Gurage Zone Abeshige Woreda Communication affairs office

Gurage Zone Abeshige Woreda Communication affairs office Abeshige woreda government communication affairs dep't!

የአበሽጌ ወረዳ ንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤት የክረምት በጎ ስራን አስመልክቶ ለአንዲት አቅመ ደካማ እናት የመኖሪያ ቤት የመገንባት ስራ አስጀመረነሀሴ 10/2018 ዓ.ም (ወልቂጤ)በጉራጌ ዞን ...
16/08/2026

የአበሽጌ ወረዳ ንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤት የክረምት በጎ ስራን አስመልክቶ ለአንዲት አቅመ ደካማ እናት የመኖሪያ ቤት የመገንባት ስራ አስጀመረ

ነሀሴ 10/2018 ዓ.ም (ወልቂጤ)

በጉራጌ ዞን አበሽጌ ወረዳ አምበልታ ቀበሌ የወረዳው ንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤት የክረምት በጎ ስራን አስመልክቶ ለአንዲት አቅመ ደካማ እናት የመኖሪያ ቤት የመገንባት ስራ አስጀምሯል።

ተቋሙ በዛሬው ዕለት ባደረገው የመጀመሪያ ድጋፍ ለቤት መስርያ የሚያገለግል የተለያዩ ቁሳቁሶችን ያበረከተ ሲሆን ቤቱ ተገንብቶ እስኪጠናቀቅ ድረስ አስፈላጊውን ሁሉ እንደሚያደርጉ አስታውቋል።

በርክክብ ስነስርአቱ የተገኙት የአበሽጌ ወረዳ ንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊና የወረዳው ም/አስተዳዳሪ አቶ ቢኒያም ጥላሁን እንደገለጹት የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት ስራዎች ስኬታማ ለማድረግና ውጤታማ ስራዎችን ለመስራት ሁሉም ባለድርሻ አካላት ተባብሮ መስራት እንደሚገባቸው ጠቅሠዋል።

በዛሬው እለትም በአምበልታ ቀበሌ በመገኘት ለወ/ሮ ፋጥወት ኑሮ የቤት መስሪያ አስፈላጊ ቁሳቁስ ድጋፍ እንዲያደርጉ ያነሳሳቸው ወይዘሮዋ በከፍተኛ የመኖሪያ ቤት ችግር ላይ መሆናቸውን በማየትና ደጋፊና ጧሪ የሌላቸው በመሆኑ እንደሆነ ገልጸዋል።

አክለውም ቤታቸው ለመኖሪያነት የማይሆን መሆኑን በመመልከት ይህን ድጋፍ ማድረጋቸው ኃላፊው ገልጸው የቀበሌውም ነዋሪ በመተባበር ባጠረ ጊዜ ተጠናቆ ማስረከብ እንደሚገባ ጠቁመዋል።

በወረዳ ደረጃም በተያዘው የክረምት ወራት በርካታ የአረጋውያን ቤቶች እየተገነቡ እንደሚገኝ አስታውሠው በበጋው ወራትም መሠል ተግባራት ቅንጅታዊ አሰራሮችን አጠናክሮ በማስቀጠል መቀጠል እንደሚገባቸው አቶ ቢኒያም አሳስበዋል።

በስጦታ የተበረከቱት ለቤት ግንባታ የሚሆኑ ቁሣቁሶች ከወረዳው የነጋዴው ማህበረሰብ በተሠበ ገንዘብ መሆኑን አውስተው በግልም አንዳንድ ባለሀብቶች መሣተፋቸውን ገልጸዋል።

የአበሽጌ ወረዳ ውሀና ማእድን ኢነርጂ ጽ/ቤት ኃላፊና የቀበሌው ደጋፊ አቶ ሙላቱ ደሳለኝ በበኩላቸው ለወገን ደራሽ ወገን መሆኑን ለማስመስከር አቅመ ደካማ ለሆኑ እናት እያደረጉ ያሉትን የመኖሪያ ቤት ገንብቶ የመስጠት ተግባር እጅግ የሚያስመሰግን ነው ስሉ ገልጸዋል።

አክለውም ይህ ቤት በዛሬው ዕለት እንደተጀመረ ሁሉ በአጭር ጊዜ ተጠናቆ እማወራዋ እፎይታን እንድታገኝ ሁሉም አካላት ከወዲሁ እርብርብ እንዲያደርግ አሳስበዋል።

ወ/ሮ ፋጥወት ኑሮ በበኩላቸው ኑሮዋቸው አስቸጋሪ እንደነበር ጠቁመው ይኖሩበት የነበረው ሳር ቤት በከፊል በመፍረሱ ምክንያት የከፋ ችግር ውስጥ ገብተው እንደነበር ተናግረው ዛሬ በተደረገላቸው ድጋፍ መደሰታቸውንና ድጋፉን ያደረጉ አካላትን አመስግነዋል።

በመርሀ-ግብሩ ላይ የወረዳው የአበሽጌ ወረዳ ንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊና የወረዳው ም/አስተዳዳሪ አቶ ቢኒያም ጥላሁን ፣ አበሽጌ ወረዳ ውሀና ማእድን ኢነርጂ ጽ/ቤት ኃላፊና የቀበሌው ደጋፊ አቶ ሙላቱ ደሳለኝ ጨምሮ የጽ/ቤቱ ባለሙያዎች ተገኝተዋል።

ዘገባው የአበሽጌ ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት ነው።

ፔጃችን ስለምትከታተሉ እያመሰገንን ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ከታች የተቀመጡትን ሊንኮች በመጫን የተቋማችን የሚዲያ አማራጮችን ይጠቀሙ፡-
‎‎👉://www.facebook.com/profile.php?id=100070918473865&mibextid=kFxxJD

‎👉http://tiktok.com/

‎👉 ቴሌግራም፦ https://t.me/awc567

‎👉 ዩቲዩብ:- https://youtube.com/?si=8HvFtXplAUMiEnmx

‎👉 instagram :-
https://www.instagram.com/abeshigeworeda?igsh=MjQyMXN5bnhkb2d2

‎👉X
https://x.com/AWoreda5717?t=x9hbuUQi9Esw9XahIjQkWQ&s=09

በአበሽጌ ወረዳ ህገ-ወጥ የመሬት ወረራን ለመከላከል የሚያስችል ባለድርሻ አካላት የተሳተፉበት የንቅናቄ ውይይት ተካሄደ"ውስን የሆነውን የመሬት ሀብታችንን ከህገ-ወጥ ወረራና ምዝበራ በመከላከል...
16/08/2026

