Gurage Zone Abeshige Woreda Communication affairs office

Gurage Zone Abeshige Woreda Communication affairs office Abeshige woreda government communication affairs dep't!

በምርጫ ሂደት ውስጥ የአባላት ሚና የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን ለማረጋገጥና የሀገርን ቀጣይ አቅጣጫ ለመወሰን እጅግ ወሳኝ እንደሆነ ተገለፀ።ግንቦት 6/2018 ዓ.ም (ወልቂጤ)በአበሽጌ ወረዳ ...
14/05/2026

በምርጫ ሂደት ውስጥ የአባላት ሚና የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን ለማረጋገጥና የሀገርን ቀጣይ አቅጣጫ ለመወሰን እጅግ ወሳኝ እንደሆነ ተገለፀ።

ግንቦት 6/2018 ዓ.ም (ወልቂጤ)

በአበሽጌ ወረዳ ገቢዎች እና ንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤት በጋራ በመሆን የብልፅግና ፓርቲ ቤተሠብ አባላት የቡና ጠጡ ፕሮግራም አካሄዱ።

ለ7ኛው ዙር ሀገራዊ እና ክልላዊ ምርጫ እጩዎችን ለማስተዋወቅ እና የምረጡ ቅስቀሳ በተዘጋጀው ፕሮግራም ላይ ብልጽግና ፓርቲን ወክሎ የቀረቡ እጩዎችን እና የምርጫ ምልክት የማስተዋወቅ መርሃ-ግብር ተካሄዷል።

የመርሃ-ግብሩ ዋነኛው ዓላማው መጪው 7ኛው ዙር ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ፍፁም ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ተዓማኒ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ሁሉም አባል የበኩሉን መወጣት እንደሚገባው ተገልጿል።

''ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር'' በሚል መሪ ሀሳብ የ7ኛው ዙር ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ የብልጽግና ፓርቲ መወዳደሪያ ምልክት፤ የፓርቲው የምርጫ ማኒፌስቶ እና እጩዎችን የማስተዋወቅ ተግባር ተከናውኗል።

ብልጽግና ፓርቲ በባለፉት ዓመታት የተለያዩ ፈተናዎችን በድል በማሻገር ዘርፈ ብዙ ተግባራትና በርካታ ትሩፍቶች ለህዝቡ ተጠቃሚነትና ተደራሽነት ከማትረፉ በዘለለ ብዙ የተሞክሮ ተምሳሌቶችን ያተረፈ መሆኑን በመርሃ-ግብሩ ተብራርቷል።

​በመድረኩም 7ኛው ዙር ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ስኬታማ እንዲሆን በየደረጃ የሚገኙ የሁሉም አባላት ሚና ከፍተኛ መሆኑ ተጠቅሶ ቀጣይ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን ለማረጋገጥ በዘርፉ ብዙ ተግባራት ላይ አባላት ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርጉ መልዕክት ተላልፏል።

በመርሃ-ግብሩም የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ካሡ ጁሀር ፣ የወረዳው ም/ዋና አስተዳዳሪና ንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ቢኒያም ጥላሁን ፣ የወረዳው ገቢዎች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፋንታሁን ብርሀን ፣ የሁለቱም ጽ/ቤቶች የፓርቲው አባላት ተሳትፈዋል።

ዘገበው የአበሽጌ ወረዳ የመንግስት ኮ/ጉ/ጽ/ቤት ነው

‎ፔጃችን ስለምትከታተሉ እያመሰገንን ለተጨማሪ መረጃዎች የተቋማችን የሚዲያ አማራጮችን ይጠቀሙ፡-
‎‎👉://www.facebook.com/profile.php?id=100070918473865&mibextid=kFxxJD

‎👉http://tiktok.com/

‎👉 ቴሌግራም፦ https://t.me/awc567

‎👉 ዩቲዩብ:- https://youtube.com/?si=8HvFtXplAUMiEnmx

‎👉 instagram :-
https://www.instagram.com/abeshigeworeda?igsh=MjQyMXN5bnhkb2d2

‎👉X
https://x.com/AWoreda5717?t=x9hbuUQi9Esw9XahIjQkWQ&s=09

ዛሬ የምንናገረው ተስፋ ብቻ አይደለም እጅ በአፍ የሚያስጭኑ፣የጠላቶቻችን አንገት ያስደፉ ድሎችን ይዘን ነው ።
14/05/2026

ዛሬ የምንናገረው ተስፋ ብቻ አይደለም እጅ በአፍ የሚያስጭኑ፣የጠላቶቻችን አንገት ያስደፉ ድሎችን ይዘን ነው ።

በአበሽጌ ወረዳ ላቼና ኦማንቾ ቀበሌ ከማድ ቤት በተነሳ የእሳት ቃጠሎ ንብረት መውደሙ ተገለጸ። ‎‎ወልቂጤ ፣ ግንቦት 6/2018፣ በጉራጌ ዞን አበሽጌ ወረዳ ላቼና ኦማንቾ ቀበሌ ከማድ ቤት በ...
14/05/2026

በአበሽጌ ወረዳ ላቼና ኦማንቾ ቀበሌ ከማድ ቤት በተነሳ የእሳት ቃጠሎ ንብረት መውደሙ ተገለጸ።

‎ወልቂጤ ፣ ግንቦት 6/2018፣ በጉራጌ ዞን አበሽጌ ወረዳ ላቼና ኦማንቾ ቀበሌ ከማድ ቤት በተነሳ የእሳት ቃጠሎ ንብረት መውደሙ ተገለጸ።

በቃጠሎው ሶስት ሳር ቤት፣በጥሬ 50 ሺህ ብር እንዲሁም እህልና የቤት ውስጥ ቁሳቁስ መውደሙ ከቀበሌው ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

ትናንት ከቀኑ ረፋድ አካባቢ የተነሳው የእሳት ቃጠሎ በህብረተሰቡ ተሳትፎ ወደ ሌሎች አካባቢዎች ሳይዛመት በቁጥጥር ስር ማዋል የተቻለ ሲሆን በሰው ህይወት ላይ የደረሰ አደጋ የለም።

