CERG Office of Auditor General የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ዋና ኦዲተር መ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Wolkite
  • CERG Office of Auditor General የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ዋና ኦዲተር መ/ቤት

CERG Office of Auditor General የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ዋና ኦዲተር መ/ቤት ኦዲት ተጠያቂነትን በየደረጃ በማረጋገጥ የተቋማቱን አፈፃፀም፡አገልግሎት አሰጣጥ፡የሀብትና ንብረት አጠቃቀም በመፈተሸ ዜጎች በመንግስትና በተቋማቱ ላይ ያላቸዉን እምነት ያጠናክራል፡፡

የማ/ኢ/ክ/መ/ዋና ኦዲተር መ/ቤት አመራርና ሰራኞች በ2018 በጀት አመት ዕቅድ ክንዉንና በ2019 ዓ.ም ጠቋሚ ዕቅድ ሪፖርት ዙሪያ ዉይይት አደረጉ፡፡ማኢዋኦ ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም.  : ...
04/09/2026

የማ/ኢ/ክ/መ/ዋና ኦዲተር መ/ቤት አመራርና ሰራኞች በ2018 በጀት አመት ዕቅድ ክንዉንና በ2019 ዓ.ም ጠቋሚ ዕቅድ ሪፖርት ዙሪያ ዉይይት አደረጉ፡፡
ማኢዋኦ ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም. : የክልሉ ዋና ኦዲተር መ/ቤት የ2018 ዕቅድ አፈፃፀምና የ2019 ጠቋሚ ዕቅድ አስመልክቶ ዉይይት ያደረገ ሲሆን መደረኩን የመ/ቤቱ ም/ዋና ኦዲተር አቶ መሐመድ አብደላ መርተዋል፡፡
የዋና ኦዲተር መ/ቤት የ2018 በጀት አመት አፈፃፀምና የቀጣይ አመት ጠቋሚ ዕቅድ በል/ዕ/በዘ/ክ/ዳይሬክቶሬት ዲይሬክተር ተወካይ አቶ ገነቱ ሲሻዉ የየስራ ክፍሎችን ክንዉንና በመ/ቤቱ እንደተቋም የተመዘገቡ ዉጤቶችን እንዲሁም የ2019 ዓ.ም. ዕቅድና ግቦችን ያመላከት ሪፖርት በዝርዝር አቅርበዋል፡፡በዚiህም የዋና ኦዲተር መ/ቤት የ2018 በጀት አመት አጠቃለይ አፈፀፀም 94.15 % መሆኑንም ተገልጿል፡፡
በቀረበዉ ሪፖርት መነሻነት ተሳታፊ አመራርና ሰራተኞች ጥያቄና አስተያየት አቅርበዉ በም/ዋና ኦዲተር መሐመድ አብደላ ምላሽና ማብራሪያ እንዲሁም በቀጣይ አመት ከዚህ የተሸለ ዉጤት ለማስመዝገብ ተግቶ መስራት እንደሚገባ የስራ አቅጣጫ ሰጥተዉ የዉይይት መድረኩ ተጠናቋል፡፡
ዘገባዉ የመ/ቤቱ ኮሙንኬሽንና ሚዲያ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ነዉ፡፡

“Communication is the lifeline of any audit process. It bridges the gap between auditors and stakeholders, ensuring tran...
02/09/2026

“Communication is the lifeline of any audit process. It bridges the gap between auditors and stakeholders, ensuring transparency and trust."