በአበሽጌ ወረዳ ህገ-ወጥ የመሬት ወረራን ለመከላከል የሚያስችል ባለድርሻ አካላት የተሳተፉበት የንቅናቄ ውይይት ተካሄደ

"ውስን የሆነውን የመሬት ሀብታችንን ከህገ-ወጥ ወረራና ምዝበራ በመከላከል ፍትሃዊ የከተሞች እድገትን እናረጋግጣለን" በሚል መሪ ቃል በአበሽጌ ወረዳ ከተማ ልማትና ቤቶች ልማት ጽህፈት ቤት አስተባባሪነት የባለድርሻ አካላት የንቅናቄ ውይይት መድረክ ተካሄደ።

ነሐሴ 10/2018 ዓ.ም ወልቂጤ

የአበሽጌ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ካሡ ጁሀር በመድረኩ እንደገለፁት የመሬት ሀብትን በአግባቡ መምራት የከተሞችን የገቢ አቅም ለማሳደግ፣ የኢንዱስትሪ ልማትና የሥራ እድል ፈጠራን ለማፋጠን ከፍተኛ ድርሻ አለው።

አክለውም የታችኛው እርከን አመራሮችና ባለሙያዎች ህገ-ወጥነትን የገቢ ምንጭ በማድረግ በሌብነት መሳተፋቸውና በህገ-ወጦች ላይ የማያዳግም ህጋዊ እርምጃ አለመወሰዱ ለህገ-ወጥ መሬት ምዝበራ መስፋፋት በምክንያትነት ዘርዝረዋል።

አያይዘውም "ወደፊት ህጋዊ ይደረግልኛል" የሚል አጉል ተስፋ መኖሩ እንዲሁም የአመራር ለውጥ የሚደረግባቸውን እና የመንግስት መዋቅር በሌሎች ስራዎች የሚጠመድበትን አጋጣሚ በመጠቀም የሚፈጸም መሆኑን አብራርተዋል።

የጉራጌ ዞን ትራንስፖርት እና መንገድ ልማት መምሪያ ኃላፊና የወረዳው ደጋፊ አመራር አቶ የህያ ሡልጣን በበኩላቸው
ችግሩ አደገኛ ደረጃ ላይ በመድረሱ በይደር የሚታለፍ ባለመሆኑ ዛሬ ነገ ሳይባል በቅንጅት መፍትሔ መስጠት እንደሚገባ አመላክተዋል።

ለዚህም ይረዳ ዘንድ የከተማ ወሰኖችን በአግባቡ ማካለል፣ የይዞታዎችን መረጃ አጥርቶ መያዝ እና ለአርሶ አደሮች ጊዜያዊ የእርሻ መጠቀሚያ ሰርተፊኬት መስጠት ችግሩን ቀድሞ ለመከላከል ይረዳል ብለዋል።

የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ሰይፈ ገዛኸኝ እንዳመለከቱት በአሁኑ ወቅት በከተሞች ማስፋፊያ አካባቢዎች፣ በመንግስትና በህዝብ የጋራ ይዞታዎች እንዲሁም በአረንጓዴ ስፍራዎች ላይ የሚፈጸመው ህገ-ወጥ የመሬት ወረራ ከመቼውም ጊዜ በላይ እየተበራከተ መጥቷል።

ውስን የሆነውን የመሬት ሃብት በአግባቡ መምራት ከተሞችን በፕላንና በዘመናዊ መንገድ ለመምራት ይጠቅማል ያሉ ሲሆን የገቢ አቅማቸውን እንዲያሳድጉ፣ፍትሃዊ የሀብት ክፍፍል እንዲኖርና ቀጣይነት ያለውን ገቢ በማግኘት ልማታቸውን እንዲያፋጥኑ ያግዛል በማለት ጠቀሜታው ዘርዝረዋል።

ከዚህም በተጨማሪ የመኖሪያ ቤት አቅርቦትን ለማሻሻል ይረዳል ያሉት አቶ ሰይፈ ህገ-ወጥ ተግባሩ በዋናነት በልማት ተነሺዎች፣ በመኖሪያ ቤት ህብረት ሥራ ማህበራት፣ በኢንተርፕራይዞችና በኢንቨስትመንት ስም የሚከናወን መሆኑን ገልፀው ድርጊቱ ኢኮኖሚያዊ፣ ህጋዊ፣ ፖለቲካዊ እና ማህበራዊ ቀውስ እያስከተለ ይገኛል በማለት አብራርተዋል።

በመጨረሻም አቶ ሰይፈ ገዛኸኝ እንዳሰመሩበት፣ ህገ-ወጥ ግንባታ ከተካሄደ በኋላ ማፍረስ የሀብት ብክነት የሚያስከትል በመሆኑ፣ ዋናው ትኩረት ህገ-ወጥነትን በጅምር ማስቆም እና የቀደሙ ጥፋቶች ላይ አስተማሪ ህጋዊ እርምጃ መውሰድ እንደሆነ ገልጸዋል።

የውይይቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው በህገ-ወጥ ወረራ እና ምዝበራ ላይ በተሳተፉ ግለሰቦች፣ ደላሎችና አስተባባሪ አመራሮች ላይ የማያዳግም ህጋዊ እርምጃ መውሰድና ህብረተሰቡ ጥቆማ የሚሰጥበትንና መሬቱን የሚጠብቅበትን አሰራር መዘርጋት፣ ማህበረሰብ አቀፍ ፖሊስን ማጠናከር ይገባል ብለዋል።

በውይይቱ የአበሽጌ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ሃላፊና ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ሙሉጌታ ፈቀደ ጨምሮ አጠቃላይ የወረዳ አመራር ፣ የማዘጋጃ ከተማ ስ/አስኪያጆችና ባለሙያዎች እንዲሁም የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።

ዘገባው የአበሽጌ ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት ነው።

ፔጃችን ስለምትከታተሉ እያመሰገንን ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ከታች የተቀመጡትን ሊንኮች በመጫን የተቋማችን የሚዲያ አማራጮችን ይጠቀሙ፡-
‎‎👉://www.facebook.com/profile.php?id=100070918473865&mibextid=kFxxJD

