03/06/2026
የጋዞ ወረዳ አስተዳደር ምክር ቤት የልማት፣ የፖለቲካና መልካም አስተዳደር ተግባራት አፈፃፀም ግምገማ አካሄደ!
እስታይሽ ፦ ግንቦት 26/2018 ዓ.ም(ጋዞ ወረዳ ኮሙኒኬሽን)
በሰሜን ወሎ ዞን የጋዞ ወረዳ አስተዳደር ምክር ቤት ከወረዳው ጠቅላላ አመራር በተገኙበት የውይይት ባለፉት ሁለት ወራት የልማት ፣ የፖለቲካና የመልካም አስተዳደር ተግባራት አፈፃፀም ዙሪያ የነበሩ ጥንካሬና ድክመቶችን በመለየት ሰፊ ውይይት የተደረገ ሲሆን በቀጣይም በትኩረት ተይዘው የሚከናወኑ ዋና ዋና የልማትና የመልካም አስተዳደር ተግባራት በዝርዝር ተለይተው ቀርበው አቅጣጫ ተቀምጧል ።
የውይይት መድረኩን የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሃብቴ ካሳው እና የወረዳው ብልፅግና ፓርቲ ቅ /ጽ/ቤት አቶ ዝናቡ ገረመው በጋራ መርተውታል።