Central Ethiopia Water,Irrigation and Mine Bureau

Central Ethiopia  Water,Irrigation and Mine  Bureau Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Central Ethiopia Water,Irrigation and Mine Bureau, Government Organization, Wolkite.

ኢትዮጵያ በጥቁር ህዝቦች ታሪክ ነጻነቷን እና ሉአላዊነቷን አረጋግጣ የቆየች ሀገር ናት:- አፈ ጉባኤ ፋጤ ስርሞሎ (ሆሳዕና፣ጳጉሜ 3/2018)በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳ...
08/09/2026

ኢትዮጵያ በጥቁር ህዝቦች ታሪክ ነጻነቷን እና ሉአላዊነቷን አረጋግጣ የቆየች ሀገር ናት:- አፈ ጉባኤ ፋጤ ስርሞሎ

(ሆሳዕና፣ጳጉሜ 3/2018)በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በተገኙበት የጽናት ቀን በወልቂጤ ከተማ በልዩ ልዩ ዝግጅቶች በድምቀት እየተከበረ ይገኛል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት ኢትዮጵያ ከብዙ ሀገራት የቀደሙ የሀገረ መንግስት ግንባታ ታሪክ እንዳላት ተናግረዋል።

በጥቁር ህዝቦች ታሪክ ነጻነቷን እና ሉአላዊነቷን አረጋግጣ የቆየች ሀገር ስለመሆኗም ዋና አፈ ጉባኤዋ አብራርተዋል።

በተለያዩ ጊዜያት የተሞከሩ የውጭ ወረራዎችን በመመከት ነጻነቷን ያወጀች ሀገር መሆኗን ጠቁመዋል።

ምንም እንኳን ሀገራዊ ሉአላዊነታችንን አስጠብቀን ለረጅም ዘመን የቆየን ቢሆንም የኢኮኖሚ ነጻነታችንን ባለመስጠበቃችን ከድህነት ጋር አብረን ኖረናል ብለዋል።

የለውጡ መንግስት በርካታ ውስብስብ ፈተናዎችን እየተሻገረ አኩሪ ድሎችን እያስመዘገበ መሆኑን አፈ ጉባኤዋ አስረድተዋል።

የለውጡ መንግስት የአፍሪካውያን የጽናት ተምሳሌት መሆን ስለመቻሉ የገለጹት ዋና አፈ ጉባኤዋ ሀገራችን የተሟላ የኢኮኖሚ ሉአላዊነቷን እንድታረጋግጥ እየተጋ ስለመሆኑም ጠቅሰዋል።

ባለፉት ስምንት የለውጥ አመታት በሀገሪቱ ፖለቲካዊ፣ኢኮኖሚያዊ፣ማህበራዊ እና ዲፕሎማሲያዊ ድሎች እየተመዘገቡ መሆኑን ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ አብራርተዋል።

የለውጡ መንግስት አህጉራዊ እና አለም አቀፋዊ ቀጠናዊ ተለዋዋጭ ሁኔታዎችን በጽናት እየተሻገረ የዜጎችን ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ ከተስፋ ብርሀን ወደ ሚጨበጥ ብርሀን መሸጋገር ተችሏል ብለዋል።

ኢትዮጵያ በሁሉም መስኮች እምርታዊ ለውጥ በማምጣት በማንሰራራት ላይ እንደምትገኝ ጠቁመዋል።

ልዩነቶችን በምክክር የመፍታት አዳዲስ ባህል እያዳበረች የመጣች ሀገር ስለመሆኗም ዋና አፈ ጉባኤዋ ጠቁመዋል።
የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ፣ የመሰረተ ልማት ማዘመን፣ የኮሪደር ልማት፣ የሌማት ትሩፋት፣ የአረንጓዴ አሸራ፣ የብሾፍቱ አለም አቀፍ አየር ማረፊያ እና የኒውክሌር ኃይል ማመንጫ ጅማሬዎች ጨምሮ በርካታ ሜጋ ፕሮጀክቶች የኢትዮጵያ ማንሰራራት ማሳያዎች መሆናቸውን ጠቅሰዋል።

እለቱን በማስመልከት ወታደራዊ ትርኢት እና መሰል ዝግጅት እየቀረበ ነው።

የክልሉ መንግስት ኮምኒኬሽን

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት ፣"የጽናት ቀንኢትዮጵያን ስናስብ፣ ሌት ተቀን በጽናት በመቆም ሀገርን ከጠላት ለመጠበቅ ወጥተው ለሚያድሩት ብርቱ የፀጥታ ኃይሎቻችን ቅድሚያ...
08/09/2026