‎👉http://tiktok.com/

‎👉 ቴሌግራም፦ https://t.me/awc567

‎👉 ዩቲዩብ:- https://youtube.com/?si=8HvFtXplAUMiEnmx

‎👉 instagram :-
https://www.instagram.com/abeshigeworeda?igsh=MjQyMXN5bnhkb2d2

‎👉X
https://x.com/AWoreda5717?t=x9hbuUQi9Esw9XahIjQkWQ&s=09

የሳምንቱ አበይት ዜናዎችና መረጃዎች ===========//=========ነሐሴ 10/2018 ዓ.ም ወልቂጤ በጉራጌ ዞን አበሽጌ ወረዳ ቦረር ቀበሌ አመራሮችና ከተለያዩ የኀብረተሰብ ክፍሎች ጋር ...
16/08/2026

የሳምንቱ አበይት ዜናዎችና መረጃዎች
===========//=========
ነሐሴ 10/2018 ዓ.ም ወልቂጤ

በጉራጌ ዞን አበሽጌ ወረዳ ቦረር ቀበሌ አመራሮችና ከተለያዩ የኀብረተሰብ ክፍሎች ጋር በወቅታዊ የሰላምና የልማት ጉዳዮች ዙሪያ የህዝብ ውይይት ተደረገ።

በጉራጌ ዞን የአበሽጌ ወረዳ ገቢዎች ጽህፈት ቤት እና ንግድና ገበያ ልማት ጽህፈት ቤት በጋራ በመሆን ከሐምሌ 1/2018 ዓ.ም ጀምሮ ሲካሄድ የቆየውን የደረጃ "ለ" ግብር አሰባሰብና የ2019 ዓ.ም የንግድ ሥራ ፈቃድ ዕድሳት አፈጻጸም ገመገሙ።

በጉራጌ ዞን የአበሽጌ ወረዳ የ2018/19 የመኸር ወቅት ወረዳዊ የጤፍ ዘር ማስጀመሪያ መርሃ-ግብር በማመዴ ቀበሌ በደመቀ ሁኔታ ተካሄደ።

የወልቂጤ ግብርና ምርምር ማዕከል ከአካባቢው አልፎ ለሀገር ጭምር የሚሆኑ የምርምር ሥራዎችን በመሥራትና በማስተዋወቅ ረገድ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከተ እንደሚገኝ
የአበሽጌ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ካሱ ጁሃር ገለፁ።

ፔጃችን ስለምትከታተሉ እያመሰገንን ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ከታች የተቀመጡትን ሊንኮች በመጫን የተቋማችን የሚዲያ አማራጮችን ይጠቀሙ፡-

‎✅https://www.facebook.com/profile.php?id=100070918473865&mibextid=kFxxJD

‎✅http://tiktok.com/

‎✅https://t.me/awc567

‎✅https://youtube.com/?si=8HvFtXplAUMiEnmx

‎✅https://www.instagram.com/abeshigeworeda?igsh=MjQyMXN5bnhkb2d2

የአርሶአደሮች ተጠቃሚነት በዘላቂነት  ለማረጋገጥ  የእንሰት አጠውልግ በሽታ  ለመከላከል በትኩረት እንደሚሰራ የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት አስታወቀ።ነሀሴ9/2018(ወልቂጤ)ከእንስት...
15/08/2026

የአርሶአደሮች ተጠቃሚነት በዘላቂነት ለማረጋገጥ የእንሰት አጠውልግ በሽታ ለመከላከል በትኩረት እንደሚሰራ የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት አስታወቀ።

ነሀሴ9/2018(ወልቂጤ)

ከእንስት አጠውልግ በሽታ ነጻ የሆነ መንደር ለመፍጠር የማስጀመሪያ ፕሮግራም በእዣ ወረዳ የስራይ ቀበሌ አካሂዷል ።

የጉራጌ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ አበራ ወንድሙ እንደገለጹት እንሰት ለዞኑ ህዝብ የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ ድርቅ ለመከላከልና የኢኮኖሚ ዋልታ መሆኑን አስረድተዋል።

የእንሰት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በዘርፉ የሚስተዋሉ ተግዳሮቶችን በተለይ የአጠውልግ በሽታ በሰብሉ ላይ ከፍተኛ ጉዳት እያደረሰ በመሆኑ ከተለያዩ ምርምር ተቋሟት ጋር እየተሰራ ይገኛል።

እንሰት ከጉራጌ ማህበረሰብ እጅጉን የተዋሀደ ከምግብነት ባለፈ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ የሚሰጥ በመሆኑ አርሶአደሮች የሚሰጣቸውን የበሽታው መከላከያ ዘዴዎችን በአግባቡ ሊጠቀሙበት እንደሚገባ ተናገረዋል።

በኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የግብርና ምርምር ማስተባባሪያ ጽህፈት ቤት ሀላፊ ዶ/ር መኩረያ ታደሰ እንደተናገሩት ኢንስቲትዩቱ የአርሶአደሮች ተጠቃሚነት በዘላቂነት ለማረጋገጥ የእንሰት አጠውልግ በሽታ ለመከላከል እየሰራ ይገኛል።

የተሻሻለ ዝርያ ያላቸው የእንሰት ምርቶችን በማብዛትና አርሶአደሩ ከምርቱ ተጠቃሚ እንዲሆን ከግብርና ሚነስትር እንዲሁም ከተለያዩ ተራድኦ ድርጅቶች ጋር ኢንስቲትዩቱ እየሰራ መሆኑን ዶ/ር መኩሪያ አስረድተዋል ።

የወልቂጤ ግብርና ምርምር ማእከል ዳይሬክተር አቶ ቤተል ነክር በበኩላቸው የወልቂጤ ምርምር ማእከል በጉራጌና በምስራቅ ጉራጌ ዞኖች በእንሰት አጠውልግ በሽታ የተጠቁ አካባቢዎችን በመለየት ከበሽታው የማላቀቅ ስራዎች እየተሰሩ ነው ብለዋል።

አርሶአደሮች የማሳ ንጽህና በተገቢው በመጠበቅና የመገልገያ እቃዎችን በማጽዳት እንዲሁም በበሽታው የተጠቁ እንሰቶችን በጥንቃቄ በማስወገድ የእንሰት አጠውልግ በሽታን ሊከላከሉ እንደሚገባ ተናግረዋል።

አቶ ቤተል አክለውም ለመድሀኒትነትና ለሌሎች አገልግሎት የሚውሉ የእንሰት አይነቶች በበሽታው እንዳይጠቁና እንዳይጠፉ ዝርያቸው የማብዛት ስራ ማእከሉ በትኩረት እየሰራ እንደሆነ ገልጸዋል።