የኦዲት ስነ-ተግባቦት መርሆዎችና ስልቶችውጤታማ የኦዲት ግንኙነት  ግልጽነት፣ ተጨባጭነት እና ወቅታዊነት ባሉ ዋና ዋና መርሆዎች ላይ የተመሰረተ ሲሆን ግልጽነት፣የባለድርሻ አካላት ተሳትፎን ማ...
27/08/2026

የኦዲት ስነ-ተግባቦት መርሆዎችና ስልቶች
ውጤታማ የኦዲት ግንኙነት ግልጽነት፣ ተጨባጭነት እና ወቅታዊነት ባሉ ዋና ዋና መርሆዎች ላይ የተመሰረተ ሲሆን ግልጽነት፣የባለድርሻ አካላት ተሳትፎን ማጠናከር ስልታዊ ምሰሶዎች ናቸዉ፡፡
የኦዲት ግንኙነት መርሆዎች
• ግልጽነት፡ ዉስብስብ ቃላትን ማስወገድና ቀላል፣ ቀጥተኛ ቋንቋን በመጠቀም ሁሉም አንባቢዎች መልእክቱን እንዲረዱ ማስቻል።
• ትክክለኛነት፡ ሁሉንም ግኝቶች እና ሪፖርቶች በጠንካራ እውነታዎች፣ ግልጽ እና ትክክለኛ መረጃዎች ላይ የተመሰረት ማድረግ።
• ተጨባጭነት፡ መረጃዎችን ገለልተኛና ሚዛናዊ አድርጎ ማቅረብ።
• ወቅታዊነት፡ የሚጋሩት የኦዲት ሪፖርቶች ትኩስ፡ወቅታዊና ጊዜን የጠበቁ መሆን አለባቸዉ፡፡
• ምጥን፡የተግባቦት መልዕክቶቹ አጭር፡ አንኳር መረጃዎችን ያካተቱ አድርጎ ማቅረብ ናቸዉ፡፡
የኦዲት ባለድርሻ አካላት ግንኙነት ምሰሶዎች
• ግልጽነት፡ ስለ ኦዲት አላማ፡ግቦች፣ ዘዴዎች እና ውጤቶች ግልጽ፣ ቀጥተኛ መረጃን ለሁሉም ባለድርሻ አካላት ማጋራት።
• መደበኛ ግንኙነት፡- ከባለድርሻ አካላት ጋር በስብሰባዎችና ሌሎች የግንኙነት አጋጣሚዎች በኦዲት ተግባር፡ሂደትና ስለሚያጋጥሙ ችግሮች ከባለድርሻ አካላት ጋር በመደበኛነት መነጋገርና መወያት፡፡ • የጋራ መተማመንን መፍጠር፡- የተሳታፊዎችን ሐሳብ በማክበርና ቅንነትን በተላበሰ መንገድ ጠንካራ ትስስር መፍጠር፡፡
ከባለድርሻ አካላት ከፍተኛ ታማኝነትን በመጠበቅ እና የእያንዳንዱን ቡድን ሚና በማክበር ጠንካራ የስራ ትስስር ይገንቡ።
• ምላሽ ሰጪነት፡- የባለድርሻ አካላትን አስተያየት በጥንቃቄ በማድመጥና ያዳምጡ እና ለጥያቄዎቻቸው በፍጥነት ምላሽ በመስጠት ግንኙነትን ማጠናከር ።
• የእሴት ፈጠራ፡- የኦዲት መሰረታዊ አላማና ግብ የመንግስት ሀብትና ንብረት ለታለመለት አላማ መዋሉን የማረጋገጥ ተግባር መሆኑን ግልፅ በማድረግ ባለድርሻ አካላት እሴት አንዲጨምሩ ማበረታታት ናቸዉ፡፡
በአጠቃላይ በጥሩ ሁኔታ የተዘጋጀ የኦዲት ኮሙኒኬሽን ስትራቴጂ ለተሳካ የኦዲት ተግባር ቁልፍ ሲሆኖን ሂደቱም ግልጽነትን፣ እና የባለድርሻ አካላትን ተሳትፎ ያረጋገጠ መሆን አለበት።
ጠንካራ የኦዲት ስነ- ተግባቦት የሚከተሉትን ቁልፍ ስልቶችን ያካትታል
 ግልፅ አላማና የጊዜ ሰሌዳ ማካተት፡
 ባለድርሻ አካለትን መለየትና ማሳተፍ፡
 ዘርፈ-ብዙ የመገናኛ ዘደዎችን መጠቀም፡
 ግብረ-መልስ የሚገኝበትን መንገድ ማበጀት እና
 በመደበኛነት አዳዲስ መረጃዎችን ማሰራጨትና የሂደት ሪፖርት ማቅረብን ያጠቃልላል፡፡