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት ፣

"የጽናት ቀን

ኢትዮጵያን ስናስብ፣ ሌት ተቀን በጽናት በመቆም ሀገርን ከጠላት ለመጠበቅ ወጥተው ለሚያድሩት ብርቱ የፀጥታ ኃይሎቻችን ቅድሚያ ሳንሰጥ ስለ ሁለንተናዊ ከፍታ ማሰብ ፈጽሞ አይቻልም፡፡ ለዚህም ነው በዚህ የጽናት ቀን፣ ለሀገረ-መንግሥታችን ዘላቂነትና ሉዓላዊነት ሲሉ ውድ ሕይወታቸውን የከፈሉትን የጀግኖቻችንን ታሪካዊ መስዋዕትነት በከፍተኛ ሀገራዊ ክብር የምንዘክረው፡፡
ዛሬ ላይ ሀገራችን በራሷ ዕውቀትና በልጆቿ አቅም የላቀ የቴክኖሎጂ ብቃት ያላቸውን ሰው አልባ አውሮፕላኖችን፣ ዘመናዊ የታጠቁ ወታደራዊ ተሽከርካሪዎችን፣ ከባድ መሣሪያዎችንና መድፎችን፣ እንዲሁም ተተኳሽ ጥይቶችን በራሷ ወታደራዊ ኢንዱስትሪዎች ማምረት ችላለች፡፡ ይህ በራስ የመቆም አቅም፣ የሕዝባችን ሰላምና የሁለንተናዊ ኢኮኖሚ እድገታችን ጽኑ መሠረት በመሆኑ፣ ሀገራዊ ጽናታችንን በተጨባጭ ልማትና በጠንካራ የመጠበቅና የመከላከል አቅም እያረጋገጥን የኢትዮጵያን ዘላቂ ብልጽግና እናጸናለን!"

ጳጉሜ 3:- የጽናት ቀንጽናት በፈተና ውስጥ ሳይበገሩ፣ ተስፋ ሳይቆርጡ እና ከዓላማ ሳይወጡ በብርታት የመቀጠል ታላቅ የውስጥ ሀይልና ባህሪ ነው። ጽናት የህዝቦችን አንድነት የሚያጎለብትና የሚ...
08/09/2026

ጳጉሜ 3:- የጽናት ቀን

ጽናት በፈተና ውስጥ ሳይበገሩ፣ ተስፋ ሳይቆርጡ እና ከዓላማ ሳይወጡ በብርታት የመቀጠል ታላቅ የውስጥ ሀይልና ባህሪ ነው።
ጽናት የህዝቦችን አንድነት የሚያጎለብትና የሚያጠናክር በመሆኑ ሀገርን ከማንኛውም የውጭና የውስጥ ተግዳሮት በመጠበቅ ለሉዓላዊነት አስተማማኝ ዋስትና ይሆናል።

ኢትዮጵያም ለዘመናት የገጠሟትን ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ዲፕሎማሲያዊ ፈተናዎችን በልጆቿ የላብ ዋጋና የደም መስዋዕትነት ተቋቁማ፣ ሉዓላዊነቷ ተከብሮ ኖራለች፡፡

ከኢትዮጵያውያን ጽናትና አኩሪ ድሎች አንዱና ዋነኛው ለአፍሪካውያንና ለመላው ጥቁር ህዝቦች የነጻነት ማንቂያ የሆነው እንዲሁም ለሰው ልጆች ሁሉ የይቻላል መንፈስን ያላበሰው የአድዋ ድል ነው፡፡

ሌላው ዳግማዊ አድዋ ተብሎ ሊወሰድ የሚችለው የአፍሪካ ግዙፉ ፕሮጀክት፣ የቀጠናው ብርሃን፣ ለኢትዮጵያ ማንሰራራት የኃይል ምንጭ የሆነው ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ነው፡፡

ግድቡን፣ ኢትዮጵያውያን በላባቸውና በዕውቀታቸው ከመገንባት ባሻገር ግንባታው እንዲደናቀፍ የሚደረግ ጫናን ለመቀልበስ የተያዘው ጽኑ ሀገራዊ አቅጣጫ በታሪክ ሲታወስ ይኖራል፡፡ ለዚህም መንግስት ‹‹ለአፍሪካ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሔ›› በሚል እንዲሁም ኢትዮጵያውያንና ትውልደ-ኢትዮጵያውያን ‹‹ግድቡ የኔ ነው›› በሚል ጽኑ አቋም በአንድ ላይ ቆሙ፤ አሳኩትም፡፡

