Gurage Zone Finance Department

Gurage Zone Finance  Department Gurage Zone Finance Department

02/06/2026

በ7ተነ የገን ሽፗቸ የጉራጌ ሐልቅ በዞንዌ ብንም የሽፗቸ ጣቢያ በጋት ተረከበም ወሸብት ቀነሰም።

አታት ቲሸብቶ ያዝራጘነዮ ሰብ የባሮሐማ በቀጥወ አምስት ዘበር ገን ያትረቅ፣ ሽናትም ዝፓና ያቸንደቴ የባረዊ ፓርቲ ሸፐቶም።
በሽፗቸሁና ንቅ ሳና የተሰማኖሐማ ኦዶም።

የካልም (CALM) ፕሮግራም የሂሳብ መዝጊያ የምክክር መድረክ በወልቂጤ ከተማ ተካሄደወልቂጤ (ግንቦት 17/2018 ዓ.ም)፦ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፋይናንስ ቢሮ አስተባባሪነት፣ የካልም (...
25/05/2026

የካልም (CALM) ፕሮግራም የሂሳብ መዝጊያ የምክክር መድረክ በወልቂጤ ከተማ ተካሄደ
ወልቂጤ (ግንቦት 17/2018 ዓ.ም)፦ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፋይናንስ ቢሮ አስተባባሪነት፣ የካልም (CALM) ፕሮግራም የመጀመሪያ ምዕራፍ ማጠቃለያ የሂሳብ መዝጊያ የምክክር መድረክ በወልቂጤ ከተማ በስኬት ተካሂዷል።

ከ2012 ዓ.ም ጀምሮ በዓለም ባንክ የ5 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ሲተገበር የቆየውና የአየር ንብረት አፈጻጸም፣ ተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ እንዲሁም የመሬት አስተዳደር ላይ የሚያተኩረው ይህ ታላቅ ፕሮግራም እስከ ሰኔ 30/2018 ዓ.ም ሙሉ በሙሉ የሚጠቃለል ይሆናል።
የመድረኩ ዋና ዋና መልዕክቶች፦

&, የተመዘገቡ ስኬቶች፦ ፕሮግራሙ በክልሉ በሚገኙ 409 የህብረት ሥራ ማህበራት ላይ ያተኮሩ ዘላቂ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎችን ያከናወነ ሲሆን፣ ለአርሶ አደሮችም የመሬት ባለቤትነት ማረጋገጫ ሰርተፍኬት በመስጠት ረገድ ትልቅ አሻራ አሳርፏል።

$, ለፋይናንስና ኦዲት የተሰጠ አቅጣጫ፦ የፕሮግራሙን የመጀመሪያ ምዕራፍ በይፋ ለመዝጋት የሂሳብ አሰራር ክፍተቶችን በፍጥነት መሙላት እና የውስጥ ኦዲተሮች የፕሮጀክቱን በጀትና ንብረት በጥብቅ ቁጥጥር ኦዲት ማድረግ እንዳለባቸው አጽንኦት ተሰጥቶበታል።

$,የጋራ ቁርጠኝነት፦ በመድረኩ የተገኙ ባለድርሻ አካላት የሂሳብ መዛግብትን በወቅቱ መዝጋት ለፕሮጀክቱ ውጤታማነት ወሳኝ መሆኑን በመረዳት፣ የተሰጣቸውን የቤት ሥራ ከተቀመጠው የጊዜ ገደብ (እስከ ሰኔ 30) በፊት ለማጠናቀቅ ወደ ተግባር መግባታቸውን አረጋግጠዋል።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት ፋይናንስ ቢሮ አስተባባሪነት፣ የሒሳብ መዝጊያ ዋና ዋና የአስፈጻሚዎች ተግባራት መግለጫ ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ በወልቂጤ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል። ...
25/05/2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት ፋይናንስ ቢሮ አስተባባሪነት፣ የሒሳብ መዝጊያ ዋና ዋና የአስፈጻሚዎች ተግባራት መግለጫ ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ በወልቂጤ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።

