Gurage Zone Government Communication Affairs Department

Gurage Zone Government Communication Affairs Department We work hard to build an informed society by providing hot and hard news, articles and documentary films!

በመስኖ ተቋማት ልማት አስተዳደር ኤጀንሲ በምግብ ስርአት ማጠናከሪያ ፕሮግራም (FSRP) በጀት ድጋፍ በሶስት የፕሮግራሙ ወረዳዎች ምዕራብ አዘርነት በርበሬ፣ ጉመርና ሶዶ ወረዳዎች በፋክት አማ...
03/09/2026

በመስኖ ተቋማት ልማት አስተዳደር ኤጀንሲ በምግብ ስርአት ማጠናከሪያ ፕሮግራም (FSRP) በጀት ድጋፍ በሶስት የፕሮግራሙ ወረዳዎች ምዕራብ አዘርነት በርበሬ፣ ጉመርና ሶዶ ወረዳዎች በፋክት አማካሪ ድርጅት የተጠኑ የሶስት አነስተኛ የመስኖ ግድቦች ዝርዝር ጥናትና ዲዛይን ለመገምገም የውይይት መድረክ በወልቂጤ ከተማ እየተካሄደ ነው።

ነሀሴ 28/2018ዓ.ም(ወልቂጤ)

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመስኖ ተቋማት ልማትና አስተዳደር ኤጀንሲ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ካሳዬ ተክሌ እንዳሉት በመስኖ ዘርፍ በተናጥል መስራት ውጤት ሊያመጣ እንደማይችል አንስተው፤ ከግብርና፣ ከመስኖ፣ ከውሃና ከሌሎችም ተቋማት በመቀናጀት ውጤታማ ስራ መስራት ይገባል።

የምግብ ስርአት ማጠናከሪያ ፕሮግራም (FSRP) በክልሉ በዘርፉ በርካታ የልማት ስራዎች ሲሰራ መቆየቱንም ተናግረዋል።

በዛሬው እለት እየተገመገሙ ያሉ የመስኖ ፕሮጀክቶች 7መቶ 80 ሄክታር መሬት ሊያለሙ የሚችሉ መሆናቸውንም አንስተዋል።

በፌደራል ግብርና ሚኒስቴር የምግብ ስርአት ማጠናከሪያ ፕሮግራም ማስተባበሪያ ዩኒት ኢንጂነር ያለው በለጠ በበኩላቸው፥ የምግብ ስርአት ማጠናከሪያ ፕሮግራም (FSRP) በ2004 ዓ.ም የግብርና እድገት ፕሮግራም በሚል ስያሜ እንደጀመረ ጠቁመው፤ ይህ ፕሮግራም በአሁኑ ወቅት በዘርፉ በርካታ የልማት ስራዎች እያከናወነ ይገኛል።

እነዚህ የተጠኑ የመስኖ ፕሮጀክቶች ውጤታማ እንዲሆኑ በዘርፉ ሁሉም የሚመለከታቸው አካላት በትኩረት መስራት እንዳለባቸውም አመላክተዋል።

በግምገማ መድረኩም ከፌደራል፣ የክልሉ የግብርና ቢሮ የስርአት ምግብ ማጠናከሪያ ፕሮግራም አስተባባሪዎችና ባለሙያዎች፣ የመስኖ ተቋማት ልማትና ኤጀንሲ የማኔጅመንት አካላትና የጥናትና ዲዛይን ከፍተኛ ባለሙያዎች፣ ጥናቱ ያጠኑ አካላትና ሌሎችም ተገኝተዋል።

03/09/2026

የጉራጌ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ የ2018 ሴክቶሪያል ጉባኤ

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት፣"በሀገራችን የመጀመሪያውን የተለየ የቤት መግዣ ብድር መልሶ ማጠናከሪያ ኩባንያ ለማቋቋም የሚያስችለውን ታሪካዊ የትብብር ማዕቀፍ፤ የኢትዮጵ...
03/09/2026

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት፣

"በሀገራችን የመጀመሪያውን የተለየ የቤት መግዣ ብድር መልሶ ማጠናከሪያ ኩባንያ ለማቋቋም የሚያስችለውን ታሪካዊ የትብብር ማዕቀፍ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን (IFC) መካከል ስምምነት ዛሬ አከናውነናል።