በአደጋው በአጠቃላይ 2 ሚሊዮን የሚገመት ሃብት መውደሙ የተገለፀ ሲሆን ወቅቱ ደረቅና ነፋሻማ በመሆኑ መሰል ችግሮች እንዳይፈጠሩ ማህበረሰቡ አስፈላጊውን ጥንቃቄ ማድረግ እጅግ አስፈላጊ ነው።

‎ፔጃችን ስለምትከታተሉ እያመሰገንን ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ከታች የተቀመጡትን ሊንኮች በመጫን የተቋማችን የሚዲያ አማራጮችን ይጠቀሙ፡-
‎‌👉://www.facebook.com/profile.php?id=100070918473865&mibextid=kFxxJD

‎👉http://tiktok.com/

‎👉 ቴሌግራም፦ https://t.me/awc567

‎👉 ዩቲዩብ:- https://youtube.com/?si=8HvFtXplAUMiEnmx

‎👉 instagram :-
https://www.instagram.com/abeshigeworeda?igsh=MjQyMXN5bnhkb2d2

‎👉X
https://x.com/AWoreda5717?t=x9hbuUQi9Esw9XahIjQkWQ&s=09

የአበሽጌ ወረዳ ባህልና ቱሪዝም ጽህፈት ቤት ባለፉት አምስት ዓመታት የጉራጌን ባህል፣ ቋንቋና የቱሪስት መስህቦች ለማልማትና ለማስተዋወቅ በርካታ ስኬታማ ተግባራትን ማከናወኑን የጽ/ቤቱ ኃላፊ ...
14/05/2026

የአበሽጌ ወረዳ ባህልና ቱሪዝም ጽህፈት ቤት ባለፉት አምስት ዓመታት የጉራጌን ባህል፣ ቋንቋና የቱሪስት መስህቦች ለማልማትና ለማስተዋወቅ በርካታ ስኬታማ ተግባራትን ማከናወኑን የጽ/ቤቱ ኃላፊ ገለጹ።

ወልቂጤ ፣ግንቦት 5/2018 ዓ.ም በጉራጌ ዞን የአበሽጌ ወረዳ ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ መንግስቱ ሺነካ እንደገለፁት በዋናነት ትኩረት ከተደረገባቸው ተግባራት መካከል የባህል እሴቶችን መጠበቅ፣ የቱሪስት መዳረሻዎችን ማልማትና የቋንቋውን ተጠቃሚነት በማሳደግ የተገኙ ውጤቶችም ለወረዳው ሁለንተናዊ እድገት ፋይዳቸው የጎላ ነው።

ወረዳው የባህል እሴቶችን ለማነቃቃት ባከናወነው ተግባር አመታዊ የባህል በዓላት የሆኑት የመስቀል፣ የአንትሮሽት (የእናቶች ቀን) እና የነቆ (የልጃገረዶች) በዓላት በተለያዩ ቀበሌዎች በድምቀት እንዲከበሩ ማድረጉ ገልፀዋል።

ከዚህም ባለፈ የጉራጌን ማንነት የሚያንፀባርቁ የባህል አልባሳት ለወረዳ አመራሮችና ለቋሚ ኮሚቴዎች ግዥ ተፈጽሞ ጥቅም ላይ እንዲውሉ መደረጉን አቶ መንግሥቱ ጠቅሰዋል።

በአካባቢው የተከሰቱ የጸጥታ ችግሮችን በመፍታት ረገድም የጉራጌ ባህላዊ የግጭት አፈታት ስርአት የሆነው የ"ጆካ" ሽምግልና ትልቅ ሚና እንዲጫወት ተደርጓል ያሉ ሲሆን በተደጋጋሚ በተዘጋጁ የሽምግልና መድረኮች የጸጥታ ችግሮች ወደ ከፋ ደረጃ እንዳይደርሱና በአካባቢው ሰላም እንዲሰፍን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱ ተጠቁሟል።

የገጠር ኮሪደር ልማትን ለማፋጠን ታቅዶ እየተሰራ ያለው የጀፎረ ልማት ፕሮጀክት አንዱ ስኬት መሆኑ ገልፀው በ2017 እና 2018 ዓ.ም በድምሩ 35 ኪሎ ሜትር ለመስራት ታቅዶ እስካሁን ባለው ሂደት 31.5 ኪሎ ሜትር የሚሆነውን ማልማት መቻሉን አብራርተዋል

በተጨማሪም በወረዳው የሚገኙ ተፈጥሯዊ የቱሪስት መዳረሻዎችን ይበልጥ ሳቢ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል ያሉት ሃላፊው በዚህም በገራባ የሚገኘው ያንካደን ፏፏቴ፣የዋልጋ ፏፏቴ፣አቾ ፏፏቴ እና
ዳርጌ ፏፏቴ ወደ ቱሪስት መዳረሻነት ለመቀየር ታቅዶ ሰፊ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑ ተገልጿል።

ለዘርፉ ስኬታማነትም ለቱሪስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ባለቤቶችና ሰራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናዎችም መስጠቱን አብራርተዋል።

የጉራጌኛ ቋንቋን የትምህርት፣ የሥራና የሚዲያ ቋንቋ ለማድረግ የተጀመሩ ስራዎች አበረታች መሆናቸውን የገለጹት ኃላፊው፤ ለዚህም ስኬት የሚተጋ የቴክኒክ ኮሚቴ መቋቋሙን ተናግረዋል።

ከዚህ ጋር ተያይዞም በርካታ እንቆቅልሾች፣ ተረቶችና ምሳሌያዊ አነጋገሮች ተሰብስበው ወደ አማርኛ ተተርጉመዋል ብለዋል።

በቅርሶች ላይ የሚደርሰውን ጉዳት ለመቀነስ የጥበቃና የእንክብካቤ ስራዎች ተከናውነዋል ያሉ ሲሆን ባህላዊ መድሃኒቶችን የመሰብሰብና ለሚመለከታቸው ተቋማት ተደራሽ የማድረግ ስራ መሰራቱን አብራርተው በእደ-ጥበብ ለተሰማሩ ማህበራት ሙያዊ ድጋፍና ክትትል መደረጉን ገልፀዋል።

