14/05/2026
በምርጫ ሂደት ውስጥ የአባላት ሚና የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን ለማረጋገጥና የሀገርን ቀጣይ አቅጣጫ ለመወሰን እጅግ ወሳኝ እንደሆነ ተገለፀ።
ግንቦት 6/2018 ዓ.ም (ወልቂጤ)
በአበሽጌ ወረዳ ገቢዎች እና ንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤት በጋራ በመሆን የብልፅግና ፓርቲ ቤተሠብ አባላት የቡና ጠጡ ፕሮግራም አካሄዱ።
ለ7ኛው ዙር ሀገራዊ እና ክልላዊ ምርጫ እጩዎችን ለማስተዋወቅ እና የምረጡ ቅስቀሳ በተዘጋጀው ፕሮግራም ላይ ብልጽግና ፓርቲን ወክሎ የቀረቡ እጩዎችን እና የምርጫ ምልክት የማስተዋወቅ መርሃ-ግብር ተካሄዷል።
የመርሃ-ግብሩ ዋነኛው ዓላማው መጪው 7ኛው ዙር ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ፍፁም ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ተዓማኒ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ሁሉም አባል የበኩሉን መወጣት እንደሚገባው ተገልጿል።
''ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር'' በሚል መሪ ሀሳብ የ7ኛው ዙር ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ የብልጽግና ፓርቲ መወዳደሪያ ምልክት፤ የፓርቲው የምርጫ ማኒፌስቶ እና እጩዎችን የማስተዋወቅ ተግባር ተከናውኗል።
ብልጽግና ፓርቲ በባለፉት ዓመታት የተለያዩ ፈተናዎችን በድል በማሻገር ዘርፈ ብዙ ተግባራትና በርካታ ትሩፍቶች ለህዝቡ ተጠቃሚነትና ተደራሽነት ከማትረፉ በዘለለ ብዙ የተሞክሮ ተምሳሌቶችን ያተረፈ መሆኑን በመርሃ-ግብሩ ተብራርቷል።
በመድረኩም 7ኛው ዙር ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ስኬታማ እንዲሆን በየደረጃ የሚገኙ የሁሉም አባላት ሚና ከፍተኛ መሆኑ ተጠቅሶ ቀጣይ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን ለማረጋገጥ በዘርፉ ብዙ ተግባራት ላይ አባላት ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርጉ መልዕክት ተላልፏል።
በመርሃ-ግብሩም የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ካሡ ጁሀር ፣ የወረዳው ም/ዋና አስተዳዳሪና ንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ቢኒያም ጥላሁን ፣ የወረዳው ገቢዎች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፋንታሁን ብርሀን ፣ የሁለቱም ጽ/ቤቶች የፓርቲው አባላት ተሳትፈዋል።
ዘገበው የአበሽጌ ወረዳ የመንግስት ኮ/ጉ/ጽ/ቤት ነው
ፔጃችን ስለምትከታተሉ እያመሰገንን ለተጨማሪ መረጃዎች የተቋማችን የሚዲያ አማራጮችን ይጠቀሙ፡-
👉://www.facebook.com/profile.php?id=100070918473865&mibextid=kFxxJD
👉http://tiktok.com/
👉 ቴሌግራም፦ https://t.me/awc567
👉 ዩቲዩብ:- https://youtube.com/?si=8HvFtXplAUMiEnmx
👉 instagram :-
https://www.instagram.com/abeshigeworeda?igsh=MjQyMXN5bnhkb2d2
👉X
https://x.com/AWoreda5717?t=x9hbuUQi9Esw9XahIjQkWQ&s=09