Gazo Woreda Government Communication Office

Gazo Woreda Government Communication Office ጋዞ ወረዳ በሰሜን ወሎ ዞን አስተዳደር ከሚገኙ ወረዳዎች አንዱ ነው።

የጋዞ ወረዳ አስተዳደር ምክር ቤት  የልማት፣ የፖለቲካና  መልካም አስተዳደር  ተግባራት አፈፃፀም ግምገማ አካሄደ!እስታይሽ ፦ ግንቦት 26/2018 ዓ.ም(ጋዞ ወረዳ ኮሙኒኬሽን) በሰሜን ወሎ ...
03/06/2026

የጋዞ ወረዳ አስተዳደር ምክር ቤት የልማት፣ የፖለቲካና መልካም አስተዳደር ተግባራት አፈፃፀም ግምገማ አካሄደ!

እስታይሽ ፦ ግንቦት 26/2018 ዓ.ም(ጋዞ ወረዳ ኮሙኒኬሽን)

በሰሜን ወሎ ዞን የጋዞ ወረዳ አስተዳደር ምክር ቤት ከወረዳው ጠቅላላ አመራር በተገኙበት የውይይት ባለፉት ሁለት ወራት የልማት ፣ የፖለቲካና የመልካም አስተዳደር ተግባራት አፈፃፀም ዙሪያ የነበሩ ጥንካሬና ድክመቶችን በመለየት ሰፊ ውይይት የተደረገ ሲሆን በቀጣይም በትኩረት ተይዘው የሚከናወኑ ዋና ዋና የልማትና የመልካም አስተዳደር ተግባራት በዝርዝር ተለይተው ቀርበው አቅጣጫ ተቀምጧል ።

የውይይት መድረኩን የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሃብቴ ካሳው እና የወረዳው ብልፅግና ፓርቲ ቅ /ጽ/ቤት አቶ ዝናቡ ገረመው በጋራ መርተውታል።

የዞኑ ሕዝብ በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ፍፁም ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የነቃ ተሳትፎ ማድረጉ ተገለፀ፡፡ወልድያ፦ ግንቦት 25/2018 ዓ.ም (ሰሜን ወሎ ዞን ኮሙኒኬሽን) በዞኑ የተካሄደው 7ኛው ዙ...
02/06/2026

የዞኑ ሕዝብ በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ፍፁም ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የነቃ ተሳትፎ ማድረጉ ተገለፀ፡፡

ወልድያ፦ ግንቦት 25/2018 ዓ.ም (ሰሜን ወሎ ዞን ኮሙኒኬሽን) በዞኑ የተካሄደው 7ኛው ዙር ሀገራዊ ምርጫ ፍጹም ዲሞክራሲያዊ፣ ሰላማዊ፣ ፍትሃዊና ታማኝነት ባለው መልኩ መጠናቀቁን ተገለፀ፡፡

የምርጫ ሂደቱን አስመልክቶ ማብራሪያ የሰጡት የሰሜን ወሎ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አራጌ ይመር 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ስኬታማ እንዲሆን ከቅድመ ዝግጅት ጀምሮ፣ በምርጫው ዕለትና ከምርጫ በኋላ የሚከናወኑ ተግባራት ታቅደው ሰፊ ርብርብ ሲደረግ መቆየቱን ገልጸዋል።

በዞኑ በሚገኙ ሁሉም የገጠር ወረዳዎችና የከተማ መስተዳድሮች የሚገኘው ሕዝብ መብቱን በመጠቀም፣ "ይሆነኛል፣ ይጠቅመኛል" የሚለውን መንግስት ለመምረጥ በነቂስ መውጣቱ አስተዳዳሪ ተናግረዋል፡፡

ሕዝቡ ያለምንም መሰላቸት ከጠዋቱ 12:00 ሰዓት ጀምሮ በሰልፍ በመጠባበቅና የምርጫ ሕጉን በማክበር፣ በፍጹም ትዕግስትና አስተዋይነት ድምጹን ሲሰጥ መዋሉን የገለጹት አቶ አራጌ ለዚህም ለዞኑ ሕዝብ ታላቅ ክብርና ምስጋና አቅርበዋል።