በቀጣይም በአሁኑ ወቅት ጊዜያዊ የባህል ቤት ተገንብቶ ተበታትነው የነበሩ የባህል እቃዎች ተሰብስበው በአግባቡ እንዲቀመጡና በቀጣይ ወረዳውን ሊመጥን የሚችል ዘመናዊ የባህል ቤት ግንባታ ለማከናወን መታቀዱን ገልፀዋል።

ለዚህም የሚሆን የፕሮጀክት ፕሮፖዛል በየዓመቱ እየተዘጋጀ ለሚመለከታቸው አካላት ተደራሽ እየተደረገ መሆኑን ገልፀው በአጠቃላይ የወረዳው አስተዳደር ለዘርፉ በሰጠው ከፍተኛ ትኩረት የጉራጌ ባህልና ቋንቋ ከምንጊዜውም በላይ እያደገ መምጣቱን ኃላፊው ጨምረው ገልጸዋል።

ዘገባው የወረዳው መንግስት ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው

ፔጃችን ስለምትከታተሉ እያመሰገንን ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ከታች የተቀመጡትን ሊንኮች በመጫን የተቋማችን የሚዲያ አማራጮችን ይጠቀሙ፡-

‎‎👉://www.facebook.com/profile.php?id=100070918473865&mibextid=kFxxJD

‎👉http://tiktok.com/

‎👉 ቴሌግራም፦ https://t.me/awc567

‎👉 ዩቲዩብ:- https://youtube.com/?si=8HvFtXplAUMiEnmx

‎👉 instagram :-
https://www.instagram.com/abeshigeworeda?igsh=MjQyMXN5bnhkb2d2

‎👉X
https://x.com/AWoreda5717?t=x9hbuUQi9Esw9XahIjQkWQ&s=09

የጥቁር ሕዝቦች ድምፅ በተመድ አዳራሽ - ኢትዮጵያ ለነፃነት የከፈለችው ዲፕሎማሲያዊ ዋጋ******************** (የዕለቱ መልዕክት) ኢትዮጵያ እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ያላቸ...
14/05/2026

የጥቁር ሕዝቦች ድምፅ በተመድ አዳራሽ - ኢትዮጵያ ለነፃነት የከፈለችው ዲፕሎማሲያዊ ዋጋ
********************

(የዕለቱ መልዕክት)

ኢትዮጵያ እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ያላቸው ትሥሥር እንደ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ብቻ የሚታይ ሳይሆን፣ በታሪክ አውድማ ላይ በፅናት እና በሉዓላዊነት የተገመደ የክብር ሰንሰለት ነው።

ከሰማንያ ዓመታት በፊት ዓለም በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ፍርስራሽ ላይ ቆማ አዲስ ተስፋን ስትፈልግ፣ ኢትዮጵያ ከ51ዱ መሥራች ሀገራት መካከል አንዷ ሆና የቻርተሩን ሰነድ ስትፈርም ተራ ተሳታፊ አልነበረችም።

ይልቁንም፣ የዲፕሎማቶቻችን ድምፅ የኃያላንን የበላይነት ለመሞገት እና የደካማ ሀገራትን መብት ለማስጠበቅ የሚተጋ የፍትሕ ጩኸት ነበር።

በወቅቱ በቅኝ ግዛት ቀንበር ሥር ለነበሩት ወንድም የአፍሪካ እና የእስያ ሕዝቦች፣ ኢትዮጵያ ብቸኛ የነፃነት እና የራስን ዕድል በራስ የመወሰን መብት ተሟጋች ሆና መቅረቧ፣ “ለራስ ሲቆርሱ አያሳንሱ” የሚለውን ብሂል ወደ ጎን በመተው ለሰው ልጅ ሁሉ ነፃነት መቆሟን ያሳየ ታላቅ የሞራል ልዕልና ነበር።

ይህ የታሪክ አሻራ ዛሬም በደማቅ ቀለም እየተጻፈ ይገኛል። ኢትዮጵያ ላለፉት ሰማንያ ዓመታት በሚጠጋ ጊዜ ውስጥ ከ100 ሺህ በላይ የሰላም ዘቦችን በተለያዩ የዓለም ክፍሎች በማሠማራት፣ በዓለም ሰላም ማስከበር ሂደት ውስጥ ያላትን የማይናወጥ ሚና በተግባር አሳይታለች።

የሀገራችን ሠራዊት በሄደበት ሥፍራ ሁሉ የሚታወቅበት የጥንካሬ፣ የዲሲፕሊን እና የሕዝባዊነት ገጽታ፣ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሰላም አስከባሪ ሠራዊት ከሚያዋጡ ሀገራት ግንባር ቀደም ተጠቃሽ አድርጓታል። ይህ መሥዋዕትነት ለራሳችን ብቻ ሳይሆን ለጎረቤቶቻችን እና ለመላው ዓለም ሰላም መቆማችንን የሚያረጋግጥ የቆራጥነት ማሳያ ነው።

በተመድ እና በአፍሪካ ኅብረት ጥላ ሥር የሚከናወኑት እነዚህ ተልዕኮዎች፣ የኢትዮጵያን የሰላም አምባሳደርነት በዓለም አደባባይ ከፍ አድርገውታል።

ዛሬ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ አዲስ አበባን በተደጋጋሚ መጎብኘታቸው እና የድርጅቱን 80ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል እዚህ በታሪካዊቷ ከተማችን እንዲከበር መወሰኑ፣ እንዲሁ የተገኘ ድንገተኛ ክስተት አይደለም። ይህ ውሳኔ ኢትዮጵያ ለድርጅቱ ያበረከተችው ታሪካዊ አስተዋፅኦ እና ለዓለም ሰላም የከፈለችው መሥዋዕትነት የተሰጠው ታላቅ እውቅና ነው።

“መልካም ስም ከመቃብር በላይ ይውላል” እንዲሉ፣ የሀገራችን የዲፕሎማሲ ጥንካሬ እና የሠራዊታችን አኩሪ ገጽታ ለስምንት ዐሥርተ ዓመታት ተጠብቆ ቆይቶ ዛሬም በዓለም መድረክ ድምፃችን ጎልቶ እንዲሰማ አድርጎታል።

