North wollo Grievance Handling /የሰሜን ወሎ ህዝብ ቅሬታ ሰሚ

  • Home
  • Ethiopia
  • Woldia
  • North wollo Grievance Handling /የሰሜን ወሎ ህዝብ ቅሬታ ሰሚ

North wollo Grievance Handling /የሰሜን ወሎ ህዝብ ቅሬታ ሰሚ Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from North wollo Grievance Handling /የሰሜን ወሎ ህዝብ ቅሬታ ሰሚ, Government Organization, North wollo, Woldia.

"ሰባተኛው ሃገራዊ ምርጫ ትላንትን የምናክምበትና ለነገ መሰረት የምንጥልበት ነው"ዲ/ን ተስፋው ባታብልላሊበላ፣ ግንቦት 14፣2018 (ላሊበላ ኮሙኒኬሽን) ብልጽግና ፓርቲ በላሊበላ ከተማ አስተ...
22/05/2026

"ሰባተኛው ሃገራዊ ምርጫ ትላንትን የምናክምበትና ለነገ መሰረት የምንጥልበት ነው"ዲ/ን ተስፋው ባታብል

ላሊበላ፣ ግንቦት 14፣2018 (ላሊበላ ኮሙኒኬሽን) ብልጽግና ፓርቲ በላሊበላ ከተማ አስተዳደር የጎዳና ላይ የምረጡኝ ቅስቀሳ አካሂዷል።

በመርሐ ግብሩ ላይ የአማራ ክልል አደጋ ስጋትና ስራ አመራር ኮምሽን ኮምሽነርና በብልፅግና ፓርቲ የቡግና ምርጫ ክልል ፣ለክልል ምክር ቤት ዕጩ ተወዳዳሪ የሆኑት ዲ/ን ተስፋው ባታብልን ጨምሮ ሌሎች የዞንና የወረዳና የከተማ አስተዳደር የስራ ሀላፊዎች ተገኝተዋል።

ብልፅግና ፓርቲ በሁሉም ዘርፍ የህዝቡን ክብርና ሉዓላዊነት የሚያስጠብቁ፣ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊትን የሚያረጋግጡና አፍሪካዊት ሃያል ኢትዮጵያን ለመገንባት የሚያስችሉ የለውጥ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ ዲ/ን ተስፋው ባታብል ተናግረዋል።

ሰባተኛው ሃገራዊ ምርጫ ትላንትን የምናክምበትና ለነገ መሰረት የምንጥልበት ነው ብለዋል ሃላፊው።

ምርጫው የኢትዮጵያን የብልፅግና ጉዞ የምናረጋግጥበት በመሆኑ ሰላማዊ፣ ዲሞክራሲያዊና ታዓማኒነት ሁኖ እንዲጠናቀቅ የህዝቡ ድርሻ ከፍተኛ መሆኑንም አስገንዝበዋል።

የብልፅግና ፓርቲ ማሳያዎቹ በግብርና ዘርፍ የታየው ለውጥ መሆኑን ያነሱት ዲ/ን ተስፋው ባታብል ይህም የህዝቡ የጥረት ውጤት መሆኑን አረጋግጠዋል።

ከዚህ ቀደም ከውጭ የምናስገባውን ስንዴ አሁን ላይ ራሳችን ለማምረት በቅተናል ያሉት ሃላፊው ይህ ስኬት የአርሶ አደሩ ድካም፣የመንግስት ድጋፍና የህዝብ ትብብር ውጤት ነውም ብለዋል።

7ኛው ሃገራዊ ምርጫ በኢትዮጵያ ታሪክ ትልቅ ምዕራፍ የምንወስንበትና የወደፊት አቅጣጫችን የምንወስንበት ወቅት መሆኑን ነው ያነሱት።

ምርጫው በጥላቻና መከፋፈል አለያም በመደመርና በአንድነት መንገድ መጓዝ እንዳለብን የምንወስንበት በመሆኑ ዛሬ የምንሰጠው ድምፅ የቀጠዩን ትውልድ ህይወት ይወስናል ብለዋል።

ምርጫችን የስሜት ሳይሆን፣የሃገር ፍቅርና፣የሰላም ፍላጎትና የልማት አስተሳሰብ መሆን እንዳለበትም ነው ያስረዱት።

ፓርቲው መሰረቱ መደመር በመሆኑ አንዱ ሌላውን ማጥፋት ሳይሆን አብሮ መኖርና ለሃገር ጥቅም በጋራ መቆም በመሆኑ ብልፅግናን እንዲመረጡ ነው የጠየቁት።

የአማራ ክልል የገጠር መንገድ ኤጀንሲ አማካሪና በብልፅግና ፓርቲ በቡግና ምርጫ ክልል ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዕጩ ተወዳዳሪው ሙሉጌታ ገብረ ማርያም ብልፅግና ፓርቲ ባለፉት አመታት በርካታ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎችን ሲሰራ ቆይቷል ነው ያሉት።

ፓርቲው የምግብ ሉዓላዊነት በማረጋገጥ፣ታላላቅ ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅና በቱሪዝም ልማት ዘርፍ በሰራው ስራ አመርቂ ውጤት ማስመዝገቡን ነው ያነሱት።