ግንቦት 17/2018 ዓ.ም (ወልቂጤ)

የካልም ፕሮግራም በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በ13 ወረዳዎችና በአንድ ልዩ ወረዳ እየተፈፀመ ይገኛል።

ፕሮግራሙ በጉራጌ ዞን 10 ወረዳዎች ፣በየም ዞን 3 ወረዳዎች እንዲሁም የቀቤና ልዩ ወረዳን
ተጠቃሚ እያደረገ ይገኛል።

የካልም ፕሮግራም በክልሉ በሺዎች የሚቆጠሩ አርሶ አደሮች ተጠቃሚ ከማድረጉም በላይ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎች ላይ ውጤት እያስገኘ ይገኛል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፋይናንስ ቢሮ የቻናል አንድ ፕሮግራሞች ዳይሮክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ታረቀኝ ኑራሞ የውይይቱ ሰነድ ባቀረቡበት ወቅት እንዳሉት የካልም ፕሮግራም ውጤት ተኮር ፕሮግራም ነው ብለዋል።

የፕሮግራሙ ሂሳብ በታቀደለት ጊዜ በጥራት እንዲዘጋ ለማድረግ ተሳታፊዎች እንደ ዘርፋቸዉ በሚገኙ አስፈጻሚ አካላት ከፍተኛ ጥረት እና ክትትል ማድረግ ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።

በውይይቱ ላይ የጉራጌ ዞን፣ የም ዞን እና የቀቤና ልዩ ወረዳ የፋይናንስ ፣ የመንግስት ፋይናንስ ዘርፍ ሀላፊዎች የኦዲት፣ የክፍያ የግዢ እና የንብረት አስተዳደር ባለሙያዎች ፣ የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም የተፈጥሮ ሀብት እና የህብረት ስራ ልማት ጽህፈት ቤቶች የፕሮግራሙ ፎካሎች ፣ እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላት በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።

የዞኑ ወጣቶች በአካባቢያቸው ሰርተው እንዲለወጡ የጀመርነው ሁሉን አቀፍ ድጋፍ አጠናክረን እንቀጥላለን፦ክቡር አቶ ላጫ ጋሩማግንቦት 11/2018 (ወልቂጤ)፦የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አ...
19/05/2026

የዞኑ ወጣቶች በአካባቢያቸው ሰርተው እንዲለወጡ የጀመርነው ሁሉን አቀፍ ድጋፍ አጠናክረን እንቀጥላለን፦ክቡር አቶ ላጫ ጋሩማ

ግንቦት 11/2018 (ወልቂጤ)፦የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ላጫ ጋሩማ በወልቂጤ ከተማ ጉብሬ ክፍለ ከተማ የስራ ፈጠራ አርዓያ የሆነው የወጣት እንዳለ በንቲ የወተት ከብት እርባታ ጎበኙ።

ወጣቶች ከራሳቸው አልፈው ሌሎች ዜጎችን የስራ እድል ተጠቃሚ ለማድረግ በቁርጠኝነት መስራት እንዳለባቸው ተጠቁሟል።

የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ላጫ ጋሩማ በጉብኝት ወቅት እንደገለፁት ወጣቶች ከራሳቸው አልፈው ሌሎች ዜጎችን የስራ እድል ተጠቃሚ ለማድረግ በቁርጠኝነት መስራት ይጠበቅባቸዋል።

የዞኑ ወጣቶች በአካባቢያቸው ሰርተው እንዲለወጡ ሁሉን አቀፍ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ነን ያሉት ክቡር አስተዳዳሪው ወጣቶች በተለያዩ የስራ ዘርፎች በመሰማራት የኢኮኖሚ አቅማቸው ለማሳደግ መንግስት የመስሪያ ቦታ፣ የብድርና ሙያዊ ድጋፍ እንዲያገኙ እየሰራ እንደሆነም ገልፀዋል።

