14/08/2026
በዛሬው እለት ማለትም ነሃሴ 08 ቀን 2018 ዓ.ም በአብክመ ንግድ እና ገበያ ልማት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ (በአቶ ፈንታው ፈጠነ) የተመራ የሰሜን ወሎ ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ እና የወልደያ ከተማ አስተዳደር ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ አላማ ፈፃሚ ባለሙያዎችን ያካተተ በወልዲያ ከተማ ከንቲባ ህንፃ አዳራሽ የጋራ ውይይት ተካሄደ።
የውይይቱ አጀንዳዎች
1. የ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርት በሁለቱም መምሪያዎች ቀርቦ በታዳሚዎች ውይይት ተደርጎበታል።
2. የቀጣይ የ2019 በጀት አመት አቅጣጫ በአምስቱ ስትራቴጅክ ግቦች ላይ መሰረት በማድረግ በአቶ ፈንታው ፈጠነ ቀርቦ ውይይት ተደርጓል። እነዚህም ግቦች
የኑሮ ዉድነትን በማረጋጋት በጀት በመመደብ አቅርቦትን ማሳደግ
ህገ-ወጥ የንግድ አሰራርን በመከላከል የግብይት ስርአቱን ከደላላ የጸዳ ማድረግ
ዘመናዊ የገበያ ማእከላትን በመገንባት የተለያዩ የሰብልና የኢንደስትሪ ሞርቶችን በማቅረብ የገበያ ተደራሽነትን ማሳደግ
የአገልግሎት አሰጣጥን በማሻሻል ከሽንገላ እና ከሙስና የጸዳ እንዲሆን ማድረግ
የተቀላጠፈ የቴከኖሎጂ አገልግሎት መስጠት መሰረታዊ ሃሳቦች ላይ በመመርኮዝ ከቤቱ በርካታ ሃሳቦች፣ አስተያየቶችና በስራ ላይ ያጋጠሙ ችግሮች ተነስተው በሰፊው ውይይት በማድርግ እና የመፍትሄ አቅጣጫ በማስቀመጥ የ2019 ዋነኛ የመነሻና የመስፈንጠሪያ ነጥብ መሆኑን በመረዳት ከወልዲያ ከተማ አስተዱደር ጋር በመቀናጀት የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ሁሉም አላማ ፈጸሚ ባለሙያ እርብርብ ለማድረግ ቃል በመግባት ዉይይቱ ተጠናቋል።