አርሶአደር ጀማል ሁሴንና ነስሩ ሁሴን በእዣ ወረዳ የስራይ ቀበሌ ነዋሪዎች ሲሆኑ የእንሰት አጠውልግ በሸታው የእንሰት ምርታቸውን በከፍተኛ ሁኔታ እየጎዳ እንደነበር ሲያነሱ በተሰጣቸው የግንዛቤ ስልጠና በሽታውን እየተከላከሉ እንደሚገኙ ተናግረዋል።

የእንሰት ተክል መሳሪያ የሆኑትን ባለመዋዋስ ካልሆነ ከተዋዋሱም እቃቸውን በአግባቡ አጽድተው እንደሚጠቀሙ ሲጠቁሙ በበሽታው የተጠቁ እንሰቶችን ወደ ሌላ እንዳያስተላልፉ በተዘጋጀላቸው ጉድጓድ እንደሚያስወግዱ ገልጸዋል።

የወልቂጤ ግብርና ምርምር ማእከል ለአርሶአደሮች በሽታው የሚተላለፉባቸው መንገዶች ለመቀነስ የማሳ ግብአቶችን እንዲሁም ለተደራጁ ወጣቶች የእንሰት መፋቂያ ማሽን ተበርክቶላቸዋል።

በመጨረሻም የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሀግብር ሲከናወን በቀጣይ በበሽታውን ለመከላከል የሚያግዝ ውይይት ተካሂዷል።

ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ሕፃናት እና በተለያዩ ምክንያቶች ያቋረጡ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት እንዲመጡ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ሚናቸውን እንዲወጡ ጥሪ ቀረበነሃሴ 09/2018 ዓ.ም (ወ...
15/08/2026

ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ሕፃናት እና በተለያዩ ምክንያቶች ያቋረጡ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት እንዲመጡ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ሚናቸውን እንዲወጡ ጥሪ ቀረበ

ነሃሴ 09/2018 ዓ.ም (ወልቂጤ)

በጉራጌ ዞን አበሽጌ ወረዳ ትምህርት ፅ/ቤት የ2018 ዓ.ም የክረምት ስራዎች አፈፃፀም ግምገማና እና የ2019 ዓ.ም የተማሪዎች ቅበላ የንቅናቄ መድረክ ከባለድርሻ አካላት ጋር ተካሄደ።

የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ካሡ ጁሀር በመድረኩ ተገኝተው ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ሕፃናት ወደ ትምህርት ቤት እንዲመጡ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ሚናቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።

ቀሪውን የክረምት ወቅት በመጠቀም ትምህርት ቤቶች ምቹ የመማር ማስተማር አካባቢ እንዲኖራቸው በማድረግ የትምህርት ጥራትን በማስጠበቅ የተማሪዎችን ውጤት እንዲሻሻል መስራት ይገባል ብለዋል።

ትምህርት የሁሉም ማህበረሰብ ጉዳይ በመሆኑ ያሉ ተግዳሮቶችን በመወጣት የተማሪዎች ምዝገባ በወቅቱ እንዲጠናቀቅ የተማሪዎች ልየታ በተቀመጠለት መርሃ ግብር መሰረት መካሄድ እንዳለበትና የ2019 ዓ.ም ቅበላ ዕቅድ በተሳካ ሁኔታ ማስፈጸም እንደሚገባም ጠቁመዋል።

ትምህርት ያቋረጡና ከትምህርት ገበታ ውጭ ያሉ ሕፃናትን በቤት ለቤት ዳሰሳ በመለየት ወደ ትምህርት ገበታ እንዲመለሱ ለማድረግ የትምህርት አመራሩና የተማሪ ወላጆች ሀላፊነታቸውን ሊወጡ እንደሚገባም አቶ ካሡ አሳስበዋል።

በተያዘው ክረምት በትምህርት ከታቀዱ ተግባራት መካከል የመሠረታዊ ኮምፒውተር ስልጠና ፣ የአረንጓዴ አሻራ ከችግኝ ተከላ ማካሄድ ፣ የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርት ከመስጠት ፣ የክረምት በጎ ፈቃድ በወጣቶችና በማህበረሰብ ከመስራት አኳያ እየተሠሩ ያሉ ስራዎች አበረታች መሆናቸውን ገልጸው በተለይ ምቹ የመማሪያ ስፍራ ከመፍጠር ጋር አሁንም በትኩረት መሠራት እንደሚገባው ጠቁመዋል።

የወረዳው ብልፅግና ፓርቲ ጽህፈት ጽህፈት ቤት ኃላፊና ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ሙሉጌታ ፈቀደ በበኩላቸው በትምህርት ዘርፍ በርካታ ስራዎች መሠራታቸውን አውስተው ነገር ግን ትምህርት ቤቶች ለተማሪዎች ምቹ ከማድረግ ጋር ቀሪ ስራ እንዳለው ገልጸዋል።

በተለይም በክረምት ወራት የተማሪዎች ውጤት ለማሻሻል እየተሰሩ ያሉ ውጤታማ ስራዎች ይበልጥ ማጠናከር እንደሚገባና ተማሪዎች በሚፈለገው ልክ ተቀስቅሰው ወደ ትምህርት ገበታ እንዲገቡና በወቅቱ ምዝገባ እንዲያካሂዱ የትምህርት ባለድርሻ አካላት ትልቅ ሀላፊነት እንዳለባቸው ተናግረዋል።

በቀበሌ ያሉ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በትምህርት ጉዳይ እኩል ተሳታፊ በመሆንና ቤት ለቤት ልየታ በማድረግ የተማሪዎች ምዝገባ ወቅቱን ጠብቆ መካሄድ እንደሚገባው ገልጸዋል።

የአበሽጌ ወረዳ ትምህርት ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ እንግዳ ጥሩሀ በበኩላቸው የትምህርት ጥራት ለማሻሻል በወረዳው በርካታ ስራዎች ሲሰሩ መቆየታቸውን አስታውሠው አሁን ደግሞ ተማሪዎችን በወቅቱ በመመዝገብ ወደ ትምህርት ገበታ በማስገባት የመማር ማስተማር ስራ በተሳካ መልኩ መጀመር እንደሚገባ ገልጸዋል።

በወረዳው በ2019 የትምህርት ዘመን ከ 21 ሺህ 5 መቶ 18 በላይ ተማሪዎችን ለመቀበል መታቀዱን ጠቁመው የተማሪዎች ምዝገባ ከነሐሴ 11 እስከ ነሀሴ 30/2018 ዓ.ም እንደሚከናወን ገልጸዋል።