ነሀሴ 1 /2018የማእከላዊ ኢትዮጲያ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር፣5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 6ኛ መደበኛ ጉባኤ ላይ  የክልሉን ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ሪፖርት አድምጧል የክልል ዋና ኦዲተር መስ...
07/08/2026

ነሀሴ 1 /2018

የማእከላዊ ኢትዮጲያ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር፣5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 6ኛ መደበኛ ጉባኤ ላይ የክልሉን ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ሪፖርት አድምጧል

የክልል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ዋና ኦዲተር ወ/ሮ ፈዲላ አደም የ2018 የኦዲት ሪፖርት ለምክር ቤቱ ባቀረቡት ወቅት እንደገለጹት በ2018 88 ተቋማት ኦዲት ለማድረግ ታቅዶ 83 ተቋማት 94/100 ኦዲት መደረጉ ገልፀው ትክክለኛ ገፅታ የሚያሳይ አስተያየት የተሰጠባቸው መ/ቤቶች 9፣ አልፎ አልፎ የሚጠቀስ ችግር በመታየቱ ነቀፌታ አስተያየት የተሰጠባቸው 33፣ ጎላ ያለ ችግር በመታየቱ ተቀባይነት የሚያሳጣ አስተያየት የተሰጠባቸው 22 እና አስተያየት መስጠት ያልቻለባቸው 1መ/ቤት መሆኑን በሪፖርታቸው ገልፀዋል ።
የምክር ቤቱ አባላት በበኩላቸ የክልሉ ዋና ኦዲተር መ/ቤት የክልሉ በጀት ለልማት መዋሉና አለመዋሉ ኦዲት ማድረግ ዋና ሀላፊነቱ መሆኑ ገልፀው የተገኙ የኦዲት ግኝት የማስመለሱ ተግባር ግን የአስፈፃሚውና የምክር ቤት አባላት ሀላፊነት መሆኑ ገልፀዋል ።
በመጨረሻም በክልሉ ዋና ኦዲተር የቀረበ የ2019 ጠቋሚ እቅድና እቅዱን ለማስፈፀም የቀረበ 68ሚሊየን .642ሺ .651 ብር በጀት ቀርቦ በምክር ቤቱ አባላት በሙሉ ድምፅ ፀድቋል።

ዘገባው የክልሉ ዋና ኦዲተር መ/ቤት የኮሚዩኒኬሽን ዳሬክቶሬት ነው!

02/07/2026
ኦዲት አላማዉ ስህተት መፈለግ ሳይሆን የህጋዊነት፡የኢኮኖሚያዊነት፡የቅልጥፍና እና የዉጤታማነት መርህን የጣሱ አሰራሮችና ጉዳዮች በፍጥነት በመለየት የስራ አመራሩ የእርምት ወይም የመከላከያ እር...
25/06/2026

ኦዲት አላማዉ ስህተት መፈለግ ሳይሆን የህጋዊነት፡የኢኮኖሚያዊነት፡የቅልጥፍና እና የዉጤታማነት መርህን የጣሱ አሰራሮችና ጉዳዮች በፍጥነት በመለየት የስራ አመራሩ የእርምት ወይም የመከላከያ እርምጃ እንዲወስድ ማድረግ ነዉ፡፡

