Woldia city council office /ወልድያ ከተማ ምክር ቤት ጽ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Woldia
  • Woldia city council office /ወልድያ ከተማ ምክር ቤት ጽ/ቤት

Woldia city council office /ወልድያ ከተማ ምክር ቤት ጽ/ቤት የህዝብን ጥያቄ ና የም/ቤቱን ውሳኔ ለህዝብ ተደራሽ ማድረግ

በወልድያ ከተማ ምክር ቤት የ04 የጁ ገነት ቀበሌ ምክር ቤት ወርሃዊ ጉባኤዉን አካሄደ፡፡ነሐሴ 22/2018 ዓ.ም (ወልድያ )ምክር ቤቱ በዋናነት የተወያየባቸዉ አጀንዳዎች •  የቀበሌ አስተዳ...
28/08/2026

በወልድያ ከተማ ምክር ቤት የ04 የጁ ገነት ቀበሌ ምክር ቤት ወርሃዊ ጉባኤዉን አካሄደ፡፡
ነሐሴ 22/2018 ዓ.ም (ወልድያ )

ምክር ቤቱ በዋናነት የተወያየባቸዉ አጀንዳዎች
• የቀበሌ አስተዳዳሪ ሹመት ማጽደቅ
• የቀበሌ ምክር ቤቱን 2019 ዓ.ም አቅድ ማጽደቅ
• የቀበሌ ምክር ቤቱን የቋሚ ኮሚቴ እቅድ ማፅደቅ
• የሴቶች ፎረም እቅድ ማጽደቅ

በሚል አጀንዳዎች ላይ ምክር ቤቱ ዉይይት ያደረገ ሲሆን በቀበሌ አመራር ባለዉ ክፍተት የቀበሌዉ ማህበረሰብ አገልግሎት ለማግኘት እንቅፋት መሆኑን አንስተዉ የቀበሌ አስተዳዳሪዎችን በቶሎ የመተካት ስራ እንደሚገባና ለህብረተሰቡ ፈጣን አገልግሎት መስጠት ይገባል ተብሏል፡፡
በሌላ በኩል የቀበሌ ምክር ቤቱን የ2019 ዓ.ም አመታዊ እቅድ ፤የቋሚ ኮሚቴ እቅድ፤የሴቶች ፎረም እቅድ ቀርቦ የምክር ቤት አባሉ ሰፊ ዉይይት በማድረግ ና የቀጣይ አቅጣጫ በማስቀመጥ ጉባኤዉ ተጠናቋል፡፡

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች ፤ እንኳን ለ1 ሺህ 501ኛው  የነቢዩ መሐመድ የመውሊድ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!በዓሉ የሰላም የፍቅር፣የመተሳሰብ አና  የአብሮነት እንዲሆንላችሁ  ምኞቱ...
24/08/2026

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች ፤ እንኳን ለ1 ሺህ 501ኛው የነቢዩ መሐመድ የመውሊድ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
በዓሉ የሰላም የፍቅር፣የመተሳሰብ አና የአብሮነት እንዲሆንላችሁ ምኞቱን ይገልጻል።

የወልድያ ከተማ ምክር ቤት

የ2019 በጀት አመት የወልድያ ከተማ ምክር ቤት ጽ/ቤት ለተዋረድ ምክር ቤቶች የእቅድ ኦረንቴሽን ተሰጠ፡፡   (ወልድያ ነሐሴ 18/2018 ዓ.ም)የወልድያ ከተማ ምክር ቤት ጽ/ቤት ለ6ቱ ከተ...
24/08/2026

የ2019 በጀት አመት የወልድያ ከተማ ምክር ቤት ጽ/ቤት ለተዋረድ ምክር ቤቶች የእቅድ ኦረንቴሽን ተሰጠ፡፡
(ወልድያ ነሐሴ 18/2018 ዓ.ም)

የወልድያ ከተማ ምክር ቤት ጽ/ቤት ለ6ቱ ከተማ ቀበሌ ምክር ቤቶች አፈ-ጉባኤዎች ፤ምክትል አፈ-ጉባኤዎች ፤ እና ለቋሚ ኮሚቴዊች እና የጽ/ቤት ባለሞያዎች ፤ቡድን መሪዎች የ2019 በጀት አመት የእቅድ ኦረንቴሽን ስልጠና ተሰጠ።