ፓርቲው ኢትዮጵያን ወደ ብልፅግና ማማ ለማድረስ እየሰራ እንደሚገኝ በማስታወስ ፓርቲውን በመመረጥ የተጀመሩ፣የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎችን ማስቀጠል ይገባል ብለዋል።

ምርጫው ሰለማዊ፣ፍትሃዊና ተአማኒ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ማህበረሰቡ የድርሻውን እንዲወጣ ነው የጠየቁት።

ብልፅግና ፓርቲ ሰው ተኮር መሆኑን ያነሱት የላሊበላ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ሃላፊና የክልል ምክርቤት ዕጩ ተወዳዳሪዋ ዮርዳኖስ መርሻ ናቸው።

የሃገራችን የማህበራዊ፣ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጉዞ ለማስቀጠልና የተጀመሩ የልማት ስራዎችን ዳር ለማድረስ ብልፅግናን እንዲመርጡ ነው የጠየቁት።

ምርጫው ፍትሃዊና ዴምክራሲያዊ እንዲሆን የሴቶች ተሳትፎ ወሳኝ ነው።ላሊበላ፣ ግንቦት 13፣2018 ( ላሊበላ ኮሙኒኬሽን) ብልጽግና ፓርቲ በላሊበላ ከተማ አስተዳደር  የምረጡኝ ቅስቀሳ አካሂዷል...
21/05/2026

ምርጫው ፍትሃዊና ዴምክራሲያዊ እንዲሆን የሴቶች ተሳትፎ ወሳኝ ነው።

ላሊበላ፣ ግንቦት 13፣2018 ( ላሊበላ ኮሙኒኬሽን) ብልጽግና ፓርቲ በላሊበላ ከተማ አስተዳደር የምረጡኝ ቅስቀሳ አካሂዷል።

ሴቶች የተሳተፉበት ብቻ የምረጡኝ ቅስቀሳ ነው በከተማ አስተዳደሩ የተካሄደው።

በመርሐ ግብሩ ላይ የላሊበላ ከተማ ከንቲባ መሳይ ወደጀን ጨምሮ ሌሎች የስራ ሀላፊዎችና የፓርቲው ደጋፊዎች ተገኝተዋል።

ምርጫ የዲምክራሲያዊ መገለጫ በመሆኑ ምርጫው ፍትሃዊና ዲሞክራሲያዊ እንዲሆን ሴቶች ወሳኝ ናቸው ያሉት ከንቲባ መሳይ ወዳጀ ናቸው።

ዴሞክራሲና ፍትህ በሌለበት የመጀመሪያዎቹ ተጠቂዎቹ ሴቶች ናቸው ያሉት ከንቲባው ሴቶ ግንቦት 24 በሚካሄደው 7ኛው ሃገራዊ ምርጫ ብልፅግናን እንዲመርጡ ነው የጠየቁት።

ብልፅግና ፓርቲ ስለወጣቶች የስራ እድል ፈጠራ፣ስለ ሴቶች ተሳትፍ ፣ስለ ሰላም የሚሰራ ፓርቲ ነው ያሉት የላሊበላ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ሃላፊና የክልል ምክርቤት ዕጩ ተወዳዳሪዋ ዮርዳኖስ መርሻ ናቸው።

ስለሴቶች አበክሮ የሚሰራውን ብልፅግና ፓርቲን በመምረጥ በድምፃችን መንግስት በመመስረት፣ ትውልድን ልንገነባ ይገባል ነው ያሉት።

ፓርቲው ኢትዮጵያን የሚገነባ ፓርቲ መሆኑን ያነሱት ሃላፊዋ ፓርቲው ዛሬንና ነገን ያስተሳሰረ ፓርቲ ነውም ብለዋል።

ሃገር የሚቆመው በመንግስት ነው ያሉት በብልፅግና ፖርቲ የቡግና ምርጫ ክክል ለህዝብ ተወካዮች ምክርቤት የሚወዳደሩት ሙሉጌታ ገብረ ማርያም (ዶ.ር)ናቸው።

ግንቦት 24 በሚካሄደው ምርጫ ብልፅግናን በመምረጥ ሃገርን ማሻገር ይገባልም ብለዋል።

የምርጫ ምልክታችን የግብርና ውጤት የሆነውና የምግብ ዋስትና ማረጋገጫችን የስንዴ ነዶን እንዲመርጡ ጠይቀዋል።

በቅስቀሳ መርሐ ግብሩ ላይ የተገኙ ሴት የፓርቲው አባላትና ደጋፊዎች ፓርቲው በሴቶች ተጠቃሚነት ያስገኛቸው ዘርፈ ብዙ ትርፋቶች የበለጠ ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ከፓርቲው ጎን መሆናቸውን አረጋግጠዋል።ምርጫው ፍትሃዊና ዴምክራሲያዊ እንዲሆን የሴቶች ተሳትፎ ወሳኝ ነው።

