02/07/2026
ቱሪዝም ኢኮኖሚ የሚሆነው በዘርፉ ግብይት ሲፈጠር ነው
ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ
ለጎብኚዎች የሚሰጡ አገልግሎቶችን ለማስፋት አዲስ አበባ ውስጥ በርከት ያሉ ሞሎች እየተገነቡ እንዳሉና አራት ሞሎች በሚቀጥለው ዓመት ሥራ ይጀምራሉ ተብሎ ይጠበቃል። ቱሪዝም ኢኮኖሚ የሚሆነው በዘርፉ ግብይት ሲፈጠር ነው፡፡ በቱሪዝም መዳረሻዎች አካባቢ ለቱሪስቶች የሚሆን ምግብ፣ ቡና፣ ቅርጻቅርፆች፣ አልባሳት እንዲሁም ሱቆች መኖር እንዳለባቸው፡፡
ጎብኝዎች መጥተው የቱሪስት መዳረሻ ስፍራዎችን አይተው መሄዳቸው ብቻውን ቱሪዝምን ስለማያነቃቃ አንድ ጎብኚ ልቡ ተደስቶ፣ ተዝናንቶ ይዞ የመጣውን ወጪም አውጥቶ መሄድ አለበት፡፡ ለዚህም የሞሎችና የሱቆች ግንባታ በጣም አስፈላጊ በመሆኑ አዲስ አበባ ላይ በርከት ያሉ ሞሎች እየተገነቡ ነው ሶስት አራት የሚጠጉ ሞሎች በሚቀጥለው ዓመት ሥራ ይጀምራሉ ይጠበቃል፡፡
ኢትዮጵያ ውስጥ እየተሰሩ ያሉ ሞሎች በጥራት ደረጃ በዓለም ጥሩ የሚባሉ ናቸው እነዚህ ስራ ሲጀምሩም ሞል አልባ ከነበረው በመነሳት አፍሪካ ውስጥ የተሻለ ሞል ካላቸው ሃገራት ተርታ ያስገባናል። በኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች ትላልቅ ለቱሪዝም መዳረሻ የሚሆኑ ፕሮጀክቶች እየተሰሩ ነው። በዚህም የቱሪዝም ዘርፉ እየተነቃቃ ሲሆን ይሄም የዜጎች፣ የግል ዘርፉ እንዲሁም የብዙ ሰዎች የሃብት እና የዕውቀት ድምር ውጤት ናት።