‎በ100 ቢሊዮን የኢትዮጵያ ብር ካፒታል የተቋቋመው እና በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን ደግሞ 200 ሚሊዮን ዶላር የሚደርስ አስተዋፅኦ የሚያደርግበት ይህ ተቋም፤ በባንክ ዘርፋችን ውስጥ የጥሬ ገንዘብ ፍሰት አለመመጣጠንን የሚቀርፍ እና በመላው ኢትዮጵያ ተደራሽ የሚሆን የቤት መግዣ ብድር ፋይናንስን የሚያስገኝ ይሆናል።

‎ይህ አጋርነት በተመጣጣኝ ዋጋ የሚገነቡና የኢትዮጵያውያንን ክብር የጠበቁ 1.5 ሚሊዮን ቤቶችን ለማቅረብ እንዲሁም በፋይናንስ ሥርዓታችን ውስጥ የግል ዘርፉን ተሳትፎ ለማስፋት ያስቀመጥነውን ግብ የሚያሳካ ወሳኝ እርምጃ ነው።
‎ኢትዮጵያ ፈጣን፣ ጠንካራ እና ሁሉንም ያካተተ ኢኮኖሚ መገንባቷን ትቀጥላለች።"

03/09/2026

የጉራጌ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ የ2018 ሴክቶሪያል ጉባኤ በወልቂጤ ከተማ እያካሄደ ይገኛል።

የተቀናጀ የከተማ ግብርና ለእምድብር ከተማ ነዋሪዎች የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትና የሥራ ዕድል ምንጭ መሆኑን ጉራጌ ዞን አስተዳደር አስታወቀ።ነሀሴ 27/2018(ወልቂጤ )በባህርዛፍና  በጫካ የተወረረ...
02/09/2026

የተቀናጀ የከተማ ግብርና ለእምድብር ከተማ ነዋሪዎች የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትና የሥራ ዕድል ምንጭ መሆኑን ጉራጌ ዞን አስተዳደር አስታወቀ።

ነሀሴ 27/2018(ወልቂጤ )

በባህርዛፍና በጫካ የተወረረ መሬታችን በማጽዳት ወደ ተቀናጀ የግብርና ማሳ ቀይረን ሀብት መፍጠር ችለናል ሲሉ የእምድብር ከተማ ወጣቶች ተናገሩ።

የጉራጌ ዞን ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በእምድብር ከተማ እየተሰሩ ያሉ የግብርና ልማት ስራዎች ተዛዙረው ጎብኝተዋል።

የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ እንደገለፁት የተቀናጀ ግብርና ለእምድብር ከተማ ነዋሪዎች የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትና የሥራ ዕድል ምንጭ መሆኑን ተናግረዋል።

በእምድብር ከተማ በየጊዜው አዳዲስ የግብርና ስራዎች በመሰራታቸው ምርታማነትን በላቀ ሁኔታ እንዲፈጸም እያስቻሉ በመሆኑ ተግባሩን አድንቀዋል።

ወጣቶች የትኛውም ስራ ሲጀምሩ የአመለካከት ለውጥ ማድረግ ከቻሉ ውጤታማ መሆን እንደሚቻል በከተማው በግብርና ዘርፍ የተሰማሩ ወጣቶች ምሳሌ መሆናቸውም ተናግረዋል።

አቶ ላጫ አክለውም በግብርና ዘርፍ ለተሰማሩ አምራቾች አስፈላጊውን ሁሉ ድጋፍ እንዲደረግላቸው መክረው በእምድብር ከተማ የታዩ ሞዴል ስራዎች በሁሉም መዋቅሮች አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል ሲሉ አሳስበዋል።

የጉራጌ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አበራ ወንድሙ እንደገለፁት እምድብር ከተማ የሚገኙ ወጣቶች ሞዴል የግብርና ስራዎች በመስራት ውጤታማ እየሆኑ ነው።

ወጣቶች ተምረው ከመቀጠር ይልቅ ግብርናን አዋጭ የስራ ዘርፍ በማድረግ ሀብት እያፈሩበት ያለ ስራ መሆኑን ጠቁመው የእምድብር ከተማ ወጣቶች የዚህ ምሳሌ ናቸው ብለዋል።

ከተማው በተቀናጀ ግብርናና በሌማት ትሩፋት ስራ በክልሉም ግንባር ቀደም ስራዎች በመስራት ለሌሎች አስተማሪ የሚሆኑ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑ ጠቁመዋል።