በየደረጃው በሚገኘው የምርጫ ክልልና ምርጫ ጣቢያዎች የተመደቡ የምርጫ አስፈጻሚዎች የተጣለባቸውን ኃላፊነት በአግባቡ መወጣታቸውንና ከአካባቢው ተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር በመተባበርና በመቀናጀት ተልዕኳቸውን ማሳካታቸው ገልፀዋል።

ምርጫው በስኬት እንዲጠናቀቅ አመራሩ፣ ሕዝቡ፣ አስፈጻሚዎች፣የፀጥታ መዋቅሩና ተፎካካሪ ፓርቲዎች በጋራ ምክር ቤት አማካኝነት በቅንጅት መስራታቸው ለውጤቱ መገኘት ትልቅ አስተዋጽኦ ማበርከቱ ገልጿል።

ከምርጫ በኋላ ስላለው ዝግጁነት የምርጫ ቦርድ ይፋዊ ውጤትን ከተከተለ በኋላ ሕዝቡ የመረጠው ፓርቲ በኃላፊነትና በአደራ ማገልገል እንዳለበት ጠቁመዉ። እንደ ብልጽግና ፓርቲ ምርጫውን ካሸነፉ፣ በየማኒፌስቶው የገቧቸውን ቃላቶች በሙሉ በማክበር ሕዝብን ዝቅ ብሎ ማገልገል እንደሚገባ ገልፀዋል።

በመጨረሻም ዋና አስተዳዳሪዉ በሕዝቡ ዘንድ የሚነሱ የአገልግሎት አሰጣጥ፣ የመልካም አስተዳደር፣ የፍትሃዊነትና የልማት ጥያቄዎችን በአግባቡ ለቅሞ በመፍታት፣ ሕዝብ የሰጠውን አደራ በተግባር ለመወጣት ፓርቲው ሙሉ ዝግጁነትና ግዴታ ያለበት መሆኑን አስገንዝበዋል።

በመቄት ቀጥር ሁለት እና በዋድላ የምርጫ ክልሎች  በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች የምርጫ ቁሳቁስ ስርጭት ተጠናቆ ለምርጫ ዝግጁ ሆኗል። በሰሜን ወሎ ዞን በመቄት ቁጥር 2 የምርጫ ክልል እና በዋድላ...
31/05/2026

በመቄት ቀጥር ሁለት እና በዋድላ የምርጫ ክልሎች በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች የምርጫ ቁሳቁስ ስርጭት ተጠናቆ ለምርጫ ዝግጁ ሆኗል።

በሰሜን ወሎ ዞን በመቄት ቁጥር 2 የምርጫ ክልል እና በዋድላ የምርጫ ክልል ስር ለሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች የድምፅ መስጫ ቁሳቁስ ስርጭት በአግባቡ የተሰራጨጪ ሲሆን የምርጫ ጣቢያዎችም ግንቦት 24/2018ዓ.ም ለሚደረገው 7ኛው ጠቅላላ ክልላዊና ሀገራዊ ምርጫ በተሟላ መልኩ ድምፅ ለማሰጠት የሚያስችል ዝግጂት አዲርገው አጠናቀዋል።

31/05/2026
7ኛውን ጠቅላላ ክልላዊና ሀገራዊ ምርጫ በስኬት ለማጠናቀቅ የፀጥታ ሀይሉ ዝግጁ መሆኑ ተገለፀ።እስታይሽ ፦ግንቦት22/2018 ዓ.ም (ጋዞ ወረዳ ኮሙኒኬሽን)7'ኛውን ጠቅላላ ክልላዊና ሀገራዊ ም...
30/05/2026