የወልድያ ከተማ ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ የተከበሩ አቶ ኢትዩጵስ አያሌው ለስልጠናው ተሳታፊዎች የስልጠናው አስፈላጊነት ፤ዓላማ ፤የእቅድ መሰረታዊ ይዘትን አስመልክቶ፤ማሟላት የሚገባውን መሰረታዊ ይዘትን ማካተት እንዳለበት በቀጠይ ለመፈጸም እንቅፋት የሆኑትን ግምት ውስጥ ማስገባት እንዳለበት እና እቅዱ የታቀደው የቀበሌውን ሀብት እና አቅም ያገናዘበ መሆኑን የእቅድ ዋና መሰረታዊ ጉዳይ መሆኑን በመክፈቻ ንግግራቸው ለተሳታፊዎች ገልጸዋል፡፡

የወልድያ ከተማ ምክር ቤት ጽ/ቤት የበጀትና እቅድ የክትትልና ቁጥጥር ቡድን መሪ የሆኑት አቶ በድሩ ሁሴን በአጠቃላይ በእቅድ መሰረታዊ ጽንስ ሃሳብ እና በእቅዱ መካትት የሚገባቸውን መሰረታዊ ነጥቦች በማድረግ የስልጠና መነሻ ሰነድ አቅረበዋል፡፡ በሰነዱ ለውይይት የሚሆን በድክመት በጥንካሬ በነበረው አፈጻጸም ተግዳሮቶች በመጠቆም ለተሳታፊዎች አቅረበዋል፡፡
በተለይም የእቅዱ ዋና መነሻው የቀበሌው ሀብት መሰረት ያደረገ መሆን መቻል እንዳለበት በሰነዱ ተጠቁሟል በተለይም የእቅድ ግቦችን እና ዝርዝር ተግባራትን ለመፈጸም የበጀትና የተግባር ማስፈጸሚያ በጀት ትስስር መኖር መቻል እንዳለበት ተገልጾል፡፡

በቀረበው ሰነድ መነሻ በማድረግ ከተሳታፊዎች የተለያዩ ሀሳብ ፤አስተያየት፤ጥያቄዎች በቀረበው እቅድ በቀጣይ ማካተት የሚገባው ለአፈጻጸም ችግር የሆኑ ጉዳዩችን ትኩረት ሰጥተው መሰራት እንዳለባቸው ሀሳባቸውን ገልጸዋል፡፡ በዋናነት ከአስፈጻሚ አካሉ ጋር ያለው ከቅንጅታዊ አስራር ፤ከአመራር ከመተካት ፤ወርሀዊ ጉባኤን ከማስኬድ ፤የቋሚ ኮሚቴዎች የክትትልና ቁጥጥር አስራርን ውጤታማ ከማድረግ አንጻር እንዲሁም የምክር ቤት አባላት የምርጫ ዘመን መራዘም አዲስ ምርጫ መካሄድ አለመቻሉ በዋናነት የተነሱ ሃሰቦች ናቸው ፡፡

ምክር ቤቶች የተሰጣቸውን የህዝብ ውክልና ህገ-መንግስታዊ ሀላፊነት ለመወጣት የተለያዩ የመልካም ስተዳደር ፤የፍትህ ፤የልማት ማህበራዊ ፤ኢኮኖሚያዊ የሆኑ ችግሮችን ለመፍታት የክትትልና ቁጥጥር ፤የወረሀዊ ጉባኤ በማካሄድ፤የህዝብ ግንኙነት ተግባራ ውጤታማ በማድርግ እና ከአሰፈጻሚ አካላት ጋር ቅንጅታዊ አሰራርን በማጠናከር በቀጣይ ትኩረት ተሰጥቶ መስራት እንዳለበት ተጠቁሟል፡፡ በተደጋጋሚ የተለያዩ የአቅም ግናባታ ስልጠናውችን በእቅዳችን መሰረት ተፋጸሚ እንደሚሆን ተገልጾል፡፡

የ2019ዓ .ም የእቅድ ኦረንቴሽን የወልድያ ከተማ ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ የተከበሩ አቶ ኢትዩጵስ አያሌው ለ6ቱ የተዋረድ የከተማ ምክርቤቶች አፈ-ጉባኤዎች ፤ምክትል አፈ-ጉባኤዎች ፤እና ለቋሚ ኮሚቴዊች በመስጠት የእቅድ ኦረንቲሽን የቀጣይ አቅጣጫዎችን በመስጠት ስልጠናው ተጠናቋል፡፡
የወልድያ ከተማ ምክር ቤት
(ነሐሴ 18/2018 ዓ.ም)
ወልድያ