አቶ አበራ አክለውም መምሪያውም የክትትልና ድጋፍ ስራዎች በመስራት፣የግብርና ግብአት በማቅረብ፣አርሶ አደርና ባለሙያው በማሰልጠንና የግብርና ኢኒሼቲቮች ተግባራዊ በማድረግ አበረታች ውጤቶች እየተመዘገቡ እንደሚገኝ አስገንዝበዋል።

የእምድብር ከተማ ከንቲባ አቶ ግንባሩ በርጋ በከተማው እየተከናወኑ የሚገኙ የተቀናጀ ግብርናና የሌማት ትሩፋት ሥራዎች የነዋሪዎችን የኑሮ ሁኔታ እያሻሻሉ መሆኑን ገልጸዋል።

የከተማው መንግስትም በግብርና የተሰማሩ ነዋሪዎች የሥራ አቅማቸውን እንዲያሳድጉ የመሬትና የብድር አቅርቦትን ከማመቻቸት ባለፈ የሙያ ድጋፍና ሌሎች አስፈላጊ ድጋፎችን በማጠናከር ላይ መሆኑን ገልጸዋል።

አቶ ግንባሩ አክለውም በከተማው በተቀናጀ ግብርና የሚከናወኑ ሥራዎች የምግብ ምርትን ከማሳደግ ባለፈ የገቢ ምንጭን በማስፋትና የሥራ ዕድልን በመፍጠር የነዋሪዎችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ የሚያግዝ መሆኑ ጠቁሟል።

የከተማው ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ወለላ ሸምሱ እንዳሉት በከተማው በባህርዛፍ የተሸፈኑ መሬቶችን በማስለቀቅ በቡና በአትክልትና ፍራፍሬ ተቀይሯል።

በከተማው በዘንድሮ አመትም ከ2መቶ 15 ሺ በላይ የቡና ችግኞች መተከላቸውን ጠቅሰዋል።

ወጣት አዳነ ሹሜ፣ ወጣት ዳዊት ትዛዙና አቶ ሰይፈ ፍራንሷ የእምድብር ከተማ ነዋሪዎች ሲሆኑ በግብርና ዘርፍ በመሰማራት የተለያዩ የግብርና ምርቶችን በማምረት ለገበያ እያቀረቡ ይገኛሉ።

ወጣቶቹ በመጀመሪያ በግብርና መለወጥና ራስን በራስ መቻል እንደሚቻል የአመለካከት ለውጥ ማድረጋቸውን ገልጸው፣ በባህርዛፍና በጫካ የተወረረ መሬትን በማጽዳት ወደ ምርታማ የተቀናጀ የግብርና ማሳ መቀየራቸውን አብራርተዋል።

በማሳውም ዝንጅብል፣ ቡና፣ ሙዝ፣ እንሰት፣ አቮካዶ፣ ኮረሪማና ሌሎች የግብርና ምርቶችን በስፋት በማምረት ለገበያ እያቀረቡ መሆናቸውን ተናግረዋል።

በቤተሰብና በግል በመደራጀት ከመንግስት ያገኙትን ውስን የገንዘብ ድጋፍ ወደ ሥራ በማስገባት አሁን ላይ በሚሊዮን የሚቆጠር ገቢ ማስገኘት መቻላቸውን ገልጸዋል።

የከተማውና የዞኑ መንግስት እያደረገላቸው የሚገኘው የተለያዩ ድጋፎች ለስኬታቸው የሚጫወተው ሚና ከፍተኛ መሆኑን የገለጹት ነዋሪዎቹ፣ የመሬት አቅርቦትና ሌሎች ድጋፎች እንዲጠናከሩላቸው ጠይቀዋል።

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟላ መረጃዎችን ለማግኘት ከታች የተቀመጡ ሊኮች በመጫን የተቋማችንና ሌሎች የሚዲያ አማራጮችን ይጠቀሙ፡-👇

ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/gurage1Zone
ፌስቡክ ጉራግኛ፦https://www.facebook.com/profile.php?id=61582123942054
Website:- https://gurage.gov.et
Telegram:- https://t.me/comminuca
ቲዊተር፡-https://x.com/GurageT17420?t=zgBzoBE_oQSZbQUbAbPYMw&s=09
በYoutub:-https://www.youtube.com/-u8y4y
በቲክቶክ:-https://vm.tiktok.com/ZMrYn7vV5/
በኢንስታግራም:-https://www.instagram.com/gurage_zone_gov.tcommunication?igsh=MTM3eDV2dms5YTg0Zw==
Whatsapp፦https://chat.whatsapp.com/KYIxtaMxPs77YwugtSq7oF?mode=hqctcla