በተመሳሳይ ሁኔታ ኢትዮጵያ የባህር በር የማግኘት ተፈጥሮአዊና ህጋዊ መብቷን ለማረጋገጥ ህዝብና መንግሥት በጽናት ቆመዋል፤ ይህም ጊዜውን ጠብቆ ጉባ ላይ በተበሰሩ ሀገራዊ ሜጋ ፕሮጀክቶች ታጅቦ ለኢትዮጵያ ህዝብ የሚበረከት የጽናት ውጤት ይሆናል፡፡

የጽናት ቀን ሲነሳ የደኅንነት እና ጸጥታ ተቋማት ሚናም አብሮ ይነሳል፡፡ የኢትዮጵያ የደኅንነት እና ጸጥታ ተቋማት ማንኛቸውንም ፈተናዎች እና አደጋዎች በጀግንነት በመመከት የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት፣ የሕዝብ አንድነት፣ የአየር ክልል እና የየብስ ግዛት ማስከበር ከመቻላቸውም ባሻገር ዘመኑን የሚመጥን የቴክኖሎጂ፣ የሎጀስቲክስና የመፈጸም ቁመናና ብቃት ደርሰዋል፡፡

የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት፣ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ፣ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት፣ የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አስተዳደር እና የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተሊጀንስ ኢንስቲትዩት በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ታጥቀው የሀገርን ዳር ድንበር እና የሕግ የበላይነት እያስከበሩበት ያለው ቁመና ኢትዮጵያ በምትገኝበት ጂኦፖለቲካዊ ሁኔታ ውስጥ አስተማማኝ የሉዓላዊነት ዋስትና ሆኗል፡፡

በደምና በአጥንት መስዋዕትነት የተከበረው ሉዓላዊነት በኢኮኖሚ ጥገኝነት አደጋ እንዳይገጥመው ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ጉዞን በላብ መስዋዕትነት በማሳካት የኢትዮጵያን ማንሰራራት በማፋጠን ሀገሪቱ የሚገባት ከፍታ ላይ እንድትቀመጥ ህዝብና መንግስት በጽናት ቆመዋል፡፡

በመሆኑም፣ ኢትዮጵያ በጽናት ያስመዘገበቻቸውን አኩሪ የሉዓላዊነት፣ የልማትና የደኅንነት ድሎች ወደላቀ ምዕራፍ ለማሸጋገር፣ የጀመረቻቸውን ታላላቅ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል። ይኸውም ከዕዳና ከተረጂነት ነፃ የሆነ ጠንካራ የኢኮኖሚ መዋቅር ለመገንባት በሚደረገው ጥረት የሕዝብና የመንግሥትን ቅንጅት ማስፋት፣ የደኅንነትና የጸጥታ ተቋማትን ዘመናዊ የቴክኖሎጂ አቅም አቀናጅቶ ማስቀጠል፣ እንዲሁም የባህር በር የማግኘት ሕጋዊና ተፈጥሮአዊ መብትን በጽናትና በዲፕሎማሲያዊ መንገድ እውን ማድረግን ይጠይቃል።

በመጨረሻም፣ ይሄው የ‹‹ይቻላል›› እና የጽናት መንፈስ በትውልድ መካከል ሳይቋረጥ እንዲሸጋገር በማድረግ የሀገርን ሉዓላዊነትና ሁለንተናዊ ከፍታ በአስተማማኝ ሁኔታ ማረጋገጥ ያስፈልጋል።

ጽኑ መሰረት ብርቱ ሀገር!