የሶለል ቡሄ በዓል አከባበር (ወልድያ ከተማ)ነሐሴ-16/2018ዓ.ም  Woldia City Communication Affairs Office
22/08/2026

የሶለል ቡሄ በዓል አከባበር (ወልድያ ከተማ)
ነሐሴ-16/2018ዓ.ም
Woldia City Communication Affairs Office

"ባህል ድልድያችን፤ አንድነት መዳረሻችን" አሸንድየ አሸንዳ እና ሶለል ስርአተ ክዋኔ በልጃገረዶቹ አማካኝነት የሚከወን ባህላዊ ክዋኔ ነዉ፡፡የክዋኔዎቹ የቡድን አመሰራረት ደግሞ እድሜያቸዉን መ...
18/08/2026

"ባህል ድልድያችን፤ አንድነት መዳረሻችን"

አሸንድየ አሸንዳ እና ሶለል ስርአተ ክዋኔ በልጃገረዶቹ አማካኝነት የሚከወን ባህላዊ ክዋኔ ነዉ፡፡የክዋኔዎቹ የቡድን አመሰራረት ደግሞ እድሜያቸዉን መሰረት በማደረግ ይተገበራል፡፡ የበዓሉ መከበር በርካታ ፋይዳዎች አሉት፡፡

ባህላዊ ፋይዳዉን ብንመለከት ሥርአተ ክዋኔዎቹ ከተለያዩ ባህላዊ ዘፈኖች ፣ዉዝዋዜዎች ፣ጭፈራዎች ባህላዊ የሙዚቃ መሳሪያዎች ባህላዊ አልባሳት፣እና ጌጣጌጦች ታጅበዉ ይቀርባሉ፡፡የጸጉር ስሬቶች እንዲሁም ባህላዊ የፍቅር መግለጫ ሥርአቶች ባህላዊ መሰረታቸዉን ጠብቀዉ ከትዉልድ ትዉልድ እንዲሸጋገሩ የማስቻል አቅም አላቸዉ፡፡ሥርአተ ክዋኔዉ የባህለዊ እሴት መወራረስ እንዲኖር ቀጣይነቱን ለማረጋገጥ እንዲሁም ትውልዱ ከባህላዊ ሥርአቶቹ ትምህርት እንዲቀስም ያስችላል፡፡

በዓሉ ከፍተኛ ቱሪዝማዊ ፋይዳም ያስገኛል የአሸንድየ ሻደይ እና ሶለል ሥርአተ ከበራዎች በቱሪስቶች ልቦና ዉስጥ አይረሴነታቸዉን የማሳረፍ አቅም አላቸዉ፡፡በመሆነንም ቱሪስቶች እለቱን በጉጉት እንዲጠብቁት የማድረግ አቅምን ይፈጥራል ፡፡ሀገር በቀል ዜማዎቹ ፣ቃል ግጥሞቹ ፣ዉዝዋዜዉ እንዲሁም ጭፈራዉ በዉህደት በስሜት ህዋሳት እንዲጣጣሙ የማድረግ ኃይል አላቸዉ፡፡ይህ ደግሞ አይረሴነቱን ይተክላል ሥርአተ ከበራዎች በሀገረሰባዊ አልባሳት ፣በሀገረሰባዊ ምግብና መጠጦች እንዲሁም በሀገረሰባዊ እጅ ስራዎች ደምቀዉ የሚከወኑ በመሆናቸዉ የቱሪስት መስህብን የማጎልበት ሚናቸዉ የላቀ ነዉ፡፡

የአሸንድየ ፣ሻደይእና ሶለል ሥርአተ ከበራዎች በተለያዩ ቁሳዊ ባህሎችና ባህላዊ ስርአቶች መሪነት የሚከወን በመሆኑ ቱሪስቶች የማህበረሰቡን ባህል፣ታሪክ፣ግብረ ገብነት፣ማህበራዊ መስተጋብር ፣ፍልስፍና እንዲሁም ስነ ልቦናዊ እሳቤዎችን ይረዱበታል፡፡