ይህም የአፍሪካን ዳግም መነሣት የሚያበስር ምልክት እና ለጋራ ብልጽግና የምታደርገውን ጉዞ የሚያፋጥን የጥንካሬ ምሰሶ ነው።

ኢትዮጵያ እና ተመድ በዘላቂ ልማት ግቦች ዙሪያ ያላቸው ትብብርም ሌላው የትሥሥሩ ገጽታ ነው። ድህነትን ለማጥፋት፣ ፕላኔቷን ለመጠበቅ እና ለሁሉም ሰው ሰላምን ለማረጋገጥ የሚደረገው ጥረት፣ ሀገራችን ከድርጅቱ ጋር ያላትን ስትራቴጂክ አጋርነት ይበልጥ ያጠናክረዋል።

ወደፊትም ቢሆን ኢትዮጵያ የድርጅቱ ደጀን እና የልማት ተምሳሌት ሆና በመቀጠል፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ፍትሐዊ ሥርዓት እንዲሰፍን እና የጋራ ብልጽግና እንዲረጋገጥ የነበራትን የሞራል መሪነት አጠናክራ እንደምትቀጥል ጥርጥር የለውም።

የታሪካችን ጥንካሬ እና የሠራዊታችን ፅናት ዛሬም ለዓለም ሰላም ዋስትና፣ ለትውልድም ኩራት ሆኖ ይቀጥላል።

የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል

‎የጉራጌ ዞን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አዲስ አመራሮችን መረጠ፤ ወቅታዊ የምርጫ ጉዳዮች ላይም ምክክር አደረጓል።ግንቦት 05/2018 (ወልቂጤ)‎‎የጉራጌ ዞን የፖለቲካ ፓርቲዎች የ...
13/05/2026

‎የጉራጌ ዞን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አዲስ አመራሮችን መረጠ፤ ወቅታዊ የምርጫ ጉዳዮች ላይም ምክክር አደረጓል።

ግንቦት 05/2018 (ወልቂጤ)

‎የጉራጌ ዞን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ባካሄደው አስቸኳይ ጉባኤ፣ ክፍት የነበሩ የአመራር ቦታዎችን በዴሞክራሲያዊ ምርጫ በአዲስ አመራሮች መተካቱንና በወቅታዊ የምርጫ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት ማድረጉን አስታወቀ።

‎በዚሁ መሠረት የምክር ቤቱ በአዲስ የተተኩ አመራሮች፦

‎1. አቶ አበበ ያበኬር — ሰብሳቢ
‎2. አቶ ናስር ሀሰን — ምክትል ሰብሳቢ
‎3. ዶ/ር አብዱላዚዝ ሙሰማ — ፀሐፊ ሆነው ተመርጠዋል።

‎በጉባኤው ላይ የታደሙት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ደምስ ገብሬ፣ ሂደቱ ፍጹም ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ መጠናቀቁን ገልጸው፤ እንዲህ ዓይነት አሰራሮች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው አሳስበዋል።

በየደረጃው ያሉ የጋራ ምክር ቤቶች በፓርቲዎች መካከል የሚፈጠሩ ልዩነቶችንና ችግሮችን በውይይት የሚፈቱ "ችግር ፈቺ" ተቋማት ሊሆኑ እንደሚገባም አክለዋል።

‎የክልሉ ብልፅግና ፓርቲ የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊና የክልሉ የጋራ ምክር ቤት ምክትል ሰብሳቢ አቶ በረከት ከድር በበኩላቸው፤ ምርጫ የዴሞክራሲ መገለጫ መሆኑን ጠቅሰው፣ በሂደቱ የሚገጥሙ ማናቸውም ችግሮች በጋራ ምክር ቤቱ ደንብና መመሪያ መሠረት ምላሽ ማግኘት እንዳለባቸው ገልጸዋል።

የጉራጌ ዞን የጋራ ምክር ቤትን በክልሉ "ሞዴል" ለማድረግ የተጀመረው ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ጠቁመዋል።

‎የዞኑ ዋና የመንግስት ተጠሪና የምክር ቤቱ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ናስር ሀሰን እንደገለጹት፤ ምክር ቤቱ በቀጣይ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታን ለማጠናከር በትኩረት የሚሰራ ሲሆን፣ ማናቸውም ቅሬታዎችና ችግሮች ሲያጋጥሙ በቀጥታ ለጋራ ምክር ቤቱ ቀርበው መፍትሄ እንዲያገኙ ይደረጋል ብለዋል።

‎ምርጫው ፍፁም ሰላማዊ ዴሞክራሲያዊ እና ፍትሀዊ እንዲሆን ጠንካራ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን የገለፁት አቶ ናስር ይህ ሂደት የሁሉንም ፖርቲዎች መተጋገዝ ይጠይቃል ብለዋል።

‎የምክርቤቱ ሰብሳቢ አቶ አበበ ያበኬር በበኩላቸው፤ ምክር ቤቱን በአዲስ መንፈስና በቁርጠኝነት ለመምራት መዘጋጀታቸውን ገልጸው፣ ለስራው ውጤታማነት ደግሞ ወቅታዊና ፈጣን የመረጃ ልውውጥ ወሳኝ መሆኑን አስገንዝበዋል።

‎የጋራ ምክር ቤቱ ፀሐፊ ዶ/ር አብዱላዚዝ ሙሰማ፤ ፓርቲዎች የምርጫ ህግንና ስርዓትን አክብረው መንቀሳቀስ እንዳለባቸውና ቀጣይነት ያለው ግንኙነት ሊኖራቸው እንደሚገባ አሳስበዋል።

‎በምርጫ ቅስቀሳ ወቅት ሊስተካከሉ የሚገቡ የምርጫ ስነ-ምግባር ጉድለት የሚታዩ መሆኑን ጠቅሰው፣ እነዚህም በአስቸኳይ ሊታረሙ እንደሚገባው አሳስበዋል።

‎በመጨረሻም የጋራ ምክር ቤቱ አመራሮች በወልቂጤ ከተማ እየተገነባ ያለው ግዙፍ የዞኑ አስተዳደር ህንፃ የስራ እንቅስቃሴ የጎበኙ ሲሆን፣ በህንፃውና እየተከናወኑ ባሉ ስራዎች መደሰታቸውን ገልጸዋል።

‎በጉባኤው ከብልፅግና፣ ከኢዜማ፣ ከጎጎት፣ ከወህዴፓ እና ከነእፓ የፓርቲ ተወካዮች ተሳትፈዋል ሲል የጉራጌ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ዘግቦታል።