በዞኑ እንደ ሸረሪት ድር የተሳሰሩት መንገዶች አርሶ አደሮች ያመረቱት ምርት ደጃፋቸው ላይ ሆነው እንዲሸጡ እያስቻላቸው ይገኛል።ነሐሴ27/2018(ወልቂጤ)በጉራጌ ዞን ባለፉት ሶስት አመታት ብቻ...
02/09/2026

በዞኑ እንደ ሸረሪት ድር የተሳሰሩት መንገዶች አርሶ አደሮች ያመረቱት ምርት ደጃፋቸው ላይ ሆነው እንዲሸጡ እያስቻላቸው ይገኛል።

ነሐሴ27/2018(ወልቂጤ)

በጉራጌ ዞን ባለፉት ሶስት አመታት ብቻ ከ1ሺህ ኪሎ ሜትር በላይ የጠጠር መንገዶች በመንግስት በማህበረሰቡና በባለሀብቱ ተሳትፎ ተሰርተዋል፤ በዚህም ዘርፈ ብዙ የአርሶ አደሮቻችን ችግሮች ተፈተዋል።

በዞኑ እኖር ወረዳ ለማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የፍራፍሬ ዘር ምንጭ እየሆነ ይገኛል!!

የጉራጌ ዞን ህብረት ስራ ልማት ጽህፈት ቤት መሰረታዊ ህብረት ስራ ማህበራትን ከአድማስ የገበሬዎች ህብረት ስራ ዩኒየን ጋር በማቀናጀት ለክልሉ ግብርና ቢሮ ለዘር ምንጭ የሚሆን የአቮካዶ ምርት እንዲቀርብ እያደረገ ይገኛል።

አድማስ ዩኒየን በመጀመሪያ ዙር 80 ኩንታል ለዘር ምንጭነት የሚያገለግል የአቮካዶ ምርት ከእኖር ወረዳ ጋሳውዴ የሮዝመሪና የፍራፍሬ ምርት አምራች መሰረታዊ ህብረት ስራ ማህበር ተረክቦ ያሰራጨ ሲሆን በሁለተኛ ዙርም 240 ኩንታል ምርትን ተረክቦ በክልሉ ለሚገኙ ወረዳዎች አሰራጭቷል።

የጠነከረ የአረንጓዴ አሻራ ልማት ስራ ውጤት የሆነው የአቮካዶ ምርት የአርሶ አደሩን የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባሻገር የገቢ አቅማቸውን እያሳደገ ይገኛል።

የጉራጌ ዞን ህብረት ስራ ልማት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ነስሩ ስራኒ እንደገለፁት በዞኑ 155ሺህ 610 አባላት ያሏቸው 790 መሰረታዊ ህብረት ስራ ማህበራት መኖራቸው ገልፀው ማህበራቱ የአባሎቻቸውና የራሳቸውን አቅም እንዲያሳድጉ ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን አብራርተዋል።

በእምድብር ከተማ እየተሰሩ ያሉ የልማት ስራዎች የከተማው እድገት የሚያፋጥኑና የመልካም አስተዳደር ችግሮች የሚፈቱ ናቸው፦ ክቡር አቶ ላጫ ጋሩማነሀሴ 27/2018(ወልቂጤ)የጉራጌ ዞን ዋና አስ...
02/09/2026

በእምድብር ከተማ እየተሰሩ ያሉ የልማት ስራዎች የከተማው እድገት የሚያፋጥኑና የመልካም አስተዳደር ችግሮች የሚፈቱ ናቸው፦ ክቡር አቶ ላጫ ጋሩማ

ነሀሴ 27/2018(ወልቂጤ)

የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ላጫ ጋሩማ ጨምሮ የዞኑ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በእምድብር ከተማ በ26 ሚሊየን ብር ወጪ የተደረገባቸው ፕሮጀክቶች መርቀው ለአግልግሎት ክፍት አደረጉ።

የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ላጫ ጋሩማ እንዳሉት ዛሬ የተመረቁት የመሠረተ ልማት ሥራዎች የህብረተሰቡን ችግሮች በተጨባጭ ለመፍታት የሚያስችሉና የኑሮ ሁኔታን የሚያሻሽሉ ናቸው።