ወጣት እንዳለ በንቲ በቁርጠኝነትና በትጋት ከሰሩ መለወጥ እንደሚቻል በተግባር ያሳየ ፣ ለሌሎች ስራ አጥ ወጣቶች ትልቅ ማሳያና አርዓያ የሚሆን ስራ ፈጣሪ መሆኑን ገልፀዋል።

ወጣቱ በ3 ዓመት ጊዜ ያስመዘገበው ካፒታል ከፍተኛ ሲሆን እርባታውን ይበልጥ ለማስፋፋት ቦታ ከማመቻቸት ጀ@ምሮ ሌሎች ተጨማሪ ድጋፎችም እንዲደረግለት አሳስበዋል።

አስተዳዳሪው አክለውም መሰል ጠንካራና ውጤታማ ወጣቶችን የመደገፍና የማበረታታት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።

የዞኑ ወጣቶች ከመሰደድ፣ ስራን ከማማረጥና ካላስፈላጊ ሱሶች በመራቅ የጉራጌ እሴት የሆነውን የትኛውንም ስራ ሰርቶ የማደግ ማንነትን ሊያስቀጥሉ ይገባል ብለዋል

ወጣት እንዳለ በንቲ በበኩሉ ስራውን ለመጀመር 300 ሺህ ብር ከኦሞ ባንክ ተበድሮ እንደነበር አስታውሶ በሂደት በነበረው ጠንካራ የስራ ዲሲፕሊንና ቁርጠኝነት በአሁኑ ወቅት የኢንተርፕራይዙ አጠቃላይ ካፒታል 5 ሚሊዮን ብር ማድረስ መቻሉን ገልጿል።

በአካባቢው የሚስተዋለው የወተት አቅርቦት እጥረት ለመቅረፍ በመነሳሳት በወተት ከብት እርባታ መሰማራቱንም ገልጿል።

በሶስት የወተት ከብት የተጀመረው እርባታ እየተስፋፋ በመምጣቱን በዘርፉ ይበልጥ ተጠቃሚ ለመሆን የድለባ ስራ መጀመሩንም ተናግሯል።

ወጣቱ በአሁኑ ጊዜ በቀን እስከ 230 ሊትር ወተት እንደሚያመርትና በእምድብና በወልቂጤ ከተሞች በሚገኙ የሽያጭ ማዕከሎቹ ለተጠቃሚዎች እንደሚያቀርብ ተናግሯል።

በመሆኑም በአሁን ወቅት የከብቶቹ ቁጥር 30 መድረሱን እና የወተት ከብት እርባታና ድለባ ስራ በማስፋፋት የገበያ ክፍተት መሙላት እንዲችል ተጨማሪ የስራ ቦታ እንዲመቻችለት ጠይቋል።

አክሎም ወጣቱ ከተመዘገበው የሀብት እድገት ባለፈ፣ ለአካባቢው ነዋሪዎችና ወጣቶች ቋሚና ጊዜያዊ የስራ እድል መፍጠር በመቻሉ ትልቅ ኩራት እንደሚሰማው ተናግሯል።

በጉብኝቱ ወቅት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ዘይቱና ኢብራሂም ጨምሮ የክልል የዞንና ሌሎች እንግዶች ተሳትፈዋል።
Gurage Zone Finance Department

ሚያዝያ 11/2018 በጉራጌ ዞን ፋይናንስ መምሪያ በሚያዝያ ወር የተሰሩ ስራዎች ወይይት ተደርጎዋል!!በውይይቱ የተገኙ የምመሪያው ምክትል ሀላፊ ሳሊም ሸምሱ እንደገለፁት፦ከክልል ፋይናንስ ቢሮ...
19/05/2026

ሚያዝያ 11/2018 በጉራጌ ዞን ፋይናንስ መምሪያ በሚያዝያ ወር የተሰሩ ስራዎች ወይይት ተደርጎዋል!!