‎በአበሽጌ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት የ2019 በጀት ዓመት የዜጎች ቅድመ በጀት ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተካሄደ::ግንቦት 5/2018 ዓ.ም (ወልቂጤ)በጉራጌ ዞን አበሽጌ ወረዳ ፋይናንስ ...
13/05/2026

‎በአበሽጌ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት የ2019 በጀት ዓመት የዜጎች ቅድመ በጀት ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተካሄደ::

ግንቦት 5/2018 ዓ.ም (ወልቂጤ)

በጉራጌ ዞን አበሽጌ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት የ2019 በጀት ዓመት የዜጎች ቅድመ በጀት ውይይት ከባለድርሻ አካላት ጋር አካሄደ::

‎የአበሽጌ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ አዳነች መልሴ እንደተናገሩት የዜጎች የቅድመ በጀት ውይይት የመንግስትን የወጪና የገቢ ዕቅድ በማሳወቅ፣ በጀት ከመጽደቁ በፊት የህዝቡን ሀሳብና አስተያየት በመሰብሰብ ተሳትፎን የሚያጎለብት መድረክ ነው ብለዋል፡፡

አክለውም ግልጽነትን፣ ተጠያቂነትንና የበጀት ፍትሃዊነትን ለማረጋገጥ የሚረዳ ነው ያሉት ኃላፊዋ ከወረዳ እስከ ቀበሌ ባሉ መዋቅሮች የዕቅድ አፈጻጸምና ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ተግባራት ላይ ውይይት ይደረጋል ያሉ ሲሆን የበጀት አጠቃቀምን ውጤታማነት ከፍ በማድረግ የሚመደበው በጀት የወረዳችንን ሕዝብ ተጠቃሚነት በሚያረጋግጡ የካፒታል ፕሮጀክቶችና በማኅበራዊ አገልግሎቶች ላይ ትኩረት እንዲያደርግ ይደረጋል ያሉ ሲሆን

ዜጎች በበጀት ሂደቶች ሁሉ የባለቤትነት ስሜት ሊኖራቸው እንደሚገባም ገልፀዋል፡፡

የ2019 በጀት ዓመት የበጀት ረቂቅ ዝግጅትን አስመልክቶ በቀረበው መወያያ ሰነድ እንደገለፁት በጀቱ የወረዳውን የልማት ፍላጎትና የመንግሥት የትኩረት አቅጣጫዎች መሠረት ያደረገ መሆኑንም ገልጸዋል።

አክለውም፣ ለ2019 በጀት ዓመት የሚመደበው በጀት በወረዳው እየተፈታ ያለውን የልማትና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን የበለጠ የሚቀርፍ ይሆናል፡፡

የፋይናንስ ጽ/ቤት የበጀት ባለሙያ ፍሬወርቅ ከማል በበኩላቸው የ2018 በጀት ዓመት የ9 ወር የገቢና የወጪ አፈጻጸም፣ የፋይናንስ ግለፀኝነትና ተጠያቂነት የተመለከተ ሰነድ እና የ2019 በጀት ዓመት የቅድመ በጀት ሰነድ አቅርበዋል።

በሰነዱ ላይ ሰፊ ውይይት የተደረገ ሲሆን በውይይቱም ተሳታፊ የነበሩ ባለድርሻ አካላትም በሰነዱ ላይ ሃሳባቸውን አስቀምጠዋል፡፡ የህዝቡ ተጠቃሚነትን ያረጋገጠ ዘላቂ ልማትን ማረጋገጥ እንደሚገባም ተጠቁመዋል።

እንዲሁም ውስን የሆነውን ሀብት ያለብክነት በመጠቀም ቅድሚያ ትኩረት ለሚሰጣቸው የልማት ሥራዎች እንዲውል የተባለ ሲሆን በጀቱን ለመሸፈን የወረዳውን የውስጥ ገቢ አሰባሰብ አቅም ማሳደግና ሌሎች የፋይናንስ ምንጮችን መጠቀም አስፈላጊ መሆኑ ተነስቷል።

በመጨረሻም የተበጀተን በጀት ለታለመለት ዓላማ ለማዋል ገቢን በአግባቡ ከመሠብሰብ እስከ አጠቃቀሙ ድረስ ውጤታማ ለማድረግ የሁሉም ባለድርሻ አካላት ርብርብ እንደሚያስፈልግም ተቀምጧል።

ዘገባው የአበሽጌ ወረዳ መንግስት ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው።

ፔጃችን ስለምትከታተሉ እያመሰገንን ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ከታች የተቀመጡትን ሊንኮች በመጫን የተቋማችን የሚዲያ አማራጮችን ይጠቀሙ፡-

‎‎👉://www.facebook.com/profile.php?id=100070918473865&mibextid=kFxxJD

‎👉http://tiktok.com/

‎👉 ቴሌግራም፦ https://t.me/awc567

‎👉 ዩቲዩብ:- https://youtube.com/?si=8HvFtXplAUMiEnmx

‎👉 instagram :-
https://www.instagram.com/abeshigeworeda?igsh=MjQyMXN5bnhkb2d2

‎👉X
https://x.com/AWoreda5717?t=x9hbuUQi9Esw9XahIjQkWQ&s=09

ወረዳዊ የበልግ ቡና ችግኝ ተከላ ማስጀመሪያ መርሃ-ግብር በአበሽጌ ወረዳ ጣጤሳ ቀበሌ ተካሄደግንቦት 05/2018 ዓ.ም (ወልቂጤ)በጉራጌ ዞን አበሽጌ ወረዳ ወረዳዊ የበልግ ወቅት የቡና ችግኝ ...
13/05/2026

ወረዳዊ የበልግ ቡና ችግኝ ተከላ ማስጀመሪያ መርሃ-ግብር በአበሽጌ ወረዳ ጣጤሳ ቀበሌ ተካሄደ

ግንቦት 05/2018 ዓ.ም (ወልቂጤ)

በጉራጌ ዞን አበሽጌ ወረዳ ወረዳዊ የበልግ ወቅት የቡና ችግኝ ተከላ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በዛሬው ዕለት በጣጤሣ ቀበሌ ተካሂዷል።