የኦዲት ተግባር ዋና ዋና ቃላቶ(ሀረጎች) እና ትርጉሞቻቸዉ• ኦዲት(Auditing)፡ የመንግስት መ/ቤት የሒሳብ መግለጫ በህግ፡ደንብና መመሪያ መሰረት የተዘጋጀ መሆኑን ወይም አንድ ፕሮጀክት(ፐ...
15/05/2026

የኦዲት ተግባር ዋና ዋና ቃላቶ(ሀረጎች) እና ትርጉሞቻቸዉ
• ኦዲት(Auditing)፡ የመንግስት መ/ቤት የሒሳብ መግለጫ በህግ፡ደንብና መመሪያ መሰረት የተዘጋጀ መሆኑን ወይም አንድ ፕሮጀክት(ፐሮግራም) ኢኮኖሚያዊ፡ቀልጣፋና ዉጤታማ በሆነ መልኩ መከናወኑን ከቀረቡት ማስረጃዎች ጋር በማመሳከር አስተማማኝ ማረጋገጫ መስጠት ነዉ፡፡
• የውጭ ኦዲት(External audit)፡ የፋይናንስ መግለጫዎችን ከቁሳዊ የተሳሳተ መግለጫ ነፃ መሆናቸውን ወይም አለመሆኑን በተመለከተ በውጭ ኦዲተሮች ገለልተኛ ምርመራ በመገምገም አስተማማኝ ማስረጃ በዋናነት ለሶስተ ኛ ወገን የሚሰጥ የኦዲት አካል ።
• የውስጥ ኦዲት(Internal audit)፡ የአንድ ተቋም የፋይናንስ አስተዳደር እና የውስጥ ቁጥጥር ሂደቶች ውጤታማ በሆነ መንገድ እየተከናወኑ ስለመሆናቸውን የማረጋገግጥ ተግባር ነዉ።
• የህጋዊነት ኦዲት(Compliance/Regularty/audit)፡የአንድ ተቋም የፋይናንስ አካሄድ ለወጡ ህጎች፣ ደንቦች፣ ወይም ደንቦች መከተሉን የመገምገም ተግባር ነዉ።
• የአሠራር ኦዲት(Operational audit)፡ የአሠራር ሂደቶችን ውጤታማነት እና ቀልጣፋነት የመገምገም ሂደት ነዉ።
• ልዩ ኦዲት(Foreinsic audit) ከሚመለከታቸዉ አካላት የማጭበርበር፣ የሙስና ወይም የህግ ጥሰትና ብልሹነት ስለመኖሩ ጥቆማ ሲቀርብ ወይም እነዝህ ችግሮች ስለመከሰታቸዉ አሳማኝ ማስረጃ ሲገኝ የሚደረግ የፋይናንስ መዝገቦች መርመራ ነዉ።
• የአይቲ ኦዲት(IT audit)፡ የቴክኖሎጂ ቁጥጥሮችን፡ የመረጃ ቅንነትና የደህንነት ስርዓቶችን አጠቃላይ ክለሳ ወይም ግምገማ መለት ነዉ።
• አሉታዊ አስተያየት(Adverse opinion)፡ የፋይናንስ መግለጫዎቹ ስህተት ያለባቸዉና የመ/ቤቱን የፋይናንስ አቋም በትክክል የማይወክሉ መሆናቸውን የሚያሳይ የኦዲተር ሪፖርት ነዉ።
• የትንታኔ ሂደቶች(Analtical procedures)፡- በፋይናንስ እና በገንዘብ ነክ ባልሆኑ መረጃዎች መካከል ያሉትን ግንኙነቶች በመተንተን የፋይናንስ መረጃዎችን አሳማኝነትን መገምገም ማለት ነዉ።
• የኦዲት ማስረጃ(Audit evidence)፡- የኦዲት ግኝቶችን ለማጠናቀር በኦዲተሩ የሚሰበሰቡ መረጃዎች ማለትም ሰነዶች፣ ምልከታዎች እና ማረጋገጫዎች የሚያጠቃልል ነው።
• የኦዲት ግኝት(Audit finding)፡- የኦዲት ግኝት በኦዲተሩ የተገኘ ልዩ ችግር፣ ድክመት ወይም የወጡ የፋይናንስ ህጎችና ደንቦች አለማክበራቸዉን፣ ለምሳሌ በፋይናንስ መዝገቦች ላይ የተገኙ ስህተቶች፣ የውስጥ ቁጥጥሮች መላላት ወይም ጥሰቶች የሚያሳይ ጥንቅር እንደማለት ነዉ ።
• የኦዲት ሪፖርት (Audit report):ኦዲተሩ ስራዉን ሲያጠናቅቅ የሚያዘጋጀው የመጨረሻው፣ መደበኛ ሰነድ ሲሆን እነዚህን ከላይ የተገለፁትን ግኝቶች የሚዘረዝር እና የአንድ መ/ቤት የፋይናንስ መግለጫዎች ትክክለኛነት ላይ አስተያየት የተሰጠበት ዘገባ ነዉ።