በውይይቱ የተገኙ የምመሪያው ምክትል ሀላፊ ሳሊም ሸምሱ እንደገለፁት፦ከክልል ፋይናንስ ቢሮ ለወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች 141.4 ሚሊዮን ብር፣ ለዞን ማዕከል ደግሞ 12.3 ሚሊዮን ብር በጀት በወቅቱ መተላለፉ ገልፀው።የጤናና የትምህርት (WASH) ፕሮጀክቶች አፈጻጸም ላይ ጠንካራ የክትትል ስራ ተሰርቷል።ከ3 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ የተሽከርካሪ መለዋወጫዎች ግዢ ተፈጽሟል።
በቀጣይ ቀሪ ወራት በትጋት ተጠናክረን መስራተ አለብን ብለዋል።

 #የጉራጌ ዞን ፋይናንስ መምሪያ የሚያዝያ ወር የዕቅድ አፈጻጸም  ውይይት ተደረገ።ወልቂጤ   ሚያዝያ,  11/2018 በመምሪያችን የግዢና ንብረት አስተዳደር፣ የበጀት እና የሂሳብ ስራዎች እን...
19/05/2026

#የጉራጌ ዞን ፋይናንስ መምሪያ የሚያዝያ ወር የዕቅድ አፈጻጸም ውይይት ተደረገ።

ወልቂጤ ሚያዝያ, 11/2018
በመምሪያችን የግዢና ንብረት አስተዳደር፣ የበጀት እና የሂሳብ ስራዎች እንዲሁም የኦዲትና ድጋፍ ተግባራት በስኬት ተከናውነዋል። በወሩ ከተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት መካከል፡-
~ለተለያዩ ሴክተሮች አገልግሎት የሚውሉ ላፕቶፖች፣ ፕሮጀክተሮች እና ፕሪንተሮች ግዢ ተፈጽሞ ገቢ ሆነዋል።
~ከ3 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ የተሽከርካሪ መለዋወጫዎች ግዢ ተፈጽሟል።
~ለዞኑ የሚዲያ ጣቢያ ማቋቋሚያ የሚሆኑ ቁሳቁሶች ግዢ ሂደት ተጀምሯል።
~ለከተማ ልማት መምሪያ በ2.2 ሚሊዮን ብር የፕላን ፕሎተር ማሽን ተገዝቷል።
~የአካል ጉዳተኞችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ 2 የኤሌክትሪክ ሞተር ሳይክሎች በ569 ሺህ ብር ተገዝተው ተከፋፍለዋል።
~በዞን ደረጃ ያረጁ ንብረቶችን በማሰባሰብ እና በጨረታ በመሸጥ ከወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች በድምሩ 2,971,808 ብር ገቢ ተሰብስቧል።
~የፋይናንስ ግልጸኝነትን ለማረጋገጥ በተደረገው የኦዲት ስራ፣ በግኝት የታየ 17,470 ብር ተመላሽ እንዲሆን ተደርጓል።
~በወረዳዎች ለሚታዩ የፔይሮል (Payroll) እና የአይቤክስ (IBEX) ሲስተም ችግሮች የቴክኒክ ድጋፍ ተሰጥቷል።
#ለተሻለ ውጤት በጋራ እንሰራለን!!!@

12/05/2026

ከ950 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ በ5330 ካሬ ሜትር ስፋት ላይ የሚገነባው "ኬር ሎጅ" ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ የሚይዘው ምስል!!

በኬር ኢንቨስትመንት የሚገነባው ሎጅ ለከተማው ልዩ ድምቀት ይሆናል ተብሎ የሚጠበቀው፤ ደረጃውን የጠበቀ B+G+8 ህንፃን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ አገልግሎት ያላቸው ሌሎች ግንባታዎች ይኖሩታል ተብሎ ይጠብቃል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያዊ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ለሎጅ ግንባታ የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ሥነ-ስርዓት እየተካሄደ ነው...
12/05/2026

የማዕከላዊ ኢትዮጵያዊ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ለሎጅ ግንባታ የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ሥነ-ስርዓት እየተካሄደ ነው።

በ5330 ካሬ ሜትር ስፋት ላይ የሚገነባው ፕሮጀክት በኬር ኢንቨስትመንት የሚገነባው "ኬር ሎጅ" ግንባታ የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ሥነ-ስርዓት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት እየተካሄደ ይገኛል።