ከቅድመ አንደኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያሉ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ሕፃናትና ወጣቶችን ሙሉ በሙሉ መመዝገብ እንደሚገባም አንስተዋል።

ትምህርት ያቋረጡና ከትምህርት ገበታ ውጭ ያሉ ሕፃናትን በቤት ለቤት ዳሰሳ በመለየት ወደ ትምህርት ገበታ እንዲመለሱ ማድረግ ልዩ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባም አሳስበዋል።

በወረዳው ከነሃሴ 11 እስከ 30 በሚካሄደው የተማሪዎች ምዝገባ በስኬት እንዲጠናቀቅ ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ እንደሚገባ ገልጸው ከነሀሴ 11/2018 ዓ.ም ጀምሮ ሁሉም መምህራን በትምህርት ቤት መገኘት እንዳለባቸውም አሳስበዋል።

‎ትምህርት በወቅቱ ባለመጀመሩ የሚባክነው የትምህርት ክፍለ ጊዜ በተማሪዎች ውጤት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ እንደሚያሳድር አንስተው ለዚህም ሁላቸውም የድርሻውን እንደሚወጡ ተናግረዋል።

አካታች የትምህርት ስርዓት ለመፍጠር አካል ጉዳተኞችና ለሴት ተማሪዎች የሚያስፈልጉ የትምህርት ቁሳቁሶችን ማሟላትና ምቹ የመማሪያ አካባቢ መፍጠር ያስፈልጋል ብለዋል።

አቶ እንግዳ ጨምረው እንዳሉት ከነሀሴ11 እስከ ነሀሴ 30 ድረስ የተማሪዎች ምዝገባ በማካሄድ መስከረም 5 በሁሉም ትምህርት ቤቶች ትምህርት እንዲጀመር ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል።

የተማሪዎችን ምዝገባ መረጃ በEMIS (የትምህርት መረጃ አስተዳደር ስርዓት) መስፈርት መሰረት በትክክል ማደራጀትና ሪፖርት ማድረግ እንደሚገባም ተናግረዋል።

የዚህ ንቅናቄ ስኬታማነት የወላጆች፣ የህብረተሰብ ክፍሎች፣ የሃይማኖት አባቶችና የባለድርሻ አካላት የጋራ ጥረትና ቅንጅታዊ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን አስገንዝበዋል።

በመድረኩም የጉራጌ ዞን ትራንስፖርት እና መንገድ ልማት መምሪያ ኃላፊና የወረዳው ደጋፊ አመራር አቶ የህያ ሡልጣን ፣ የጉራጌ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ መብራቴ ፣ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ካሡ ጁሀር ፣ የወረዳው ረዳት የመንግስት ተጠሪ እና የብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙሉጌታ ፈቀደ ጨምሮ አጠቃላይ የወረዳ አመራር ፣ መምህራንና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

ዘገባው የአበሽጌ ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት ነው።

ፔጃችን ስለምትከታተሉ እያመሰገንን ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ከታች የተቀመጡትን ሊንኮች በመጫን የተቋማችን የሚዲያ አማራጮችን ይጠቀሙ፡-
‎‎👉://www.facebook.com/profile.php?id=100070918473865&mibextid=kFxxJD

‎👉http://tiktok.com/

‎👉 ቴሌግራም፦ https://t.me/awc567

‎👉 ዩቲዩብ:- https://youtube.com/?si=8HvFtXplAUMiEnmx

‎👉 instagram :-
https://www.instagram.com/abeshigeworeda?igsh=MjQyMXN5bnhkb2d2

‎👉X
https://x.com/AWoreda5717?t=x9hbuUQi9Esw9XahIjQkWQ&s=09

የአበሽጌ ወረዳ ትምህርት ፅ/ቤት የክረምት ስራዎች አፈፃፀም ግምገማና እና የ2019 ዓ.ም መደበኛና መደበኛ ያልሆኑት ትምህርት ቅበላ የንቅናቄ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።ነሃሴ 09/2018 ዓ...
15/08/2026

የአበሽጌ ወረዳ ትምህርት ፅ/ቤት የክረምት ስራዎች አፈፃፀም ግምገማና እና የ2019 ዓ.ም መደበኛና መደበኛ ያልሆኑት ትምህርት ቅበላ የንቅናቄ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።

ነሃሴ 09/2018 ዓ.ም (ወልቂጤ)

በጉራጌ ዞን አበሽጌ ወረዳ ትምህርት ፅ/ቤት የ2018 ዓ.ም የክረምት ስራዎች አፈፃፀም ግምገማና እና የ2019 ዓ.ም የተማሪዎች ቅበላ የንቅናቄ መድረክ ከባለድርሻ አካላት ጋር እየተካሄደ ይገኛል።

የወረዳው ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ እንግዳ ጥሩሀ የተዘጋጀውን ሠነድ እያቀረቡ ይገኛል።

ትምህርት ቤቶች ምቹ የመማር ማስተማር አካባቢ እንዲኖራቸው በማድረግ የትምህርት ጥራትን በማስጠበቅ የተማሪዎች ውጤት እንዲሻሻል መደረግ እንዳለበትም ገልጸዋል።

ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ሕፃናት ወደ ትምህርት ቤት እንዲመጡ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ሚናቸውን እንዲወጡም ጠይቀዋል።

እድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህፃናት ፣ ያቋረጡ ተማሪዎችና የደገሙ ተማሪዎች በመለየት ወደ ትምህርት ገበታ በማስገባትና መምህራኖች በትምህርት ቤት በመገኘት የመማር ማስተማሩ ስራ በወቅቱ ማስኬድ እንደሚገባም ጠቁመዋል።

በመድረኩም የጉራጌ ዞን ትራንስፖርት እና መንገድ ልማት መምሪያ ኃላፊና የወረዳው ደጋፊ አመራር አቶ የህያ ሡልጣን ፣ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ካሡ ጁሀር ፣ የወረዳው ረዳት የመንግስት ተጠሪ እና የብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙሉጌታ ፈቀደ ጨምሮ አጠቃላይ የወረዳ አመራር ፣ መምህራንና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

ዝርዝር መረጃ ይዘን እንመለሣለን

ዘገባው የአበሽጌ ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት ነው።

ፔጃችን ስለምትከታተሉ እያመሰገንን ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ከታች የተቀመጡትን ሊንኮች በመጫን የተቋማችን የሚዲያ አማራጮችን ይጠቀሙ፡-
‎‎👉://www.facebook.com/profile.php?id=100070918473865&mibextid=kFxxJD