የወረዳ አመራሮች ፣ የዞኑ ግብርና መምሪያ እና የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት ማኔጅመንት አካላት እንዲሁም አርሶአደሮች በዚህ መርሐ-ግብር ላይ በመገኘት የቡና ችግኝ በመትከል አሻራቸውን አኑረዋል።

የቡና ምርት በጥራት በማምረት በዓለም አቀፍ ደረጃ ተመራጭ እንዲሆን ለማስቻል የተጀመረውን ጥረት ወደ ላቀ ደረጃ በማድረስ ከዘርፉ የሚገኘው ጥቅም ለማግኘት ቡናን በክላስተር ማምረት ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወት በመድረኩ ተገልጿል።

አርሶ አደሩ በጓሮው የቡና ችግኝ መትከል ፣ ምርት የማይሰጥ የቡና ተክል መጎንደል ወይም በመንቀል አዲስ ችግኝ መትከል እንዲሁም ለቡና ጥላ የሚሆኑ ሰብሎችን ከቡና ጎን መትከል ለዘርፉ ምርትና ምርታማነት ዕድገት አስፈላጊ መሆኑ ተነግሯል።

በመርሐ-ግብሩ ላይ የወረዳው ዋና አስዳዳሪ አቶ ካሡ ጁሀር ፣ የጉራጌ ዞን ግብርና መምሪያ ም/ኃላፊና የእንስሳትና አሳ ሀብት ዘርፍ ኃላፊ አቶ መሀመድ ሙደሲር ፣ የአበሽጌ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አብዱልከሪም ናስር ፣ የጉራጌ ዞን ግብርና መምሪያ የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ጊዜወርቅ አለሙ ፣ የጉራጌ ዞን ግብርና መምሪያ የቡናና ቅመማ ቅመም ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍቃዱ ፣ የዞንና የወረዳ ግብርና ማኔጅመንት አካላትና እንዲሁም ባለሙያና አርሶአደሮች ተገኝተዋል።

ዝርዝሩን ይዘን እንመለሣለን

ዘገባው የአበሽጌ ወረዳ መንግስት ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው።

ፔጃችን ስለምትከታተሉ እያመሰገንን ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ከታች የተቀመጡትን ሊንኮች በመጫን የተቋማችን የሚዲያ አማራጮችን ይጠቀሙ፡-

‎‎👉://www.facebook.com/profile.php?id=100070918473865&mibextid=kFxxJD

‎👉http://tiktok.com/

‎👉 ቴሌግራም፦ https://t.me/awc567

‎👉 ዩቲዩብ:- https://youtube.com/?si=8HvFtXplAUMiEnmx

‎👉 instagram :-
https://www.instagram.com/abeshigeworeda?igsh=MjQyMXN5bnhkb2d2

‎👉X
https://x.com/AWoreda5717?t=x9hbuUQi9Esw9XahIjQkWQ&s=09

ባለፉት አምስት ዓመታት በወረዳው በተከናወኑ የተቀናጁ የልማት ስራዎች፣ በማዘጋጃ ቤታዊ ገቢ፣ በመሰረተ ልማት ዝርጋታ እና በከተማ ማስፋፋት ረገድ መጠነ ሰፊ ለውጦች መመዝገባቸውን የአበሽጌ ወ...
13/05/2026

ባለፉት አምስት ዓመታት በወረዳው በተከናወኑ የተቀናጁ የልማት ስራዎች፣ በማዘጋጃ ቤታዊ ገቢ፣ በመሰረተ ልማት ዝርጋታ እና በከተማ ማስፋፋት ረገድ መጠነ ሰፊ ለውጦች መመዝገባቸውን የአበሽጌ ወረዳ የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ጽሕፈት ቤት ገለጸ።

ወልቂጤ ፣ግንቦት 5/2018 ዓ.ም በጉራጌ ዞን የአበሽጌ ወረዳ የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሰይፈ ገዛኸኝ እንደገለጹት፤ ወረዳው ካለበት የነባር ችግሮች ተላቆ ወደ ተሻለ የእድገት ምዕራፍ እንዲሸጋገር የተደረገው ጥረት ተጨባጭ ውጤቶችን እያሳየ ይገኛል።

የኢኮኖሚ አቅምና የከተማነት ዕድገት
የማዘጋጃ ቤት ገቢ አሰባሰብን በማዘመን ረገድ ከፍተኛ ውጤት የተመዘገበ ሲሆን፣ በ2013 ዓ.ም 3.9 ሚሊዮን ብር የነበረው ገቢ በ2018 ዓ.ም ወደ 33.6 ሚሊዮን ብር በማደግ የ8 እጥፍ ብልጫ አሳይቷል ብለዋል ያሉ ሲሆን በተመሳሳይ የከተማነት ዕውቅና ያገኙ ከተሞች ቁጥር ከ3 ወደ 4 ከፍ እንዲል ተደርጓል ብለዋል።

"አንድ ከተማ - አንድ ፕሮጀክት" እና ተቋማዊ ግንባታዎች
የህዝቡን የአገልግሎት ጥያቄ ለመመለስ በ2017 ዓ.ም የተጀመሩ አራት ወሳኝ ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ለአገልግሎት ክፍት መሆናቸውን አቶ ሰይፈ ገዛኸኝ ገልጸዋል። እነዚህም፦
• የዳርጌ ማህበረሰብ መድኃኒት መደብር፣
• የናቻ ጤና ኬላ፣
• የዋልጋ ምክር ቤት አዳራሽ፣
• የሆሌ ከተማ የንፁህ መጠጥ ውሃ ትራንስፎርመር ተከላና የጥገና ስራዎች ናቸው።

በተጨማሪም የአገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል የወረዳው አስተዳደር G+6 ህንፃ ጨምሮ በዋልጋ፣ በሆሌና በናቻ ከተሞች የቢሮ ግንባታዎች ተከናውነዋል።

የንግድ እንቅስቃሴን ለማሳለጥም የዋልጋ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል፣ የሆሌና ዳርጌ ሰንበት ገበያ እንዲሁም የዳርጌ ቄራ ግንባታዎች ለአገልግሎት ዝግጁ ሆነዋል።