ለከተማው ድምቀት ይሆናል ተብሎ የሚጠበቀው ደረጃውን የጠበቀ B+G+8 ሙሉ አገልግሎት የሚሰጥ ባለ 4 ኮከብ ህንፃ ግንባታ ለመገንባት የመሰረት ድንጋይ የማኖር ስነ ስርአት እየተካሄደ ያለው።

የሎጁ መገንባት በከተማው የንግድና የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ በማጠናከር፣ የከተማውን ኢኮኖሚ ለማነቃቃትና የከተማውን ገጽታ በማስዋብ ለቱሪዝምና ለኢንቨስትመንት ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል።

ሎጁ በውስጡ የምግብ፣ የአልጋ፣የመዋኛ ገንዳ፣ የህፃናት መዝናኛ ማዕከል፣የንግድ አገልግሎቶች፣ የጂምና ሌሎች ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ክፍሎችን የያዘ ነው ።

ዲዛይኑ የጉራጌ ባህላዊ ቤት አሰራርን ቅርፅ የያዘና ለከተማ ልዩ ገፅታ ይሰጠል ተብሎ ይጠበቃል።

በዕለቱ መርሀ ግብር የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር ዶ/ር እንዳሻው ጣሰው ፣ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ የብልጽግና ፓርቲ አደረጃጀት ዘርፍ ሀላፊ አቶ ይግለጡ አብዛ፣በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የመሰረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና እና የትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር መሀመድ ኑርዬ፣በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ሀላፊና የከተማና ኢንዱስትሪ ክላስተር አስተባባሪ አቶ ስንታየሁ ወልደሚካኤል፣ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ፣ የጉራጌ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ናስር ሀሰን፣ የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ሙራድ ከድር ጨምሮ የክልል፣ የዞንና የከተማ የስራ ሀላፊዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር በሚል መሪ ቃል የጉራጌ ዞን ፋይናንስ መምሪያ የብልፅግና ቤተሰብ አባላት የፓርቲውን ማኒፌስቶ የማስተዋወቅ እና "የቡና ጠጡ" ፕሮግራም አካሄዱ።ግንቦት 2/201...
10/05/2026

ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር በሚል መሪ ቃል የጉራጌ ዞን ፋይናንስ መምሪያ የብልፅግና ቤተሰብ አባላት የፓርቲውን ማኒፌስቶ የማስተዋወቅ እና "የቡና ጠጡ" ፕሮግራም አካሄዱ።

ግንቦት 2/2018 | ወልቂጤ

የጉራጌ ዞን የብልፅግና ፓርቲ በሁሉም ማህበራዊ መሠረቶች "በቡና ጠጡ" መርሀ ግብር የምርጫ ቅስቀሳውን አጠናክሮ ቀጥሏል።

የዚሁ መርሀ ግብር አካል የሆነው የዞኑ ፋይናንስ መምሪያ የብልፅግና ቤተሰብ አባላት በዛሬው ዕለት የፓርቲውን ማኒፌስቶና ምልክት በማስተዋወቅ የቃል ኪዳን ማደሻ መርሀ ግብር አከናውነዋል።

በመርሀ ግብሩ ላይ የተገኙት የጉራጌ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ሀላፊ አቶ አብዶ ሀሰን እንደገለጹት፤ ፓርቲው ባለፉት ዓመታት ፈተናዎችን ወደ ዕድል በመቀየር የዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተጨባጭ ውጤቶችን አምጥቷል ብለዋል።

በለውጡ መንግስት ጠንካራ የፋይናንስ ስርአት በመዘርጋት የዞኑ የውስጥ የገቢ አቅም እንዲያድግ ተደርጓል በሚል ገልፀዋል።

የተመደበው በጀት ለታለመለት ዓላማ እንዲውል በማድረግ እና የካፒታል ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ የዘመናት የህዝብ ጥያቄዎች ምላሽ እንዲያገኙ ተሰርቷልም ብለዋል።