7ኛውን ጠቅላላ ክልላዊና ሀገራዊ ምርጫ በስኬት ለማጠናቀቅ የፀጥታ ሀይሉ ዝግጁ መሆኑ ተገለፀ።

እስታይሽ ፦ግንቦት22/2018 ዓ.ም (ጋዞ ወረዳ ኮሙኒኬሽን)

7'ኛውን ጠቅላላ ክልላዊና ሀገራዊ ምርጫ ያለምንም የፀጥታ ችግር በሰላም እንዲጠናቀቅ የሚያስችል በቂ ዝግጅት ማድረጉን የጋዞ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት አስታወቀ ።

የጽ/ቤቱ ዋና አዛዥ ኢ/ር አብርሃም አበበ እንደገለፁት 7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ያለምንም የፀጥታችግር ሰላማዊ በሆነ መንገድ በስኬት እንዲጠናቀቅ በቅድመ ዝግጂት፣ በምርጫው እለትና ከምርጫው በኋላ መሰራት ያለባቸውን ተግባራት የወረዳው የፀጥታ መዋቅር ከሀገር መከላከያ ሠራዊት ጋር በመሆን ጠንካራና የተቀናጀ የቅድመ ዝግጅት ስራ መስራቱን ገልፀው መራጩ ሕዝብ በምርጫ ዕለት በየምርጫ ጣቢያው ያለምንም የፀጥታ ስጋት ድምፁን መስጠት እንዲችል ጠንካራ ስራ መስራቱን ተናግረዋል።

አዛዡ አክለውም የፀጥታ መዋቅሩ ጠንካራ የክትትል ስራ እየሰራ በመሆኑ የአካባቢው ማኅበረሰብ ከጸጥታ መዋቅሩ ጎን በመሰለፍ መረጃ በመስጠት የመተባበር እሴቱን የበለጠ በማጠናከር ለምርጫው ስኬታማነት የበኩሉን እገዛ እንዲያደርግ አሳስበዋል ።

በዩኒሴፍ ዋሽ አማካኝነት ለሴት ልጅ አገረድ ተማሪዎች የተለያዩ የንፅህና መጠበቂያ ቁሳቁሶች  ድጋፍ መደረጉን የጋዞ ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት አስታወቀ።እስታይሽ ፦ ግንቦት 21/2018 ዓ.ም ...
29/05/2026

በዩኒሴፍ ዋሽ አማካኝነት ለሴት ልጅ አገረድ ተማሪዎች የተለያዩ የንፅህና መጠበቂያ ቁሳቁሶች ድጋፍ መደረጉን የጋዞ ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት አስታወቀ።

እስታይሽ ፦ ግንቦት 21/2018 ዓ.ም (ጋዞ ወረዳ ኮሙኒኬሽን )
የጽህፈት ቤቱ የሀይጅንናሳኒቴሽን ኦፊሰር የሆኑት አቶ ወንደወሰን አያሌው እንደገለፁት በዩኒሴፍ ዋሽ አማካኝነት ለእስታይሽ ሁለተኛ ደረጃ እና መሰናዶ ትምህርት ቤት ተማሪዎች የተለያዩ የንፅህና መጠበቂያ አልባሳት ቢጃማ ፣ ሞዴስ፣ አንሶላ፣ የፊትና የገላ ሳሙና ፣ ፍራሽ ናትራስ ፣ ባልዲ ፣ የውሃ መቅጃ ጀሪካ ፣ የፕላስቲክ ምንጣፍ ፣ መጋረጃ እና መስታውት ድጋፍ መደረጉን ተናግረዋል።

ኦፊሰሩ አያይዘውም የተደረገው ድጋፍም ወደ ገንዘብ ሲተመን ከ1 መቶ 70 ሺህ ብር በላይ ወጭ እንደሆነ ተናግረዋል።

ከ156 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ የተገነባው ዘመናዊ የጋዞ በግ ዝርያ ማሻሻያና የስልጠና መስጫ ማዕከልግንባታ ተጠናቆ አገልግሎት ለማስጀመር በዝግጂት ላይ መሆኑ ተገለፀ።እስታይሽ፦ግንቦት 18/2...
26/05/2026