• የኦዲት አስተያየት (Audit opinion)፡- በፋይናንስ መግለጫዎች ትክክለኛነት ላይ የመጨረሻ፣ ሙያዊ መደምደሚያ (ለምሳሌ፣ ብቁ ያልሆነ፣ ብቁ ፣ አሉታዊ) በማለት የሚሰጥ አስተያየት ነዉ።
• የኦዲት ፕሮግራም(Audit program)፡- የኦዲት ቡድኑ ሊከተላቸው የሚገቡ ዝርዝር መመሪያዎች እና ሂደቶች መርሃ-ግብር ነዉ።
• የኦዲት ስጋት(Audit risk)፡- ኦዲተሩ ያገኛቸዉ የፋይናንስ መግለጫዎች ከተቀመጡ ህጎችና ደንቦች አንፃር ስህተት ያለባቸዉመሆኑን ለመግለፅ የሚሰጥ የስጋት አስተያየት ነዉ።
• የኦዲት ሒደቶች (Audit trail)፡- አጠቃላይ ሂደቱን ለማረጋገጥ በሚያስችል መልኩ እያንዳዱን የፋይናስ ኡደትበጊዜ ቅደም ተከተል ያለውን ፍሰት ደረጃ በደረጃ መዝገብ ነዉ።
• የማካካሻ ቁጥጥሮች(Compensation control)፡- በውስጣዊ ቁጥጥሮች ውስጥ የሚታወቅ ድክመትን ለመቀነስ የሚያገለግሉ ተለዋጭ ሂደቶች ወይም ቁጥጥሮችየመፈተሸበት ሂደት ነዉ።
• የአካባቢ ቁጥጥር(Environmental control)፡- አጠቃላይ የዉስጥ አሰራር በተቋሙ የተቀመጡ ፖሊሲዎች፣ የአሠራር ሂደቶችና ደንቦችን የተከተሉ ስለመሆናቸዉ የሚደረግ ከባቢያዊ ቁጥጥር ማለት ነዉ፡፡።
• የአስተያየት ማስተባበያ(Disclaimer of opinion)፡- ኦዲተሩ አስተያየት ለመስጠት በቂ ማስረጃ ማግኘት በማይችልበት ጊዜ የሚደርስበት ዉሳኔ፣ በዚህም ምክንያት አስተያየት ለመስጠት መቸገሩን የሚገልፅበት ሁኔታ ነዉ፡፡
• የመስክ ሥራ(Field work)፡- ምርመራው በደንበኛው ቦታ የሚካሄድበት የኦዲት ደረጃ።
• የውስጥ ቁጥጥሮች(Internal controls)፡- የፋይናንስ ሪፖርት አስተማማኝነት፣ የአሠራር ቅልጥፍና፡ ህግና ደንብን የተከተሉ ግቦችን ማሳካት የሚያስችሉ መሆናቸዉን ለማረጋገጥ የዉስጥ ቁጥጥር ስርአት ነዉ፡፡።
• ቁሳዊነት(Materiality)፡- የፋይናንስ ግድፈቱ ወይም የተሳሳተ መግለጫው የአስፈላጊነት ገደቡ በተቋሙኢኮኖሚያዊ ውሳኔዎች ላይ ተጽዕኖ ሊያሳድር የሚችል ከሆነ ጉዳዩ ቁስ አካል ሆነ ማለት ነዉ።
• ሙያዊ ጥርጣሬ(Proffessional skeptism)፡-የኦዲት ማስረጃዎችን በመጠርጠርና በመጠየቅ ወሳኝ ግምገማ የማድረግ አመለካከት ነዉ።
• ብቁ አስተያየት(Qualified opinion)፡- ኦዲተር አስተያየት በፋይናንስ መግለጫዎቹ ላይ በተወሰነ፣ከተወሰኑት በስተቀር በትክክል ቀርበዋል ሲል የሚሰጠዉ ማረጋገጫ ነዉ።
• የስጋት ግምገማ(Risk assessment)፡- አንድ ተቋም ግቦቹን እንዳያሳካ እንቅፋት ለሆኑ የሚችሉ ስጋቶችን መለየት እና መተንተን ነዉ።
• ናሙና(Sampling)፡- የተወሰኑ ተቋማት መርጦ በመዉሰድና ኦዲት በማድረግ በሌሎች ተመሳሳይ መ/ቤቶች መደምደሚያ ለመፍጠር የሚያስችል የኦዲት ሂደት ትግበራ ነዉ።
• ተጨባጭ ሂደቶች(Substantiative procedure)፡- ቁሳዊ ስህተቶችን ለመለየት የተነደፉና በማረጋገጥ ሂደት የሚተገበሩ የቀሪ ሂሳቦችን ጨምሮ የኦዲት ሙከራዎች፣ የምርመራና ግብይት ዝርዝሮችን ያጠቃልላል ።
• ያልተሟላ(ብቁ ያልሆነ) አስተያየት(Unqualified opinion)፡- የፋይናንስ መግለጫዎቹ በሁሉም ቁሳዊ መለኪያዎች በአግባቡ መቅረባቸዉን የሚገልጽ "ንፁህ" ሪፖርት።