አዲስ አመትን ምክንያት በማድረግ የክልሉ ማዕድንና ኢነርጂ ኤጀንሲ ለአቅመ ደካማ ወገኖች የአይነት ድጋፍ አደረገ። ጳጉሜ 02/2018 (ወልቂጤ)የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ማዕድንና ኢነርጂ ኤጀ...
07/09/2026

አዲስ አመትን ምክንያት በማድረግ የክልሉ ማዕድንና ኢነርጂ ኤጀንሲ ለአቅመ ደካማ ወገኖች የአይነት ድጋፍ አደረገ።

ጳጉሜ 02/2018 (ወልቂጤ)
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ማዕድንና ኢነርጂ ኤጀንሲ መጪውን 2019 አዲስ አመትን ምክንያት በማድረግ ከቀቤና ልዩ ወረዳ፣ ከወልቂጤ ከተማና ከአበሽጌ ወረዳ ለተወጣጡ 18 አቅመ-ደካማ ወገኖች የአይነት/ የዳቦ ዱቄት ፣ የምግብ ዘይትና ፓስታ ድጋፍ አደርጓል።

በእለቱ ተገኝተው ድጋፉን ያበረከቱት የክልሉ ማዕድንና ኢነርጂ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ መኮንን መኔዶ እንደተናገሩት ኤጀንሲው ከተጣለበት መንግስታዊ ተልዕኮ ጎን ለጎን የኤጀንሲውንና የሰራተኛውን አቅም በመጠቀም ሰው ተኮር የሆኑ ስራዎች ላይ መደጋገፍን ማዕከል በማድረግ ባለፉት ሶስት ዓመታት ሲንቀሳቀሱ መቆየታቸውን ገልፀዋል።

ይህንኑ ታሳቢ በማድረግ በሶስቱም የአስተዳደር እርከኖች የሚገኙ አቅመ ደካማ ወገኖችን ማዕከል በማድረግ በየመዋቅሮቹ ተለይተው የ2019 አዲሱን ዓመት በጋራና በደስታ እንዲያከብሩ ታሳቢ በማድረግ የተዘጋጀ ድጋፍ መሆኑን ገልፀዋል ።

እንደ ሀገር የብዘሃ ሃይማኖት ፣ ባህልና ብሄረሰብ ባለቤት በመሆናችን አብሮነት ሁል ጊዜ መሰረታዊ እንደሆነና በመተሳሰብና በመቀናጀት ርስ በርስ መደጋገፍን ማጠናከር ይገባል በሚል አቶ መኮንን ተናግረዋል ።

በእለቱ ድጋፍ የተደረገላቸው ወገኖች በኤጀንሲው የተዘጋጀው ድጋፍ በወሳኝ ሰአት እንደደረሰላቸው ገልፀው ለተደረገላቸው ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

በእለቱ የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ መኮንን መኔዶ፣ የኤጀንሲው ማናጅመንት አባላትና ሰራተኞች እንዲሁም ድጋፍ የተደረገላቸው ወገኖች ተገኝተዋል ።

የገጠር መንገድ ትስስርና ተደራሽነትን ለማስፋት  በትኩረት እየሰራ መሆኑ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ገለጸ።(ሆሳዕና፣ ጳጉሜ 2/2018) በቢሮው የገጠር ትስስ...
07/09/2026

የገጠር መንገድ ትስስርና ተደራሽነትን ለማስፋት በትኩረት እየሰራ መሆኑ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ገለጸ።

(ሆሳዕና፣ ጳጉሜ 2/2018) በቢሮው የገጠር ትስስርና ተደራሽነት ለምግብ ዋስትና ፕሮግራም የስትሪንግ ኮሚቴ የ2018 ዓ/ም አፈጻጸም እና የ2019 ዕቅድ ዝግጅት ግምገማ መድረክ በሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ነው።

በመድረኩ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የመሰረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር መሀመድ ኑሪዬ እንደተናገሩት የገጠር መንገድ ትስስርና ተደራሽነትን በማስፋት የገጠር ትራንስፎርሜሽንን ለማቀለጠፍ ቢሮው በትኩረት እየሠራ ነው።

የገጠር ትስስርና ተደራሽነት ለምግብ ዋስትና ፕሮግራም በክልሉ ከ2017 በጀት ዓመት መገባደጃ ጀምሮ በስምንት ወረዳዎች እየተተገበረ መሆኑን ዶ/ር መሀመድ ጠቁመዋል።

በዓለም ባንክ ድጋፍና በክልሉ መንግሥት በጀት የሚፈጸመው ፕሮግራሙ የገጠር ትስስርና ተደራሽነትን በማጠናከር ለምግብ ዋስትና መረጋገጥና የገጠር ትራንስፎርሜሽን ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ቢሮ ኃላፊው ጠቁመዋል።

በመድረኩ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ልማት ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡስማን ሱሩርን ጨምሮ የስትሪንግ ኮሚቴ አባላት ተገኝተዋል።