ከ156 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ የተገነባው ዘመናዊ የጋዞ በግ ዝርያ ማሻሻያና የስልጠና መስጫ ማዕከልግንባታ ተጠናቆ አገልግሎት ለማስጀመር በዝግጂት ላይ መሆኑ ተገለፀ።

እስታይሽ፦ግንቦት 18/2018ዓ.ም(ጋዞ ወረዳ ኮሙኒኬሽን)

በሰሜን ወሎ ዞን በእንሳት ሃብት እምቅ አቅም ባላት ጋዞ ወረዳ በአማራ ክልል እንሰሳት እና ዓሳ ሃብት ልማት ቢሮ በፌዝ ተክፋፍሎ ሲገነባ የነበረው የበግ ዝርያ ማሻሻያና የስልጠና መስጫ ማዕከል ግንባታ ተጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ መሆኑን የወረዳው እንሰሳትና ዓሳ ሃብት ልማት ጽ/ቤት አስታውቋል ።

የጽ/ቤቱ ሃላፊ አቶ እውነቱ የማታው ለጽ/ቤታችን በሰጡት መረጃ ለሰሜን ወሎ ዞን በተለይም ለደጋማው ወረዳዎች በሰፊው አገልግሎት ይሰጣል ተብሎ ታስቦ በአማራ ክልል እንሰሳት እና ዓሳ ሃብት ልማት ቢሮ በ100ሄክታር መሬትላይ ከ156 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ ተደርጎ በፌዝ ተከፋፍሎ ሲገነባ የነበረው ዘመናዊ የበግ ዝርያ ማሻሻያና የስልጠና መስጫ ማዕከል ግንባታ ተጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ መሆኑን ጠቁመው ደረጃቸውን የጠበቁ የእንሰሳት ክሊኒኒኮች፣የምጥን መኖ መጋዘን፣የአጥቢና ግልገል መነጠያ በረት፣የውጭ ዝርያ በጎች በረት፣የባለሙያዎች/አስተዳደር ሰራተኞች ቢሮ እና መኖሪያ ቤት፣የውሃ ታንከሮችና መፀዳጃ ቤቶች የገነቴ ህንፃ ስራዎች ድርጅት እና እነ አሥቴር:ብርሀኑና ጓደኞቻቸው ጠቅላላ ህንፃ ሥራ ተቋራጭ ኢንተርፕራይዞች በተያዘላቸው የጊዜ ሰሌዳ መሰረትግንባታውቸውን አጠናቀው ለወረዳው እንሰሳት ሃብት ልማት ጽ/ቤት ርክክብ ማድረጉን ተናግረዋል።

እንደ አቶ እውነቱ ገለፃ የአካባቢ ማህበረሰብ በእንሰሳት እርባታ የሚተዳደር በመሆኑ መንግስት የአካባቢውን በዘርፉ የመልማት አቅም አይቶ በልዩ ትኩረት ይዞ የገነባው በመሆኑ ስራ ሲጀምር ከአካባቢው ማህበረሰብ አልፎ ለአጎራባች ወረዳዎች የበለጠ ተጠቃሚ እንደሚያደርግ የታመነበት ግንባታ በመሆኑ ክልሉ በሚሰጠው አቅጣጫ መሰረት ስራ ለማስጀመር ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል ።

አቶ እውነቱ አያይዘውም በቀጣይ እንደ መንገድና መብራት ያሉ መሰረተ ልማት ለማሟላት በሂደት ላይ መሆኑን እና በግቢው የመኖ እርሻ ጭምር ያለው በመሆኑ በትራክተር አርሶ መኖ ለመዝራትና ከዚህ ባሻገር የአካባቢውን ማህበረሰብ በማስተባበር በማዕከሉ ዙሪያ የእንሰሳት የመኖ ችግኝ ለመትከል ዝግጂት ማድረጋቸውን ገልፀዋል ።

Address

Woldia

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gazo Woreda Government Communication Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Gazo Woreda Government Communication Office:

Share