‎👉http://tiktok.com/

‎👉 ቴሌግራም፦ https://t.me/awc567

‎👉 ዩቲዩብ:- https://youtube.com/?si=8HvFtXplAUMiEnmx

‎👉 instagram :-
https://www.instagram.com/abeshigeworeda?igsh=MjQyMXN5bnhkb2d2

‎👉X
https://x.com/AWoreda5717?t=x9hbuUQi9Esw9XahIjQkWQ&s=09

በዞናችን በማንኛውም ጊዜ ለሚከሰቱ ተፈጥሯዊና ሰወ ሰራሽ አደጋዎች በራስ አቅም ለአደጋ ፈጣን ምላሽ ለመስጠት ራስን ማጠናከር እንደሚያስፈልግ የጉራጌ ዞን አስተዳደር ገልጿል።ነሀሴ09/2018(...
15/08/2026

በዞናችን በማንኛውም ጊዜ ለሚከሰቱ ተፈጥሯዊና ሰወ ሰራሽ አደጋዎች በራስ አቅም ለአደጋ ፈጣን ምላሽ ለመስጠት ራስን ማጠናከር እንደሚያስፈልግ የጉራጌ ዞን አስተዳደር ገልጿል።

ነሀሴ09/2018(ወልቂጤ)

በዞኑ እየተካሄደ የሚገኘውን የ120 ቀናት የሰብዓዊ ድጋፍና ራስን የመቻል አቅም ማሳደግ ተግባር ተገምግሟል።

መድረኩን የመሩት የጉራጌ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አበራ ወንድሙ በማንኛውም ጊዜ ለሚከሰቱ ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ አደጋዎች በራስ አቅም ለአደጋ ፈጣን ምላሽ ለመስጠት ራስን ማጠናከር ያስፈልጋል ብለዋል።

ለተጋላጭ የህብረተሰበ ክፍሎች የሰብዓዊ ድጋፍነ ለማድረግ ራስን የመቻል አቅም በትኩረት እየተሰራበት የሚገኝ ስራ መሆኑን ተናግረዋል።

በተፈጥሮና በሰው ሰራሽ አደጋ ተጎጂ የሆኑ ወገኖችን መልሶ ለማቋቋም እና ቤት ንብረታቸው ለወደመባቸው ዜጎች ዘላቂ ድጋፍ ለማድረግ በሀገር አቀፍ የተጀመረውን የ120 ቀናት የሀብት ማሰባስብ ተጠናክሮ ከግብ መድረስ አለበት ብለዋል።

የጉራጌ ዞን ብልጽግና ፓርቲ የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ደሳለኝ ፈቀደ በበኩላቸው በድንገት አደጋዎች ሲከሰቱ ፈጣንና ውጤታማ ምላሽ ለመስጠት የራስ አቅም ለማሳደግ ባለድርሻ ተቋማት ተቀናጅተው ሊሰሩ እንደሚገባ አስረድተዋል።

የዞኑ ማህበረሰብ ከተፈጥሯዊና ሰው ሰራሸ አደጋዎች ለመከላከል የአደጋዎች መፍለቂያዎችን በመለየት የቅድመ ጥንቃቄ ስራዎች መስራት ያስፈልጋል ብለዋል።

በጉራጌ ዞን ግብርና መምሪያ የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ጽሕፈት ቤት ዋና ኃላፊ ወ/ሮ ጊዜወርቅ አለሙ እንደገለጹት ከተረጂነት ወደ ምርታማነት መሸጋገር ችግሮችን ሲገጥሙ በራሰ አቅም ለመቋቋም ፋይዳው የጎላ መሆኑን አስረድተዋል።

በባለፈው በጀት አመት በህብረተሰብም በመንግስት የታየው ከፍተኛ መነቃቀት በዚህ በ120 ቀናት ንቅናቄ መደገም እንደሚገባው ተናግረዋል።

ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥና ኢኮኖሚያዊ አቅምን ለማሳደግ ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ የሚገኘውን የማህበረሰቡን የመረዳዳት ባህል በማጠናከር ለዚህ ተግባር ማዋል እንደሚገባ የውይይቱ ተሳታፊዎች አስተያያታቸውን ሰጥተዋል።

በተፈጥሮና በሰው ሰራሽ አደጋዎች ለተጎዱ ወገኖች በራስ አቅም ምላሽ ለመስጠት አካባቢዎች በሚታወቁበት የሰብል ምርት እንዲያመርቱ በማገዝ የሀብትን ማሰባሰቡን ተግባር ውጤታማ ማድረግ ያስፈልጋል።

መረጃው የጉራጌ ዞን መንግስት ኮ/ጉ/መምሪያ ነው

ባለፉት ሶስት ዓመታት በክልሉ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ እየተደረገ ባለው ጥረት የላቀ ውጤት ተመዝግቧል:- ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር ) ነሐሴ 08/2018(ወልቂጤ) የማዕከ...
14/08/2026

ባለፉት ሶስት ዓመታት በክልሉ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ እየተደረገ ባለው ጥረት የላቀ ውጤት ተመዝግቧል:- ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር )

ነሐሴ 08/2018(ወልቂጤ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር )ክልሉ የተመሰረተበትን 3ኛ ዓመትን በማስመልከት በጽ/ቤታቸው መግለጫ ሰጥተዋል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር ) ለመገናኛ ብዙሀን በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት ባለፉት ሶስት ዓመታት በክልሉ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ እየተደረገ ባለው ጥረት የላቀ ውጤት ተመዝግቧል።

ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ለኢኮኖሚ እድገትና ለምግብ ዋስትና መረጋገጥ መሰረታዊ ጉዳይ ነው ሲሉም ርዕሰ መስተዳድሩ አብራርተዋል።

በክልሉ የግብርናውን ዘርፍ ለማዘመን በተደረገ ጥረት የምርታማነት እድገት እየጨመረ ስለመሆኑም ርዕሰ መስተዳድሩ አመላክተዋል።

አርሶ አደሩ ከዘልማድ የአስተራረስ ዘዴ ወጣ በማለት በገበያ ተኮር የግብርና ልማት ስራዎች ላይ ትኩረት ማድረግ በመቻሉ ኢኮኖሚያዊ አቅሙ እያደገ ስለመምጣቱም ርዕሰ መስተዳድሩ በመግለጫቸው ጠቁመዋል።