የክልሉ መንግስት ኮምኒኬሽን

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ርዕሰ መስተዳድር  እንዳሻዉ ጣሰዉ  ( ዶ/ር ) ጳጉሜን _2 የማንሰራራት ቀንን በማስመልከት ያስተላለፉት መልዕክት፦የማንሰራራት ቀን !የማንሰራራት ቀን ፣...
07/09/2026

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻዉ ጣሰዉ ( ዶ/ር ) ጳጉሜን _2 የማንሰራራት ቀንን በማስመልከት ያስተላለፉት መልዕክት፦

የማንሰራራት ቀን !
የማንሰራራት ቀን ፣ ዘመኑ የኢትዮጵያ የማንሰራራት ዘመን መሆኑን የሚያበስሩ ታላላቅ ስኬቶች መመዝገባቸዉን ከመዘከር ባሻገር፣ የኢትዮጵያ የማንሰራራት ዘመን ሁሉአቀፍ በሆነ መልኩ ተጠናክሮ እንዲቀጥል መላዉ ዜጎች የየበኩላቸዉን በቁጭት እና በላቀ ዝግጁነት ለመወጣት የሚነሳሱበት ነዉ።
ኢትዮጵያ የጀመረችው የማንሰራራት ዘመን ጉዞ ሁለንተናዊ እና ፈጣን ይሆን ዘንድ መላዉ የክልላችን ሕዝቦችም የበኩላችሁን በላቀ ደረጃ ታበረክቱ ዘንድ በዚህ አጋጣሚ በአክብሮት እጠይቃለሁ ።

የቆዩ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶችን ለማጠናቀቅ ክልሉ በትኩረት እየሰራ መሆኑ ተገለፀ። ጳጉሜ 1/2018 ዓ.ም (ወልቂጤ)በሀድያ ዞን ሶሮ ወረዳ ሀንገዳ ቀበሌ በክልሉ መንግሥት ካፒታል በጀት ከ...
06/09/2026

የቆዩ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶችን ለማጠናቀቅ ክልሉ በትኩረት እየሰራ መሆኑ ተገለፀ።

ጳጉሜ 1/2018 ዓ.ም (ወልቂጤ)
በሀድያ ዞን ሶሮ ወረዳ ሀንገዳ ቀበሌ በክልሉ መንግሥት ካፒታል በጀት ከ30 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባው የሀንገዳ የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ተመርቆ ለህብረተሰቡ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።

ፕሮጀክቱ 12 የውሃ ቦኖዎችን፣ 193 ሜትር ጥልቀት ያለው ጉድጓድ፣ 100 ኪዩቢክ ሜትር የውሃ ማጠራቀሚያ ጋን፣ 3.1 ኪሎ ሜትር የግፊት መስመር እና 8.4 ኪሎ ሜትር የማሰራጫ መስመር ያካተተ ሲሆን፣ በአጠቃላይ ከ10 ሺህ በላይ ነዋሪዎችን ያገለግላል።

በፕሮጀክቱ ምረቃ ሥነ-ሥርዓት ላይ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የመሠረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር መሀመድ ኑርዬ፣ የቆዩ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶችን ለማጠናቀቅ ክልሉ በትኩረት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል ።

ክልሉ ከአዲስ አደረጃጀት በኋላ ለሀንገዳ የውሃ ፕሮጀክት ትኩረት ሰጥቶ ሲሰራ መቆየቱን የገለጹት ዶክተር መሀመድ፣ በቀጣይም የክልሉን ህዝብ የልማት ጥያቄ ለመመለስ ተጨማሪ የመሠረተ ልማት ሥራዎች እንደሚከናወኑ ተናግረዋል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የውሃ፣ መስኖና ማዕድን ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ዳዊት ኃይሉ በበኩላቸው፣ ክልሉ ከተመሰረተ ወዲህ በውሃ ዘርፍ በርካታ ውጤቶችን ማስመዝገቡን ገልጸው፣ የሀንገዳ የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክትም የዚህ ውጤት አንዱ ማሳያ መሆኑን ጠቁመዋል።

አቶ ዳዊት ፕሮጀክቱ ተጠናቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ ላደረጉ አካላት በራሳቸውና በተቋማቸው ስም ምስጋና አቅርበዋል።

የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት የህብረተሰቡን የጤናና የኑሮ ሁኔታ ለማሻሻል ወሳኝ መሆኑን የጠቆሙት ኃላፊው፣ ህብረተሰቡ የተገነባውን የውሃ መሠረተ ልማት በአግባቡ በመጠቀምና በመጠበቅ ዘላቂነቱን እንዲያረጋግጥ አሳስበዋል።

የሀድያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማቴዎስ አኒዮ፣ በዞኑ የሚገኙ የመሠረተ ልማት ጥያቄዎች አቅም በፈቀደ መጠን ምላሽ እንዲያገኙ ከክልሉ ጋር በቅንጅት እንደሚሰሩ ገልጸዋል።

የፕሮጀክቱ ተጠቃሚ ነዋሪዎች ቀደም ሲል ንጹህ ውሃ ለማግኘት ረጅም ርቀት በመጓዝ ብዙ ጊዜና ጉልበት ያጠፉ እንደነበር ገልጸው፣ አሁን በአካባቢያቸው ውሃ ማግኘታቸው ትልቅ እፎይታ መሆኑን ተናግረዋል።

ነዋሪዎቹ ያገኙትን ጊዜ በቤተሰብ፣ በትምህርትና በሌሎች ምርታማ ሥራዎች ላይ ለማዋል እንደሚችሉ ጠቁመው፣ የውሃ መሠረተ ልማቱን በአግባቡ በመጠቀምና በመጠበቅ ዘላቂነቱን ለማረጋገጥ ተሳትፎአቸውን እንደሚያጠናክሩ ገልጸዋል።

የክልሉ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርና ገጠር ልማት ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ በክብርት ወ/ሮ ልክነሽ ስርገማ እና አቶ መዘረዲን ሁሰን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የርዕሰ መስተዳድሩ የመሠረተ ልማት ዘርፍ አማካሪ የቢሮው ምክትል የስራ ሃላፍፊዎች፣ የቢሮው ማናጅመንት አባላት ፣ የዞን፣ የወረዳ የስራ ኃላፊዎች፣ የአካባቢው ነዋሪዎች እና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት ተገኝተዋል።

የክልሉ መንግስት ኮምኒኬሽን

በሶሮ ወረዳ ከ30 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የሃንገዳ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ተደረገ።ጳጉሜ 01/2018 (ወልቂጤ)በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሃዲያ ዞን ሶሮ ...
06/09/2026

በሶሮ ወረዳ ከ30 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የሃንገዳ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ተደረገ።

ጳጉሜ 01/2018 (ወልቂጤ)
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሃዲያ ዞን ሶሮ ወረዳ በክልሉ መንግሥት ካፒታል በጀት ከ30 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የሃንገዳ የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የመሰረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና በክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር መሃመድ ኑሪዬና የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ተደርጓል።

በምረቃ መርሃ-ግብሩ የግብርናና ገጠር ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወ/ሮ ልክነሽ ስርገማ ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር የመሰረተ ልማት አማካሪ አቶ መዘረዲን ሁሴን ፣የክልሉ ውሃ፣ መስኖና ማዕድን ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ዳዊት ኃይሉ ፣የሃዲያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማቲዮስ አኒዮ፣ የቢሮው ምክትል ስራ ሃላፊዎች አየለ ኬርጋ ኢ/ር እና አቶ ሙላቱ ጡሞሮ፣ የክልል፣ የዞንና የወረዳ ስራ ሀላፊዎች እንዲሁም የሚመለከታቸው አካላት ተገኝተዋል ።

ዝርዝር መረጃውን ተከታትለን እናደርሳለን ።

06/09/2026
በሁሉም መስክ ያስመዘገብናቸው እምርታዎች ለሁለንተናዊ የብልጽግና ጉዞ መሰረት ናቸው ዛሬ ጳጉሜ 1/2018 የእምርታ ቀን ነው የእምርታ ቀን ያለፍንባቸውን ፈታኝ መንገዶች ወደኋላ መለስ ብለን ...
06/09/2026

በሁሉም መስክ ያስመዘገብናቸው እምርታዎች ለሁለንተናዊ የብልጽግና ጉዞ መሰረት ናቸው

ዛሬ ጳጉሜ 1/2018 የእምርታ ቀን ነው የእምርታ ቀን ያለፍንባቸውን ፈታኝ መንገዶች ወደኋላ መለስ ብለን የምናይበት፣ የተመዘገቡ ታላላቅ ስኬቶችን የምናከብርበት እና ወደ ላቀ ምዕራፍ ለመሻገር አዲስ ራዕይና መንፈስ የምንሰንቅበት ልዩ አጋጣሚ ነው።