"ኢትዮጵያ ወደ ተምሳሌት ሀገር !"በሚል መሪ ሀሳብ በሰሜን ወሎ ዞን የላሊበላ ከተማ አስተዳደር  7ኛው ሀገራዊ ምርጫን አስመልክቶ የብልፅግና ፓርቲ የጎዳና የምረጡኝ ቅስቀሳ  እና የምርጫ ም...
19/05/2026

"ኢትዮጵያ ወደ ተምሳሌት ሀገር !"በሚል መሪ ሀሳብ በሰሜን ወሎ ዞን የላሊበላ ከተማ አስተዳደር 7ኛው ሀገራዊ ምርጫን አስመልክቶ የብልፅግና ፓርቲ የጎዳና የምረጡኝ ቅስቀሳ እና የምርጫ ምልክት የማስተዋወቅ መርሀ ግብር ተካሔደ።

''ኢትዮጵያ ወደ ተምሳሌት ሀገር !"በሚል መሪ ሀሳብ በሰሜን ወሎ ዞን በቅዱስ ላሊበላ ከተማ የብልፅግና ፓርቲ የጎዳና ላይ የምረጡኝ ቅስቀሳ በደማቅ ሁኔታ ተካሄደ

(‎ቅዱስ ላሊበላ ከተማ -ግንቦት:-11/2018 ዓ,ም)

የቅዱስ ላሊበላ ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የፓርቲውን ምልክት እና ዕጩዎች በጎዳና ላይ ለህዝቡ በማስተዋወቅ የምረጡኝ ቅስቀሳ አድርጓል ።

#ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር!
#ምልክታችን _የስንዴ ነዶ ነው!
#ግንቦት 24/2018 ለሚካሄደው ምርጫ ብልፅግና ፓርቲን ይምረጡ

15/05/2026
13/05/2026
13/05/2026
13/05/2026
13/05/2026

አንጻራዊ ሰላም መኖሩ በላሊበላ ከተማ የቱሪዝም እንቅስቃሴው እንዲነቃቃ አድርጓል።

ባሕር ዳር: ግንቦት 05/2018 ዓ.ም (አሚኮ) ዓይኖች በስስት ይመለከቱታል፤ የሰው ልጅ የኪነ ጥበብ በረከት በሕያው ምስክርነት ተቀምጦበታል፤ ጎብኝዎች በረከትንና የመንፈስ እርካታን ይዘው ይመለሱበታል፤ የቅዱስ ላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት።

የላሊበላ ከተማ ነዋሪዎች ቅርሱን ለመጎብኘት የሚመጡ እንግዶችን እግር አጥበው እና በፍቅር ተቀብለው በጎብኝዎች ላይ ድንቅ ትውስታን ፈጥረው ይልካሉ።

በሰሜኑ ጦርነት እና በክልሉ ባጋጠመው ግጭት ምክንያት ላሊበላ ከተማ ጎብኝ ናፍቋት ቆይቷል። ነዋሪዎቹም በፍቅር የሚቀበሉት፤ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴን የሚያሳልጥላቸውን ጎብኝ በራቸውን ከፍተው፤ እጃቸውን ዘርግተው ጠብቀዋል።

የመንግሥት የሰላም ጥሪ እና የታጣቂዎች የሰላም አማራጭን መቀበል ደግሞ የከተማዋን ነዋሪዎች እንደ ጥዋት ጀምበር ገጻቸውን አፍክቷል።

በከተማዋ አንጻራዊ ሰላም መፈጠሩ የቱሪዝም እንቅስቃሴው ላይ መነቃቃትን በመፍጠሩ ዳግም የኢኮኖሚ እንቅስቃሴው እንዲነቃቃ አድርጓል።

የላሊበላ ከተማ አሥተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ መሳይ ወዳጀ የቱሪዝም እንቅስቃሴው መነቃቃት እያሳየ መኾኑን ተናግረዋል።

በአካባቢው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ታጣቂዎች የሰላም አማራጭን መቀበላቸው የአካባቢው ቱሪዝም እንዲነቃቃ ዕድል ፈጥሯል ብለዋል።

የቱሪዝም ፍስሰቱ መሻሻል እያሳየ ቢኾንም እንኳ የቆይታ ጊዜያቸውን ለማራዘም እና የአካባቢው የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ የተሻለ እንዲኾን እየተሠራ መኾኑንም አንስተዋል።

ሰላም እና ቱሪዝም የማይነጣጠሉ በመኾናቸው ሰላምን ይበልጥ በማጽናት ማኅበረሰቡ ከቱሪዝም ልማት ይበልጥ ተጠቃሚ ሊኾን እንደሚገባም ገልጸዋል።

በከተማዋ በተፈጠረው አንጻራዊ ሰላም ማኅበረሰቡን የልማት ተጠቃሚ ለማድረግ የተለያዩ መሠረተ ልማቶች እየተገነቡ እንደኾነም አንስተዋል።

ዘጋቢ:- ያየህ ፈንቴ

የአሚኮ ዲጅታል ቤተሰብ ይሁኑ

https://linktr.ee/Amharamediacorporations

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን !

Address

North Wollo
Woldia

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when North wollo Grievance Handling /የሰሜን ወሎ ህዝብ ቅሬታ ሰሚ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share