የኩታ ገጠም እርሻ ካለው የላቀ ጠቀሜታ አንጻር በአርሶ አደሩ ዘንድ እየተለመደ መምጣቱን ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቅሰዋል።

የአርሶ አደሩ የግብርና መካናይዜሽን ተጠቃሚ ባህሉ እያደገ መምጣቱን ተከትሎ በየጊዜው የምርታማነት እድገት መጨመሩን አንስተዋል።

የዘመናዊ ግብርና ስርዓት የህብረተሰቡን ኑሮ ከማሻሻል ባለፈ በሀገር ኢኮኖሚ ላይ የሚኖረውን ድርሻ ከፍተኛ መሆኑን ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቁመዋል።

በክልሉ በቅመማ ቅመም ዘርፍ የአርሶ አደሩ ተጠቃሚነት እያደገ ስለመሆኑም ርዕሰ መስተዳድሩ አብራርተዋል።

የአየር ንብረት ለውጥ በግብርና ልማት ስራ ላይ የሚያሳድረውን ተጽዕኖ መቋቋም የሚያስችል ስርዓት መዘርጋት መቻሉን ርዕሰ መስተዳድሩ በመግለጫቸው አስታውቀዋል።

በክልሉ የወቅቱ ዝናብ መጠን ማነስ እና መጨመር ስጋት መኖሩን የገለጹት ርዕሰ መስተዳድሩ ለዚህም ልዩ እቅድ በማዘጋጀት እየተሰራ መሆኑን አብራርተዋል።

የተቀናጀ የግብርና ልማት ስራ የአርሶ አደሩን የምግብ ዋስትና ከማረጋገጥ ባለፈ ወደ ገበያ መር አምራችነት እንዲሸጋገርና የኑሮ ደረጃው በዘላቂነት እንዲሻሻል ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለውም አስረድተዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ በመግለጫቸው የአርሶ አደሩን ህይወት ለመለወጥና ዘላቂ የኢኮኖሚ እድገት ለማረጋገጥ የክልሉ መንግስት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው ብለዋል።

ምንጭ፣ የክልሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን

በከተሞች የሚገኙ የመሬት ሀብቶችን ከህገወጥ መሬት ወራሪዎች በመጠበቅ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ ማድረግ እንደሚያስፈልግ የክልሉ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ገለፀ።ነሀሴ 08/2018(ወልቂጤ)በዞ...
14/08/2026

በከተሞች የሚገኙ የመሬት ሀብቶችን ከህገወጥ መሬት ወራሪዎች በመጠበቅ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ ማድረግ እንደሚያስፈልግ የክልሉ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ገለፀ።

ነሀሴ 08/2018(ወልቂጤ)

በዞኑ በሚገኙ ከተማ አስተዳደሮች ህገወጥ የመሬት ወረራን ለመከላከል የንቅናቄ መድረክ በወልቂጤ ከተማ ተካሂዷል።

የጉራጌ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ አበራ ወንድሙ በዞናችን የሚገኙ ከተሞችን ወደ ተሻለ ፈርጅ ከተማ ለማሸጋገር በከተሞች የሚገኙ የመሬት ሀብቶችን ከወራሪዎች የመጠበቅ ስራ በትኩረት ሊሰራበት እንደሚገባ አስረድተዋል።

በከተሞች ህገወጥ የመሬት ወረራዎች እንዳይኖሩ በማዘጋጃ ቤቶች የሚሰሩ በሊዝና በህብረት ስራ ማህበራት ለነዋሪዎች የሚተላለፉ መሬቶች በትኩረትና በጥንቃቄ መስራት እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል።

አቶ አበራ አክለውም ከተሞች በዘላቂነት እንዲለሙና ለኑሮ ተስማሚ የሆኑ እንዲሆኑ ቀደም ሲል የተበላሹትን በማስተካከል መስራት ይጠይቃል ብለዋል።

የክልሉ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ጨምር ኃይሌ እንደተናገሩት በከተሞች የሚገኙ የመሬት ሀብቶችን ከህገወጥ የመሬት ወራሪዎች ለመጠበቅ በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

በተለያዩ ከተሞች የሚታዩ ህገወጥ የመሬት ወረራዎችን ተከታትሎ በህጋዊ መንገድ እርምጃዎችን በመውሰድ መሬቱን ወደ መሬት ባንክ በመመለስ ለልማት እንዲውል መስራት ያስፈልጋል ብለዋል።

በቀጣይም ግብረሃይሉ በከተማ ማዘጋጃ ቤቶች ውስጥ የሚገኙ መሬቶችን በአግባቡ በመለየት ህገወጥ የመሬት ወረራዎችን ለመከላከል በንቃት እንደሚሰራ አቶ ጨምር አክለዋል።

ከነሐሴ 7/2018 ጀምሮ በሁሉም ከተሞች የማስፋፊያና አዲስ የተካለሉ አካባቢዎችን ሳያካትት ከሚካሄድ የስም ዝውውርና ከቤት ህብረት ስራ ማህበራት መሬት ትልልፍ ውጭ ያለ ማንኛውም የመሬትና መሬት ነክ እንቅስቃሴዎች ላልተወሰነ ጊዜ ታግዶ እንደሚቆይም ተናግረዋል።

የጉራጌ ዞን የመንግስት ረዳት ተጠሪ አቶ ፈይሰል ሀሰን በበኩላቸው ንቅናቄው ለከተሞች ማደግ ትልቅ እድል የሚፈጥር በመሆኑ ከተሞች ትኩረት ሰጥተው ሊጠቁሙበት ይገባል።

ህገወጥ የመሬት ወረራን ለመከላከል የተቋቋመው ግብረሃይል የቅንጅት ስራዎችን አጠናክሮ በመስራት የመሬት ወረራዎችን ቀደም ብሎ መከላከል እንደሚያስፈልግ አስረድተዋል ።

የውይይቱ ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት የከተሞች ማስፋፊያ ላይ የሚገኙ የመሬት ሀብቶች ለከፍተኛ የመሬት ወረራዎች ምክንያት እየሆኑ በመሆናቸው ግብረሃይሉ ትኩረት እንዲያደርግበት አሳስበዋል።

በከተሞች የሚታዩትን የህገወጥ መሬት ወረራዎችን በዘላቂነት ለመግታት የህብረት ስራ ማህበራትን መረጃዎች የማጥራት እነዲሁም መመሪያዎችን በአግባቡ መተግበር የትኩረት አቅጣጫ ሊደረጉ ይገባል ብለዋል።