ይህ ቀን የሁላችንንም ጥረት፣ ፅናት እና የስራ ፍቅር የምንመዝንበት ትልቅ ምዕራፍ ነው።
ባለፉት ጊዜያት ያጋጠሙንን ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ ተደራራቢ ፈተናዎች በፅናት አልፈን፣ የነደፍናቸውን ግቦች ለማሳካት በጋራ የሰራነው ስራ ለዛሬው የእምርታ ደረጃ አብቅቶናል።

ኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት ዓመታት ያጋጠሟትን የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት፣ የኮቪድ-19 ወረርሽኝ፣ እና የዓለም አቀፍ የጂኦፖለቲካ ውጥረቶችን ተቋቁማ የማክሮ ኢኮኖሚያዊ እድገቷን ቀጣይነት አስጠብቃለች።

ለዚህ ጽናት እና ኢኮኖሚያዊ እድገት ዋና ዋና አስተዋጽኦ ያደረጉ ምክንያቶች እና ማሳያዎች፡-የግብርና ክፍለ-ኢኮኖሚ ጥንካሬ፡ የሌማት ትሩፋት፣ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት እና የተሻሻሉ የግብርና አሰራሮች የሀገር ውስጥ የምግብ ዋስትናን ከመደገፋቸውም በላይ የውጭ ምንዛሬ ገቢን በማሳደግ የኢኮኖሚው ዋና ደጋፊ ሆነዋል።

የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ (Homegrown Economic Reform)፡ መንግሥት የፊስካል እና የፖሊሲ ማሻሻያዎችን በማድረግ፣ ገቢ የመሰብሰብ አቅምን በማሳደግ እና ሜጋ ፕሮጀክቶችን በሀገር ውስጥ አቅም በማጠናቀቅ የኢኮኖሚውን መረጋጋት ደግፏል።

የተገኘው ስኬት የመጨረሻው ግባችን አይደለም፤ ይልቁንም ለበለጠ እምርታ እና ተፅዕኖ ፈጣሪነት መነሻችን ነው። ወደፊት በሚኖረን ጉዞ የላቀ ጥራት፣ ፈጣን አገልግሎት እና ዘላቂ እድገት ላይ አተኩረን እንሰራለን።

​ይህ የእምርታ ቀን የሁላችንንም የውስጥ አቅም የምናወጣበት፣ ትልልቅ ህልሞችን የምናልምበት እና በጥረት የምናሳካበት አዲስ የትጋት መንገድ ነው። በጋራ በመሆን የማናልፈው ፈተና፣ የማናስመዘግበው እምርታ አይኖርም!

ያለማንም የውጭ እርዳታ፣ በራሳችን ሀብት፣ ድካምና እውቀት ግድቡን አጠናቅቀን ለምስራቅ አፍሪካ ብርሃን ፈንጥቀናል፤ ኢንዱስትሪዎቻችንን በታዳሽ ኃይል ለማንቀሳቀስ አቅም ፈጥረናል።

በዚህ የማንሰራራት መንፈስ ነው የዘንድሮዉ የጳጉሜ ቀናት የምናከብረው። በመሆኑም ጳጉሜ 1 "የእምርታ ቀን" አድርገን ስናከብር፣ አገራችን ገቢ በመሰብሰብ፣ የውጭ ምንዛሪ በማሳደግ እና ሜጋ ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ ያሳየችውን ተጨባጭ ምርታማነት እያሰብን ነው።

​ በኢትዮጵያ የነበሩ የማክሮ ኢኮኖሚ መዛባቶችን ለማስተካከል፣ የሰፊው ዘርፍ ማነቆዎችን ለመቅረፍ እና የግል ዘርፉን በኢኮኖሚው ውስጥ ያለውን ሚና ለማሳደግ የተቀረፀ ሀገራዊ የኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራም ነው በአብነት የሚጠቀስ ነው።

የዋጋ ንረትን መቀነስ፣ የውጭ ምንዛሬ እጥረትን ማቃለል (የውጭ ምንዛሬ ተመን በገበያ እንዲወሰን ማድረግን ጨምሮ) እና የሀገር ውስጥ ገቢን ማሳደግ ላይ ትኩረት ተደርጓል።

በሌላ በኩል ምርታማነትን ለማሳደግ በዋና ዋና የኢኮኖሚ ምንጮች ማለትም በግብርና፣ በማኑፋክቸሪንግ፣ በማዕድን፣ በቱሪዝም እና በዲጂታል ኢኮኖሚ ላይ ትኩረት ማድረግ ተጠቃሽ ናቸው።