የመሠረተ ልማት መስፋፋት (መንገድና መብራት)
የመንገድ መሰረተ ልማትን በሚመለከት በ2013 ዓ.ም 1.5 ኪ.ሜ ብቻ የነበረው የአዲስ ጠጠር መንገድ ግንባታ በ2018 ዓ.ም ወደ 17.217 ኪ.ሜ አድጓል።

የነባር መንገዶች ጥገናና ደረጃ ማሻሻልም በተመሳሳይ መልኩ ከ2.5 ኪ.ሜ ወደ 20.175 ኪ.ሜ ከፍ ማለቱን ገልፀው የመብራት መስመር ዝርጋታም ከ0.51 ኪ.ሜ ወደ 8.61 ኪ.ሜ በማደግ የከተሞችን ብርሃንና ደህንነት አረጋግጧል።

የማህበረሰብ ተሳትፎና የመሬት ዝግጅት
ለእነዚህ ስኬቶች የማህበረሰቡ ተሳትፎ ጉልህ ድርሻ ነበረው በዚህም በ2013 ዓ.ም 930,825 ብር የነበረው የህዝብ ተሳትፎ (በጥሬ ገንዘብ፣ በጉልበትና በቁሳቁስ) በ2018 ዓ.ም ወደ 18.6 ሚሊዮን ብር በማደግ አስገራሚ የአጋርነት መንፈስ ታይቶበታል።

ለመኖሪያና ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚውል የመሬት አቅርቦትም በሚከተለው መልኩ ተከናውኗል፦
• ለግል መኖሪያ ቤት፦ 13.75 ሄክታር ተዘጋጅቶ 4.06 ሄክታር ተላልፏል።
• ለማህበራት ቤት፦ 4.3 ሄክታር ተዘጋጅቶ 4.25 ሄክታር ተላልፏል።
• ለአገልግሎት ሰጪ ተቋማት፦ 12.98 ሄክታር ተዘጋጅቶ 7.9 ሄክታር ተላልፏል።
• ለኢንዱስትሪና ንግድ፦ ከ4.7 ሄክታር በላይ መሬት ተላልፏል።
የይዞታ ማረጋገጫን በተመለከተ ለ517 ባለይዞታዎች ህጋዊ ሰነድ፣ ለ159 አርሶ አደሮች ደግሞ የጊዜያዊ መጠቀሚያ ሰነድ መሰጠቱን ኃላፊው ገልጸው፤ በቀጣይም ከተሞች ለነዋሪዎቻቸው ምቹ እንዲሆኑ ስራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።

ዘገበው የአበሽጌ ወረዳ የመንግስት ኮ/ጉ/ጽ/ቤት ነው

‎ፔጃችን ስለምትከታተሉ እያመሰገንን ለተጨማሪ መረጃዎች የተቋማችን የሚዲያ አማራጮችን ይጠቀሙ፡-
‎‎👉://www.facebook.com/profile.php?id=100070918473865&mibextid=kFxxJD

‎👉http://tiktok.com/

‎👉 ቴሌግራም፦ https://t.me/awc567

‎👉 ዩቲዩብ:- የአበሽጌ ወረዳ የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ጽሕፈት ቤት
https://www.instagram.com/abeshigeworeda?igsh=MjQyMXN5bnhkb2d2

‎👉X
https://x.com/AWoreda5717?t=x9hbuUQi9Esw9XahIjQkWQ&s=09

ግንቦት 4/2018 ዓ.ም ወልቂጤ የአበሽጌ ወረዳ የብልፅግና ፓርቲ "የአደባባይ ቡና ጠጡ" ፕሮግራም በወረዳው ትምህርት ጽ/ቤት በመገኘት ለ7ኛ ዙር ሀገራዊ እና ክልላዊ  ምርጫ የይምረጡኝ ቅስ...
12/05/2026

ግንቦት 4/2018 ዓ.ም ወልቂጤ

የአበሽጌ ወረዳ የብልፅግና ፓርቲ "የአደባባይ ቡና ጠጡ" ፕሮግራም በወረዳው ትምህርት ጽ/ቤት በመገኘት ለ7ኛ ዙር ሀገራዊ እና ክልላዊ ምርጫ የይምረጡኝ ቅስቀሳ በድምቀት አካሄደ።

በጉራጌ ዞን የአበሽጌ ወረዳ የብልፅግና ፓርቲ "የአደባባይ ቡና ጠጡ" ፕሮግራም በወረዳው ትምህርት ጽ/ቤት በመገኘት የይምረጡኝ ቅስቀሳ በድምቀት አካሄዷል።

መምህራን በሀገር እድገትና ብልፅግና ላይ ትውልድ የመቅረፅ ፣በእዉቀትና በስነ-ምግባር የታነፁ ዜጋ በመፍጠር ረገድ ከፍተኛ ሀላፊነት እንዳለባቸው በማውሳት ለ7ኛ ዙር ሀገራዊ እና ክልላዊ ምርጫ በንቃት እንዲሳተፉ ተጠቅሷል።

ከዚህም በተጨማሪ መምህራን ለሀገሪቷ ሁሉን አቀፍ እድገት ትልቅ ባለ ውለታ መሆናቸው ታሪክ የሚመሰክረው እውነት እንደሆነ ሁሉ ወረዳው ለመምህራን ልዩ ትኩረት በመስጠት የመምህራን መብትና ጥቅማ ጥቅም በማስከበርና፣ የመማር ማስተማር ሥራው ስኬታማ እንዲሆን ጥሩ የሚባሉ ስራዎች እየሰራ መሆኑን በፕሮግራሙ ተመላክቷል።

ብልፅግና ፓርቲ ባለፉት የለውጥ አመታት በሀገሪቱ ካስመዘገባቸው ድሎች መካከል የትምህርት ፖሊሲው በማሻሻል በተማሪዎች ውጤትና ስነ ምግባር በርካታ ስራዎች እያከናወነ እንደሚገኝ ተገልጿል።

በፕሮግራሙ የአበሽጌ ወረዳ ም/አስተዳዳሪና የንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ቢኒያም ጥላሁን ፣የአበሽጌ ወረዳው ትምህርት ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ እንግዳ ጥሩሃ፣የአበሽጌ ወረዳው ትምህርት ጽ/ቤት ም/ሃላፊ አቶ ደስታ አቦሴ ጨምሮ የተቋሙ ባለሙያዎችና ሱፐርቫይዘሮች ተሳትፈዋል።

ምርጫችን👉 ብልፅግና
ምልክታችን 👉የስንዴ ነዶ
መልክታችን 👉ኢትዬጲያንወደ ተምሳሌት ሀገር !!