ስለሆነም ብልፅግና በተግባር የተረጋገጡ ስኬቶችን አስመዝግቧል በሚል ለአባላቱ አብራርተዋል።

የመምሪያው ምክትል ኃላፊ አቶ ሳሊም ሸምሱ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር ለማሸጋገር የተያዘው ውጥን ከግብ እንዲደርስ ሁላችንም ድምፃችንን ለፓርቲው በመስጠት ቃል ኪዳናችንን ማደስ ይገባናል ብለዋል።

"ብልፅግና ያሰበውን የሚፈጽም፣ ቃልን በተግባር የሚያሳይ ሀገራዊ ፓርቲ ነው" ያሉት አቶ ሳሊም፣ ሁሉም የመንግስት ሰራተኞች ምርጫው ሰላማዊ እንዲሆን የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡ አሳስበዋል።

የመምሪያው የብልፅግና ህብረት እና ቤተሰብ አባላት በበኩላቸው፤ በሀገርም ሆነ በዞን ደረጃ በሁሉም ዘርፎች እየተመዘገቡ ያሉ ስኬቶች ቀጣይነት እንዲኖራቸው "ምርጫችን ብልፅግና ነው!" በማለት ያላቸውን ጽኑ አቋም ገልጸዋል።

የጉራጌ ዞን ፋይናንስ መምሪያ በበጀት ዓመቱ ለካፒታል ፕሮጀክቶች ልዩ ትኩረት በመስጠትና በጀትን ለታለመለት ዓላማ በማዋል ውጤታማ ስራዎች ማከናወኑን አስታወቀ።መምሪያው ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ...
08/05/2026

የጉራጌ ዞን ፋይናንስ መምሪያ በበጀት ዓመቱ ለካፒታል ፕሮጀክቶች ልዩ ትኩረት በመስጠትና በጀትን ለታለመለት ዓላማ በማዋል ውጤታማ ስራዎች ማከናወኑን አስታወቀ።

መምሪያው ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከግማሽ ቢሊየን ብር በላይ ለካፒታል ፕሮጀክቶች ወጪ ማድረጉንም ገልጿል።

ሚያዚያ 30/2018(ወልቂጤ)

መምሪያው የ2018 በጀት ዓመት 3ኛ ሩብ ዓመት አፈጻጸም እና የዜጎች ቻርተር ውይይት በወልቂጤ ከተማ አካሂዷል።

የጉራጌ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ምክትል ኃላፊ አቶ ሳሊም ሸምሱ እንዳሉት መምሪያው በ2018 በጀት ዓመት 3ኛ ሩብ ዓመት ውስጥ በፋይናንስ አስተዳደር፣ በበጀት ክትትል፣ በግዢና በኦዲት ዘርፎች አበረታች ውጤቶችን አስመዝግቧል።

የአገልግሎት አሰጣጥ በማሻሻልና በጀትን ለታለመለት ዓላማ ለማዋል በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተናግረዋል።

መምሪያው ከ7 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት በፍትሃዊነት በመመደብ ለወረዳዎችና ለከተማ አስተዳደሮች ማሰራጨቱን ገልጸዋል።

በ2018 በጀት ዓመት በ9 ወሩ ለካፒታል ወጪ 519 ሚሊየን 482 ሺ 803 ብር ክፍያ መፈጸሙ አብራርተዋል።

እንደ አቶ ሳሊም ገለጻ በ3ኛው ሩብ ዓመት የበጀት አፈጻጸም 74 ነጥብ 6 በመቶ ደርሷል።

በተለይም በደመወዝ፣ በስራ ማስኬጃ እና በካፒታል ፕሮጀክቶች አበረታች ውጤት መመዝገቡን ጠቅሰው፣ ለድህነት ቀናሽ ሴክተሮች 67 በመቶ በላይ በጀት መመደቡ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ እያገዘ መሆኑን ተናግረዋል።