ስርአታዊ ክንዉኑ ደግሞ ቱሪዝማዊ ትሩፋትን ያጎናጽፋል፡፤በሌላ መልኩ ባህላዊ አልባሳቱ የማህበረሰቡን ታሪክ፣ፍልስፍና፣ማህበራዊ ደረጃ፣እድሜ ምጣኔ ሀብታዊ እርከንን፣ እንዲሁም ማህበራዊነትን የመግለጽ ሚና አላቸዉ፡፡ የአልባሳቱ የአሰራር ጥበብ የቀለሞቹ ትርጓሜ የሚለብስበት ወቅት እና ሂደት ቱሪዝማዊ ትሩፋቶችን ያመርታሉ፡፡ቱሪስቶች አልባሳቱን ሌሎች የማህበረሰብ ክፍሎች ቀጥተኛ ወይም ኢቀጥተኛ በሆነ መልኩ የሚያስተዋዉቁበት አጋጣሚዉ ከፍ ይላል፡፡

የዘንድሮውን የሶለል በዓል በወልድያ ከተማ ባህላዊና ሃይማኖታዊ ይዘቱን ሳይለቅና ሳይከለስ፣ "ባህል ድልድያችን፤ አንድነት መዳረሻችን" በሚል መሪ ሐሳብ ለማክበር ሰፊ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ፡፡


ባህለዊ እሴቶቻችንን ሳይበረዙ ሳይከለሱ መጠበቅና ለቀጣዩ ትዉልድ ማስተላላፍ ከሁላችንም ይጠበቃል መልእክታችን ነዉ፡፡

ባህል የማንነታችን መገለጫ የአንድነታችን መሰረት ነዉ!!
Woldia City Communication Affairs Office

  Amhara National Regional council የአማራ ክልል ም/ቤት 6ኛው ዙር፣ 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 12ኛ መደበኛ ጉባኤውን በይፋ ማካሄድ ጀመረ። ሐምሌ 23/2018ዓ.ም የተከበ...
30/07/2026

Amhara National Regional council
የአማራ ክልል ም/ቤት 6ኛው ዙር፣ 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 12ኛ መደበኛ ጉባኤውን በይፋ ማካሄድ ጀመረ።

ሐምሌ 23/2018ዓ.ም

የተከበሩ ወ/ሮ ፋንቱ ተስፋዬ የአማራ ክልል ም/ቤት አፈጉባኤ
ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር ጉባዔው 7ኛው ዙር ሀገራዊ እና ክልላዊ ምርጫ በተደረገበት ማግስት እንዲሁም ሁሉም የኢትዮጵያ ልጆች ለዘመናት የገጠሙን እና እያጋጠሙ ያሉ ችግሮች ለመፍታት እና የወደፊቷን ኢትዮጵያን ለትውልድ ምቹ ለማድረግ እየተሞከረ ባለበት ወቅት የሚደረግ ጉባኤ በመሆኑ ልዩ ያደርገዋል ብለዋል ።

የተጀመረው የህግ የማስከበር ተግባር ጎን ለጎን በንግግር እና ድርድርን በማጠናከር ዘላቂ ሰላምን ማረጋገጥ፤በፍትህ ስርዓቱ ላይ የዜጎች አመኔታን እንዲያጎለብቱ የህዝብ ተሳትፎን በማጠናከር የአቅም ግንባታ ተግባራትን በማጠናቀቅም የተጠያቂነት አሰራር መዘርጋት፤አገልግሎት አሰጣጣችን ለማሻሻል የሲቪል ሰርቪሱን ሪፎርሙን ተግባራዊ አጠናክሮ መቀጠል፤የገቢ አሰባሰብ የሰራ እድል ፈጠራን ማሳደግ፤የህዝብ ተሳታፊነትን እና ተጠቃሚነትን ማሳደግ፣ ብልሹ አሰራርን እንዲቀንስ አጠናክሮ መስራት ፣በጠንካራ ተቋማዊ አሰራር ማጠናከር የሚሉ ጉዳዮችን በትኩረት መስራት እንሚገባ የተከበሩ አፈጉባዔዋ አሳስበዋል ።

