራ ግንኙነትና በሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ገለጻ በማቅረብ ውይይት ተደርጓል።

‎ወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ የአገልግሎት አድማሱን እያሰፋ በመምጣቱ የተገልጋዮች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መሆኑን በማንሳት ይህን የሚመጥን የጥበቃ ዝግጁነት እንደሚጠበቅ ተገልጿል።

‎በስልጠናው ላይ 40 የሆስፒታሉ የጥበቃ አስተባባሪዎችና ሰራተኞች እንዲሁም ለሆስፒታሉ ጥበቃ የተመደቡ የፖሊስ አባላት ተገኝተዋል።

01/09/2026

የወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ እስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የአይን ህክምና ክፍል የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎትን በማስመልከት በሰጠው ነጻ የአይን ሞራ ግርዶሽ ቀዶ ህክምና የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች አስተያየት :-

Address


Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Worabe Comprehensive Specialized Hospital ወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ እስፔሻላይዝድ ሆስፒታል posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Worabe Comprehensive Specialized Hospital ወራቤ ኮምፕርሄንሲቭ እስፔሻላይዝድ ሆስፒታል:

Shortcuts

  • Want your organization to be the top-listed Government Service?

Share