በግዢ ዘርፍም መምሪያው በ9 ወራት ውስጥ ለተለያዩ የጽዳት እቃዎች፣ የጽህፈት መሳሪያዎች፣ ኤሌክትሮኒክስ፣ የሞተር ሳይክሎች ፈርኒቸሮች እና ሌሎች አስፈላጊ ግብዓቶች ከ13 ሚሊዮን 446 ሺህ ብር በላይ ወጪ በማድረግ ግዢ መፈጸሙን አቶ ሳሊም ገልጸዋል።

በ15ቱ ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮችም በድምሩ 359 ሚሊዮን 467 ሺህ ብር በማውጣት የተለያዩ ግዢዎች መከናወናቸውን አስታውቀዋል።

የግዢ ስራአቱን በማዘመን ወቅቱንና ጥራቱን የጠበቀ እንዲሆን የጥራት የሚያረጋግጥ ኮሚቴ ተቋቁሞ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

አቶ ሳሊም ሸምሱ እንዳሉት በኦዲት ዘርፍ የተገኙ ጉድለቶችን ለማስመለስ የተደረገው ጥረት ውጤታማ ሲሆን በሚሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ ወደ መንግስት ካዝና ተመልሷል።

የፋይናንስ ስርዓቱን የበለጠ ግልጽና ተጠያቂ ለማድረግም የክትትልና የድጋፍ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል።

የጉራጌ የማህበረሰብ ቴሌቪዥን ጣበያ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውል ተገብቶ ስራዎች መጀመራቸው አቶ ሳሊም ጠቅሰዋል።

የመምሪያ የልማት እቅድ ባለሙያ አቶ ዘኪዎስ አትፏዬ ሪፓርቱ ባቀረቡቡት ወቅት አዲሱን የመንግስት ሰራተኞች የደመወዝ ጭማሪ ለወረዳና ለከተማ አስተዳደሮች 683 ሚሊዮን 794 ሺህ 8 ብር ከ96 ሳንቲም የተላለፈ ሲሆን፣ ለዞን ማዕከል መንግስት ሰራተኞች የደመወዝ ጭማሪ 29 ሚሊዮን 174 ሺህ 415 ብር መተላለፉን ገልጿል።

በውይይቱ የተገኙት ተሳታፊዎቹ በበኩላቸው በተቋሙ የአገልግሎት አሰጣጥ በማሻሻል፣ለካፒታል ፕሮጀክቶች ትኩረት በመስጠትና የኦዲት ስራዎችን በማከናወን አበረታች ስራዎች ተሰርተዋል።

በተለይ ለድህነት ቀናሽ ተቋሟት ከፍተኛ በጀት በመመደብ እየተሰሩ ያሉ ስራዎች አበረታትተው ወቅቱን የጠበቀ የግዢ ስርአት በማስፈን ጥራት ያላቸው እቃዎች እንዲገዙ ማድረግ ላይ የበለጠ አጠናክሮ ማስቀጠል ያስፈልጋል ብለዋል።

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟላ መረጃዎችን ለማግኘት ከታች የተቀመጡ ሊኮች በመጫን የተቋማችንና ሌሎች የሚዲያ አማራጮችን ይጠቀሙ፡-👇

ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/gurage1Zone
ፌስቡክ ጉራግኛ፦https://www.facebook.com/profile.php?id=61582123942054
Website:- https://gurage.gov.et
Telegram:- https://t.me/comminuca
ቲዊተር፡-https://x.com/GurageT17420?t=zgBzoBE_oQSZbQUbAbPYMw&s=09
በYoutub:-https://www.youtube.com/-u8y4y
በቲክቶክ:-https://vm.tiktok.com/ZMrYn7vV5/
በኢንስታግራም:-https://www.instagram.com/gurage_zone_gov.tcommunication?igsh=MTM3eDV2dms5YTg0Zw==
Whatsapp፦https://chat.whatsapp.com/KYIxtaMxPs77YwugtSq7oF?mode=hqctcla

Address

Wolkite
SNNPR

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gurage Zone Finance Department posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share