​የ15 ዓመት ሮድ ማፕ ከባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር Validation እየተካሄደ እንደሆነ፣ በእስቴት ዩኒቨርሲቲ 6ኛው ዙር የምክር ቤት ተግባራት ጥናት እየተሰራ መሆኑ፣ የም/ቤቱ ጽ/ቤት መዋቅራዊ እንደገና ጥናት መደረጉ ፣ም/ቤቶች የተጣለባቸውን ተግባርና ኃላፊነት ለመወጣት በበጀት ዓመቱ ቋሚ ኮሚቴዎች በ3 ከተማ አስተዳደር ፤ 1ዞን ፤ 2ወረዳ የመስክ ምልከታ መደረጉ፣የህዝብ አቤቱታቸውን የተቋም የአፈፃፀም ሪፖርት እና ለሁሉም ተቋማት በየሩብ ዓመቱ ግብረ-መልስ መሰጠቱ እና በ6ወሩ እና የአመቱን ማጠቃለያ ሪፖርት ከተቋም ኃላፊዎች እና ማኔጅመንት በጋራ ውይይት መደረጉ የሚሉትን ምክር ቤቱ እንዳከናዎናቸው ገልፀዋል።

ስድስተኛው ዙር የአማራ ክልል ምክር ቤት መስከረም 20/2014 በመስረች ጉባኤ ተጀምሮ ብዙ ተግባራት በማከናወን፤ወጣ ወረዶችን በማለፍ በምክር ቤት አባላቶች፤የምክር ቤት አመራር እና ባለሙያ፤ የክልሉ መንግስት እና አጋር አካላት ትብብር 12 መደበኛ እና 1 አስቸኳይ ጉባኤዎችን ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል ።

የወልደያ ከተማ ምክር ቤት የ4ኛ ዙር 13ኛ አመት 41ኛ መደበኛ ጉባኤ አካሄደ ፡፡(ከሀምሌ 11/2018 ዓ.ም ወልደያ) የወልደያ ከተማ ምክር ቤት የ4ኛ ዙር 13ኛ አመት 41ኛ መደበኛ ጉባኤ...
18/07/2026

የወልደያ ከተማ ምክር ቤት የ4ኛ ዙር 13ኛ አመት 41ኛ መደበኛ ጉባኤ አካሄደ ፡፡
(ከሀምሌ 11/2018 ዓ.ም ወልደያ)

የወልደያ ከተማ ምክር ቤት የ4ኛ ዙር 13ኛ አመት 41ኛ መደበኛ ጉባኤ ለሁለት ተከታታይ ቀናት የተካሄደ ሲሆን የጉባኤው ተሳታፊዋች የምክር ቤት አባላት፣ቋሚ ኮሚቴዎች ፤የቀበሌ ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤዎች ፤የወልደያ ከተማ የመምሪያና የተጠሪ ጽ/ቤት አመራሮች፤ የቀበሌ ዋና አስተዳዳሪዎች፤ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችቸ የሀይማኖት ተቋማት ተወካዩች፤በከተማዋ የሚገኙ የትምህርት ኮሌጆች ፤ዩኒቨርሲቲ እና የቴክኒክ ከሌጆች እና የክፍለ ከተማ ስራ አስፈጻሚዎች፤ በጉባኤው ተሳትፈዋል ፡፡
የምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ የተከበሩ አቶ ኢትዮጲስ አያሌው የመክፈቻ ንግግራቸው የገለጽት በበጀት አመቱ የተከናወኑ አንጸባራቂ የልማት ፤የመልካም አስተዳደር እና የጽጥታ ስራዎች የተገኙ ድሎች መሆናቸውን አንስተዋል፡፡ ዋና አፈ-ጉባኤው አክለው በከተማችን በተሰሩ ስራዎች ውጤታማ የሆኑት ስራን ቆጥሮ በመቀበል መቻሉ፤ አመራሩ ከታች ወረዶ መስራት መቻሉእና ስራዎችን ክትትልና ቁጥጥር በማድርጉ እንዲሁም በጥብቅ የአመራር ድሲፕሊን የተመራ መሆኑን ገልጸዋል በመጨረሻም የእለቱን የመወያያ አጀንዳዎች ለምክር ቤት አባላት በማቅረብ አጽድቀው ጉባኤው በይፋ የተከፈተ መሆኑን አሳውቀዋል።