ዘገበው የአበሽጌ ወረዳ የመንግስት ኮ/ጉ/ጽ/ቤት ነው

‎ፔጃችን ስለምትከታተሉ እያመሰገንን ለተጨማሪ መረጃዎች የተቋማችን የሚዲያ አማራጮችን ይጠቀሙ፡-
‎‎👉://www.facebook.com/profile.php?id=100070918473865&mibextid=kFxxJD

‎👉http://tiktok.com/

‎👉 ቴሌግራም፦ https://t.me/awc567

‎👉 ዩቲዩብ:- https://youtube.com/?si=8HvFtXplAUMiEnmx

‎👉 instagram :-
https://www.instagram.com/abeshigeworeda?igsh=MjQyMXN5bnhkb2d2

‎👉X
https://x.com/AWoreda5717?t=x9hbuUQi9Esw9XahIjQkWQ&s=09

7ተኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ነፃ፣ፍትሐዊ ፣ተአማኒ ሆኖ በመራጩ ህዝብና በምርጫ ተዋንያን ዘንድ ቅቡልነት ሆኖ እንዲጠናቀቅ የድርሻቸውን ሃላፊነት እንደሚወጡ በአበሽጌ ወረዳ የሚገኙ የፐብሊክ ...
12/05/2026

7ተኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ነፃ፣ፍትሐዊ ፣ተአማኒ ሆኖ በመራጩ ህዝብና በምርጫ ተዋንያን ዘንድ ቅቡልነት ሆኖ እንዲጠናቀቅ የድርሻቸውን ሃላፊነት እንደሚወጡ በአበሽጌ ወረዳ የሚገኙ የፐብሊክ ሰርቫንት የአባላት
ገለፁ።

ወልቂጤ፣ግንቦት 4 /2018 ዓ.ም ፣ በጉራጌ ዞን የአበሽጌ ወረዳ የብልጽግና ፓርቲ የ2018 በጀት ዓመት የ3ኛ ሩብ አመት የፐብሊክ ሰርቫንትና የቀበሌ የአባላት ኮንፈረንስ አካሄደ።

በኮንፈረንሱ ላይ የህብረቱ እና የብልጽግና ኢንስፔክሽንና ስነ ምግባር ኮሚሽን የ3ተኛ ሩብ ዓመት ሪፖርት ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።

በኮንፈረንሱ ብልፅግና ፓርቲ እንደ ሀገር ብሎም እንደ ወረዳ በርካታ ተግዳሮቶችን በማለፍ የሰራቸውን ዘርፈብዙ ተግባራት ለክልሉ ብሎም ለሃገሪቱ ሁለንተናዊ ብልፅግና ማረጋገጥ ማሳያ መሆናቸውን ተገልጿል።

በቀጣይም ፓርቲው የጀመራቸውን የልማት ስራዎች አጠናክሮ በማስቀጠል በሃገር ደረጃ የተቀመጡ ትላልቅ ትልሞችን ለማሳካት የአባላቱ ድጋፍ ወሳኝ መሆኑ ተነስቷል።

አባላቱ 7ተኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ነፃ፣ኢፍትሐዊ ፣ተአማኒ ሆኖ በመራጩ ህዝብና በምርጫ ተዋንያን ዘንድ ቅቡልነት ሆኖ እንዲጠናቀቅ የድርሻቸውን ሃላፊነት እንደሚወጡም አረጋግጠዋል።

በኮንፍረንሱ ላይ በተደረገው ውይይት በአመለካከትና በተግባር ግንባር ቀደም አባል ሆኖ ለመቀጠል ቁርጠኛ አቋም የተያዘ ሲሆን በተቀመጡ አቅጣጫዎች ዙሪያ የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል።

በኮንፈረንሱ የህብረቱ እና የብልጽግና ኢንስፔክሽንና ስነ ምግባር ኮሚሽን የ3ተኛ ሩብ ዓመት የተከናወኑ ስራዎች ቀርበው ውይይት በማድረግ በቀጣይ ሊከናወኑ በሚገቡ ተግባር ላይ አቅጣጫዎች በማስቀመጥና ባለ 5 ነጥብ የአቋም መግለጫ በማውጣት ኮንፈረንሱ ተጠናቋል።

በመድረኩ የአበሽጌ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ሃላፊ አቶ ትግስቱ ወርቁ፣የአበሽጌ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ኢንስፔክሽንና ስነምግባር ኮሚሽን ቅ/ፅ/ቤት ሃላፊ አቶ ታደሰ አለሙ፣የወረዳ አመራሮች ጨምሮ የወረዳው አጠቃላይ ፐብሊክ ሰርቫንት ተሳትፈዋል።

ምርጫችን👉 ብልፅግና
ምልክታችን 👉የስንዴ ነዶ
መልክታችን 👉ኢትዬጲያንወደ ተምሳሌት ሀገር !!

ዘገበው የአበሽጌ ወረዳ የመንግስት ኮ/ጉ/ጽ/ቤት ነው

‎ፔጃችን ስለምትከታተሉ እያመሰገንን ለተጨማሪ መረጃዎች የተቋማችን የሚዲያ አማራጮችን ይጠቀሙ፡-
‎‎👉://www.facebook.com/profile.php?id=100070918473865&mibextid=kFxxJD

‎👉http://tiktok.com/

‎👉 ቴሌግራም፦ https://t.me/awc567

‎👉 ዩቲዩብ:- https://youtube.com/?si=8HvFtXplAUMiEnmx

‎👉 instagram :-
https://www.instagram.com/abeshigeworeda?igsh=MjQyMXN5bnhkb2d2

‎👉X
https://x.com/AWoreda5717?t=x9hbuUQi9Esw9XahIjQkWQ&s=09

Address

Wolkite
94

Telephone

0113301423

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gurage Zone Abeshige Woreda Communication affairs office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share