ጠንካራ ፓርቲ የሚገነባው በውስጥ ዲስፕሊንና በተጠያቂነት ነው፦ ዶክተር ዲላሞ ኦቶሬነሀሴ 8/2018 ዓ.ም(ወልቂጤ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የብልጽግና የኢንስፔክሽንና የስነምግባር ኮሚሽን ...
14/08/2026

ጠንካራ ፓርቲ የሚገነባው በውስጥ ዲስፕሊንና በተጠያቂነት ነው፦ ዶክተር ዲላሞ ኦቶሬ

ነሀሴ 8/2018 ዓ.ም(ወልቂጤ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የብልጽግና የኢንስፔክሽንና የስነምግባር ኮሚሽን “ሁለ አቀፍ እምርታ ለሁለንተናዊ ከፍታ'' በሚል መሪ ቃል የ2018 ዓ.ም እቅድ አፈጻጸም ማጠቃለያ ግምገማና የ2019 በጀት ዓመት የእቅድ መድረክ በሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ነው።

በመድረኩ መክፈቻ ላይ የተገኙት በብልጽግና ፓርቲ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ዲላሞ ኦቶሬ (ዶ/ር) ባደረጉት ንግግር፤ የኢንስፔክሽንና ሥነ-ምግባር ዘርፍ የፓርቲውን ጥንካሬ፣ ተቋማዊ አቅም እና የአባላትን እምነት ለማረጋገጥ መሠረታዊ ሚና እንዳለው ገልጸዋል።

የኢንስፔክሽንና ሥነ-ምግባር ሥራ ለአባላትና አመራሮች በሙሉ ያለ አድልዎ፣ በሁሉም ደረጃ በፍትሃዊነትና በተጠያቂነት መተግበር አለበትም ብለዋል።

የኢንስፔክሽን ሥራ ችግር ከተከሰተ በኋላ ብቻ ማጣራት ሳይሆን፣ ቀድሞ ምልክቶችን በማየት ችግሮች እንዳይፈጠሩ ቅድመ መከላከል ሥራ ላይ ትኩረት ማድረግ ይኖርበታል ሲሉም ተናግረዋል።

አክለውም ተቋማዊ መረጃዎችን፣ የጥቆማና የምርመራ ሂደቶችን በዘመናዊ የዲጂታል የመረጃ ሥርዓት መደገፍ ያስፈልጋል ብለዋል።

የኢንስፔክሽን ተቋሙ አቅም በሎጅስቲክስ ብቻ ሳይሆን በጠንካራ አስተሳሰብ፣ በእምነትና በቁርጠኝነት የሚገነባ በመሆኑ የአመራሩ ሥነ-ምግባር ቀዳሚ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል ብለዋል።

ከመድረኩ በበጀት ዓመቱ የታዩ የሥነ-ምግባርና የዲስፕሊን ግድፈቶችንና ችግሮችን በግልጽ መለየት እንደሚገባም ጠቅሰዋል።

በብልጽግና ፓርቲ የኢኒስፔክሽና የስነ ምግባር ኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ አብዱልዋሪስ ጀማል ኮሚሽኑ ከተቋቋመ ወዲህ በርካታ ተግባራትን ማከናወን የቻለ ሲሆን ከክልል ማዕከል እስከ ብልጽግና ህብረት ድረስ የፓርቲው አደረጃጀት ባለበት ሁሉ የኮሚሽኑን አደረጃጀት ተግባራዊ ማድረግ ተችሏል ብለዋል።

የፓርቲው አባላት የፖለቲካ ጥራትና የስነምግባር ጤናማነት ለማረጋገጥ እንዲሁም በተግባር አፈጻጸማቸው ግምባር ቀደም መሪ እንዲሆኑ ከፍተኛ ጥረት ተደርጓል ብለዋል።

ብልፅግና ፓርቲ በኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ ሁሉንም ኢትዮጵያዊያን አንድ ላይ ያሰባሰበ ሀገርአቀፍ ፓርቲ ነው ብለው ፓርቲው በሁለተኛው ጉባኤ ባሻሻለው የፓርቲው መተዳዳሪያ ደንብ ከፓርቲው ተቋማዊ መዋቅሮች አንዱ የኢንስፔክሽንና ስነምግባር ኮሚሽን እንደሆነ ተናግረዋል።

በበጀት አመቱ "ጠንካራ ኢንስፔክሽን ለጠንካራ ፓርቲ'' በሚል ኢንስፔክሽን በማካሄድ በየደረጀው ላለው የፓርቲ አደረጃጀቶች ግኝቶችን ከምክረ ሀሳብ ጋር በመስጠት በብልጽግና ፓርቲ 2ኛ ጉባኤ የውሳኔ አካል የሆነውን ጠንካራ የፓርቲ ተቋም የመገንባት ውጥን እንዲሳካ እሴት በመጨመር አስተዋጾ ማበርከት ተችሏል ብለዋል።

በየደረጃው በሚገኙት የኮሚሽን አደረጃጀቶች መካከል ተቀራራቢ የተግባር አፈጻጸም በማስመዘገብ ረገድ ሙሉ በሙሉ ማጥበብ ያልታቸለ መሆኑ በተለያየ ጊዜ በተደረገ ኢንስፔክሽንና ሱፐርቪዥን ማረጋገጥ ተችሎዋል ስለሆነም በቀጣይ እነዚህን ጉድለቶች ለመሻገር በቁርጠኝነት እንደሚሰራ ተናግረዋል።

መድረኩ በፓርቲው መተደደሪያ ደንብ ለኮሚሽኑ የተሰጡትን ተግባርና ሀላፊነቶች በየደረጀው ካለው የፓርቲ አደረጃጀቶች ጋር በመቀናጀት፣ በትብብር እና በላቀ ትጋት በመፈጸም የፓርቲያችንን ራዕይ 'የኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ብልጽግና˚ እውን እንዲሆን ቃላችንን የምናድስበትም ነው ብለዋል።

መድረኩ እንዲሳካ ላደረጉ፤ ለክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ፣ ለክልሉ ርዕስ መስተዳደር ጽ/ቤት እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ምስጋና አቅርበዋል ሲል የዘገበው የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ነው።

Address

Wolkite
94

Telephone

0113301423

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gurage Zone Abeshige Woreda Communication affairs office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share