የወልደያ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ዱባለ አብራሬ የ2018 በጀት አመት የእቅድ አፈጻጽም ሪፖርት በማህበራዌ ፣በመልካም አስተዳደር፣በፍትህ እና በኢኮኖሚ፣በሰላምና ጸጥታ፣በልማት ዘርፍ ትኩርት በማድረግ በዝር ዝር ለተከበረው የምክር ቤት አባላት አቅርበዋል ፡፡
በመቀጠል የከተማ የቋሚ ኮሚቴ አባላት በመስክና በቢሮ ባደረጉት ምልከታ የምክር ቤቱ የውሳኔ ሀሳብ እና የቀጣይ አቅጣጫዎችን የጥምር ቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ የተከበሩ አቶ መልኩ ደጉ አማካኝነት በዋና ዋና ጉዳዩች በማተኮር ለምክር ቤቱ በዝርዝር አቅርበዋል ፡፡
በቀረበው ሪፖርት መነሻ በማድረግ በጉባኤው ተሳታፊዎች በርካታ ሀሳብ አስተያየት እና ጥያቄዎች ተነስተዋል በዋናነት የተሸከርካሪ የነዳጅ አቅርቦት የፍታህዌነት እና ተደራሽነት የክትትልና ቁጥጥር ስራ ትኩረት ማነስ፤ከጤና አገልግሎት አስጣጥ ፍታህዌነትና ፈጣን ምላሽ ከመስጠት አንጸር ፤የማህበረስብ ተጠቃሚነት ፤የትራንስፕርት ታሪፍ ክፍያ ስርዓት ክፍተት ለተገልጋዩች አስቸጋሪ መሆኑ ፤በከተማው የተገነቡ ሸዶች ለሚመለከተው አካል ከማስተላላፍ ፤የኢንዱስትሪ ምርቶች አቅርቦትና ስርጭት፤ከኢንቨስትመንት የቦታ አቅርቦትና ፍቃድ የወሰዱ ባለሀብቶችን ወደ ስራ ከማስገባት አንጻር ፤ህገውጥ የመሬት ወረራ ከመከላከልና ከመቆጣጠር እንዲሁም የትክ ቦታ ከሶስተኝ ወገን ከማጻዳት ለአብነት በተሳታፊዎች የቀረቡ ፤ሀሳብ እና አስተያየቶች ጥያቄዎች የሚጠቀሱ ናቸው፡፡
አስፍጻሚ አካላት በተከበረው ምክር ቤት የቀረቡትን ፤ሀሳብ እና አስተያየቶች ጥያቄዎች በግብዓት በመውሰድ በቀጣዩ በጀት አመት የእቅድ አካል በማድርግ የተጠቆሙትን ክፍተቶች በማስተካከል ይቻላል በማለት አስተያየት ተሰጥተዋል፡፡

በማጠቃለያዉም ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ዱባለ አብራሬ በሁሉም ዘርፍ ለተነሱ ሀሳብ አስተያየቶችና ጥያቄዎች በዝርዝር ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል ትኩረት አድርገው ምላሽ ከሰጡበት ነጥቦች ፤ህገ ወጥ የመሬት ወረራ ከመከላከልና ከመቆጣጠር እንዲሁም የትክ ቦታ ከሶስተኝ ወገን ከማስጻዳት ጋር ተያይዞ ችግሩን ለመፍታ በቀጣዩ የተሻለ አመራር በመመደብ ቅንጅታዊ አሰራርን በማጠናከር ከስካሁኑ በተሻለ መንገድ የተጠያቂነት ስርዓት በቀጣይ በማጠናከር ኑኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡የከተማ አረንጓዴ ልማት የከተማ ግብርና ወደ ትግበራ ለመግባት አደረጃጀት በመመስረት በቀጣይ ውጤታማ ስራ እንደሚሰራ አሳስበዋል፡፡

የከተማ አውቶብስ ትራንስፖርት ፌርማታ በተመለከተ ፤የወልደያ ስታዲዩም እና መናሀሪያው ለመግንባት ፕላንና በጀት መሰረት በ2019 በጀት አመት ወደ ስራ ይገባል የምክር ቤት አባላትም በተለመደው አግባብ መንግስት የሰተጠውን ውክልን በአግባቡ በመወጣት ከጎናችን ሆኖ እንዲደግፈን እንዲያበረታታን በማለት ገልጻዋል፡፡ ተቀዳሚ ከንቲባው አክለው እንደገለጹት የተቋማትን እቅድ አፍጻጸም ውጤታማ ለማድርግ በቴክኖሎጅ የዳበረ እውቀት፤ ክህሎት ፤የትምህርት ዝግጅት አቅም ያላቸውን አመራሮችን በማፍራት ትኩርት አድርግን በቀጣይ እንደሚሰራ አሳስበዋል፡፡