ኢትዮጵያ በጊዜያት እና በታሪክ ውጣ ውረድ ውስጥ ስታልፍ፣ ፈተናዎችን በብስለት እየተሻገረች በሚመጥናት የከፍታ ልክ የሚያስቀምጣትን የማንሰራራት ጉዞ ጀምራለች።

አሁን ላይ በታሪካችን አይተን የማናውቃቸውን አዳዲስ ሀሳቦች ወደ ተግባር በመቀየርና ተጨባጭ ውጤቶችን በማስመዝገብ፣ አገርን አጽንተን ለትውልድ እንደምናስረክብ በተግባር እያሳየን እንገኛለን።

ይህ የሽግግር ወቅት በተለይም የጳጉሜን ወር ስንቀበል፣ ያለፈውን የምንገመግምበት፣ ክፍተታችንን የምናርምበት እና ለቀጣዩ የብልጽግና ጉዟችን ተስፋ የምንሰንቅበት ልዩ ታሪካዊ ቀን ነው።

​የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከተመሠረተ ሦስት ዓመታትን በማስቆጠር ታሪካዊውን "የእምርታ ቀን" ሲያከብር፣ በኅብረ ብሔራዊ አንድነት፣ በኢኮኖሚ ዕድገትና በመልካም አስተዳደር የተመዘገቡ ስኬቶችን እየዘከረ ነው።

ክልሉ ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ የሕዝብ ተሳትፎ እና ተጠቃሚነትን መሰረት በማድረግ ሰላምን በማፅናትና የኢኮኖሚ መሠረቶችን በማስፋት አበክሮ ሲሠራ ቆይቷል።

​ክልሉ የተለያዩ ብሔረሰቦች መገኛ ከመሆን ባለፈ ህዝቦች በሰላምና በፍቅር አብረው የሚኖሩበት የታታሪ ህዝቦች ምድር ነው።

ባለፉት ሦስት ዓመታት የወንድማማችነትና የእህትማማችነት እሴቶችን በማጠናከር፣ የጋራ ማንነትና የክልላዊ አንድነት ስሜት እንዲጎለብት ተደርጓል።

የሕዝቦችን እኩል ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውሳኔዎችን በማሳለፍ፣ ማኅበራዊ ፍትሕን የማስፈን ሥራ መከናወኑ ከቱሩፋቶቻችን ውስጥ ተጠቃሽ ናቸው።

በሌላ በኩል ክልሉ ለሰብል ልማት፣ለቡናና ቅመማ ቅመም፣ለቅባት እህሎች ለሌማት ትሩፋት፣ለተለያዩ አትክልትና ፍራፍሬ ምርቶች እና ለሌሎችም አያሌ የግብርና ልማት ስራዎች ተስማሚ የሆነ ለም መሬት እና ምቹ የአየር ንብረት ተችሮታል።

ይህን ተከትሎ ከዚህ ቀደም ያልተለመዱ የምርት ወቅቶችን በመጨመር በሁሉም መስክ ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ላይ በትኩረት በመሰራቱ አመርቂ ውጤት ማስመዝገብ ተችሏል።

በክልሉ ምርታማነትን በእጥፍ መጨመር የሚያስችል ስርዓት በመዘርጋቱ በኩታ ገጠም እርሻ በበቆሎ እና በሌሎችም ሰብሎች ሜጋ ክላስተር መፍጠር ተችሏል።

በሌላበኩል ተፈጥሯዊና ባህላዊ ሀብቶችን በመጠቀም የቱሪዝም መስክን ማጎልበት ተችሏል። እንዲሁም ለአግሮ-ፕሮሰሲንግና ለተለያዩ ኢንቨስትመንቶች ምቹ ሁኔታዎች በመፈጠራቸው የስራ ዕድል ተፈጥሯል።

ሰላምና ደህንነት የልማት ሁሉ መሠረት በመሆናቸው፣ በክልሉ አስተማማኝ ሰላም እንዲሰፍን በማድረግ የዜጎች የመንቀሳቀስና የመሥራት መብት ተከብሯል።

በሁሉም መስክ ያስመዘገብናቸው እምርታዎች ለሁለንተናዊ የብልጽግና ጉዞ መሰረት ናቸው።

Address

Wolkite

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Central Ethiopia Water,Irrigation and Mine Bureau posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share