በተለይም የከተማው ኮሪደር ልማት ደረጃውን የጠበቀ፣ በስፋትና በጥራት የተሻለ በመሆኑ ከተማዋን ወደተሻለ የእድገት ደረጃ የሚያሸጋግር መሆኑን አቶ ላጫ ጋሩማ ጠቁመዋል።

በተጨማሪም የአንድ ከተማ አንድ ፕሮጀክት አካል የሆነው የትምህርት ቤት ግንባታ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ጉልህ ሚና እንደሚኖረው ገልጸዋል።

የተከናወኑት ሥራዎች ለወጣቶች የሥራ ዕድል ከመፍጠር ባለፈ፣ በምርጫ ወቅት ለህዝቡ የተገቡ ቃሎችን በተግባር ለመፈጸም እያስቻሉ መሆናቸውንም ዋና አስተዳዳሪው አስረድተዋል።

የጉራጌ ዞን ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ናስር ሀሰን በእምድብር ከተማ በፓርተዉ ኢኒሼቲቭ የሚወርዱ ተግባራት ተጨባጭ ውጤት እየታየባቸው ይገኛል ብለዋል።

የከተማ የመሰረተ ልማትና የተቀናጀ ግብርና በተግባር የተረጋገጠበት ነው ያሉት አቶ ናስር በከተማ እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ለዞኑ ከተሞች ልምድ የሚወሰድባቸው በመሆናቸው ሊሰፉ እንደሚገባ መክረዋል።

የእምድብር ከተማ ከንቲማ አቶ ግንባሩ በርጋ በበኩላቸው በከተማው በየጊዜው በስፋትና በጥራት እየተሰሩ ያሉ የልማት ስራዎች የህብረተሰቡን እምነት እንዲጨምርና የህብረተሰቡ ተጠቃሚነት እያረጋገጡ ይገኛል።

በዛሬው እለት የተመረቁ 5 የዲች ሳይቶች ፣አንድ የኮብልስቶን ፣የአንድ ከተማ አንድ ፕሮጀክት አካል የሆነው አንድ ትምህርት ቤት በአጠቃላይ በ26 ሚሊየን ብር ወጪ የተደረገባቸው ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት ክፍት ሆነዋል ብለዋል።

አቶ ግንባሩ አክለውም በከተማው በመንግስትና በህብረተሰቡ የጋራ ቅንጅት 5 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ስራ ለመስራት ታቅዶ 3 ኪሎ ሜትሩ በጥሩ ሁኔታ እየተከናወነ እንደሚገኝ አስታውቋል።

የመንግስት እና የማህበረሰቡ አቅም በማስተባበር እምድብር ከተማን ከአቻ ከተሞች እንድትሰልፍ በትኩረት ይሰራል ሲሉ ከንቲባው ገልጸዋል።

አቶ ፍቅሬ ብዛ እና ወጣት ዘመቻ አስፋው የእምድብር ከተማ ነዋሪዎች ሲሆኑ ዛሬ የተመረቁ በተለይ የዲች ፕሮጀክቶቸ ለብዙ አመታት ለጎርፍ ተጋላጭ አድርጎዋቸው እንደነበር ገልጸዋል።

በከተማው የሚሰሩ የልማት ስራዎች በየጊዜው እያደጉ እና የከተማው ገጽታ እየተቀየረ ሲሆን እነሱም በገንዘብ፣በጉልበትና በሀሳብ ድጋፋቸው ከፍተኛ እንደሆነ አብራርተዋል።

በእምድብር ከተማ የተጀመሩ እና የታቀዱ የልማት ስራዎች እንዲፈጸሙ በትኩረት እንሰራለን ሲሉ ተናግረዋል።

02/09/2026

የጉራጌ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅርጫፍ ጽህፈት ቤት የሴቶች ክንፍ አደረጃጀት አባላት በሀላባ ዞን ሀላባ ቁሊቶ ከተማ በሜጦማ ቀበሌ በመገኘት ወሰን ተሻጋሪ ሰው ተኮር የበጎ አድራጎት ስራዎችን ለማከናወን በተገኙበት ወቅት የነበረው አቀባበል።

Address

Wolkite

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gurage Zone Government Communication Affairs Department posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Gurage Zone Government Communication Affairs Department:

Shortcuts

Share