በከተማው የተገነቡ ሽዶችን በቀጣይ በተዘጋጀው የመመልመያ መስፈርት መሰረት ለሚመለከታቸው አካላት የማስተላለፍ ስራ ይስራል ከብልሹ አስራር እና ከሙስና በጸዳ በተዋቀረው ኮሚቴ አማካኝነት ውጤታማ ተግባራት እንደሚከናወን ለተከበረው የምክር ቤት አባላት አስታውቀዋል፡፡
የወልደያ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ዱባለ አብራሬ ከተማችነን ከመተላለፊይነት አልፎ መዳረሻነት ለማድርግ ሁሉም የከተማችን ኗሪ ማህበረስብ በአገር ውስጥ በውጭ አገር ያሉት ተወለጆች ታዋቄ ባለሀብቶች በቀጣይ የሚሰጠውን ተልኮ በብቃት ፤በቁርጠኝነት ፤ ፍጹም ልማት ወዳድነት ልንተገብርው ወደ ተግባር ልንቀይርው ይገባል ሲሉ ተደምጠዋል ፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ የከተማችን የባህላዊ የዕርቅ፤የሽምግልና ስነ-ስርዓቶች በጥናት በመለየት ውጤታማ ማድርግ ይቻላል የወልድያ ዩኒቨርሲቲ ፕሪዝደንት ዶ/ር አነጋግሬ ጋሻው በሞያ በማገዝ በእውቀት ፤ክህሎት ላይ ተመስርቶ ስራውን ውጤታማ ለማድረግ እና ወደፊትም የተለያዩ ሲሚናሮችን በማካሄድ የእውቀት ሽግግር ማድረግ ይቻላል በማለት አሳውቀዋል፡፡

የ2018 በጀት አመት ወልድያ ከተማ ፍርድ ቤት አመታዊ የእቅድ አፍጻጸም ሪፖርት በፍረድ ቤቱ ፕሪዝደንት አቶ ጌታሁን እንደሻው አጠቃላይ የተከናወኑ ተግባራት በዋና ዋና ጉዳዩች ላይ ትኩረት በማድረግ በዝርዝር ለተከበረው የምክር ቤት አባላት አቅርበዋል፡፡በቀጣይ የከተማው የሚከናወኑ ህገወጥ የመሬት ወረራን ከመከላከል አንጻር በጋራ ተቀናጅቶ በተቀመጠው መመሪያና ስርዓት ተከትሎ መንግስት የሰጠነን ህግ የመተርጎም ሀላፊነት እንደሚወጡ ለዚህም ስኬታማነት የተከበረው የምክር ቤት አባላት ፤የከተማው በማህበረስብ እንዲሁም የህግ አውጭው ምክር ቤቱ እና የወልድያ ከተማ ቋሚ ኮሚቴ አባላት በጋራ በመቀናጀት የተጠያቂነት ስርዓት በማጠናከር የከተማው የህገ ወጥ የመሬት ወረራ ለመከላከል ሞያዊ ሀላፊነትን እንደሚወጡ ፕሬዝደንቱ ገልጸዋል፡፡
ምክር ቤቱ ባካሄደው መደበኝ ጉባኤ ከቀረቡት አጀንዳዎች መካከል አንዱ የሆነው የትምህረት ጥራትና ኤንስፔክሽን ሲሆን ሪፖርት ትኩረት ያደረገው የትምህርት የጥራት ችግር መንስኤ የሆነው በዋናነት የግብአት አቅርቦት እና ጥምርታ ተቋማት አብዛኝው ከስታንደርድ በታች መሆኑ ለአብነት ተጠቆሟል፡፡ በቀጣይ ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት የማህበረሰብ ተሳትፎን በማጠናከር ውጤታማ ተግባራት ማከናወን እንደሚቻል የወልድያ ከተማ የትምህረት ጥራትና ኤንስፔክሽን ቡድን መሪ የሆኑት አቶ ተስፋ ማሪያም ይመር ጠቁመዋል፡፡

የስራዓተ ጾታ አካቶ ትግበራ ሴቶች ፤ወጣቶች፤ አረጋውያን ፤አቅመደካሞች፤አካልጉዳተኞች የሆኑ የህብረተስብ ክፍል በዘላቂነት ለመፍታት የችግሩን መጠን መሰረት በማድረግ በገንዘብ ፤በዓይነት፤በጎልበት፤ በማማከር ፤የአቅም ግንባታ ስልጠና በቅንጅት ከሚመለከተው አካል ጋር በመስራት በቀጣይ ተጠናክሮ መሰራት እንዳለበት የሴቶች ህጻናት አረጋዉያን አካቶ ትግበራ ቡድን መሪ የሆኑት አቶ ሰለሞን በላይ ተገልጾል፡፡

የወልድያ ከተማ ከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ ሃላፊ የሆኑት አቶ ዝናቡ ሰጠ የከተማችንን ጽዳት ለመጠበቅ እና ጤናማ ማህበረሰብ ለመፍጠር የሚገነቡ የመኖሪያ ቤቶች ግንባታ አይነትና ጥራት ለመጠበቅ ዘላቂ ለማድረግ ረቂቅ ደንብ ጸድቋል፡፡
የገነቴ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ ልማት ጸ/ቤት የ2018 በጀት አመት የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርት በዋና ዋና ጉዳዮች ትኩረት በማድረግ የጽ/ቤቱ ሃለፊ የተከበሩ አቶ ጥላሁን አጥናፌ ለተከበረዉ ምክር ቤት ሪፖርቱን አቅርበዋል በተለይም ኢንተርፕራይዙ ከተቋቋመ 10 አመት የልማት ጉዞ ያከናወናቸዉን የከተማ ልማት የማህበረሰብ ልማት የተለያዩ ልምዶችን ከተቋሙ አፈጻጻም ገቢን ከማሳደግ እድገቱን በማፋጠን የተሻለ ዉጤት ያስመዘገበ ተቋም መሆኑ ተገልፆል፡፡
የወልድያ ከተማ ምክር ቤት ጽ/ቤት የ2018 በጀት አመት የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርት በክብርት አበባ አያሌው በተቋሙ ዋናዋና ግቦች ትኩረት በማድረግ አቅርበዋል በመጨረሻም የተከበሩ ዋና አፈ-ጉባኤ የምክር ቤቱን 4ኛ ዙር 13ኛአመት 41ኛ መደበኛ ጉባኤ የቀጣይ አቅጣጫዎችና የዉሳኔ ሃሳቦች በዝርዝር ለተከበረዉ ምክር ቤት አቅርበዉ ጉባኤው ተጠናቋል።

የወልድያ ከተማ ምክር ቤት
ሐምሌ 11 2018 ዓ.ም

የወልድያ ከተማ ምክር ቤት 4ኛ ዙር 13ኛ ዓመት 41ኛ መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀመረ።ሐምሌ 10/2018 ዓ.ምበጉባዔው የወልድያ ከተማ አስተዳደር 2018 ዓ.ም በጀት አመታዊ እቅድ አፈፃፀም...
17/07/2026

የወልድያ ከተማ ምክር ቤት 4ኛ ዙር 13ኛ ዓመት 41ኛ መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀመረ።
ሐምሌ 10/2018 ዓ.ም
በጉባዔው የወልድያ ከተማ አስተዳደር 2018 ዓ.ም በጀት አመታዊ እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት መገምገም ፣ የወልድያ ከተማ ፍርድ ቤት አመታዊ እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ማድመጥ፣ የወልድያ ከተማ የኦዲት ግኝት አመታዊ እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ማድመጥ ፣ የትምህረት ጥራት ኢንስፔክሽን አመታዊ እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ማድመጥ፣ የስራዓተ ፆታ አካቶ ትግበራ አመታዊ እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ማድመጥ፣ የወልድያ ከተማ ምክር ቤት ፅ/ቤት አመታዊ ሪፖርት ማድመጥ፣ ልዩ ልዩ ደንቦችን ማፅደቅ በሚል አጀንዳዎች ምክር ቤቱ 4ኛ ዙር13 ኛ አመት 41 ኛመደበኛ ጉባኤ ለተከታታይ ሁለት ቀናት የተለያዩ ውሳኔ ሳቦችና የቀጣይ አቅጣጫዎች ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል።

Address

Adago
Woldia

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Woldia city council office /ወልድያ ከተማ ምክር ቤት ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share