ለመ/ቤቱ ክዋኔና ፋይናንሻል  ኦዲተሮች በኦዲት ማንዋል 2025  ሲሰጥ የነበረው ሥልጠና ተጠናቀቀ""30/8/2018"" ቡታጅራለማእከላዊ ኢትዮጲያ  ክልል ዋና ኦዲተር መ/ቤት ለክዋኔና  ለፋይ...
08/05/2026

ለመ/ቤቱ ክዋኔና ፋይናንሻል ኦዲተሮች በኦዲት ማንዋል 2025 ሲሰጥ የነበረው ሥልጠና ተጠናቀቀ
""30/8/2018"" ቡታጅራ
ለማእከላዊ ኢትዮጲያ ክልል ዋና ኦዲተር መ/ቤት ለክዋኔና ለፋይናንሻል ኦዲተሮች ለ5 ተከታታይ ቀናት ሲሰጥ የነበረው ሥልጠና የተጠናቀቀ ሲሆን በማጠናቀቂያው መድረክ ላይ ተገኝተው የመዝጊያ ንግግር ያደረጉት የክልሉ ዋና ኦዲተር ወ/ሮ ፈዲላ አደም የፌደራል ዋና ኦዲተር መ/ቤት አሰልጣኞችን አመስግነዉ ከስልጠናው ብዙ የኦዲት አሰራር ልምዶች እንደተገኙ ገልጸው የተሻለ ሥራ እንድንሰራ እድል የሰጠ ነው ብለዋል፡፡ ከስልጠናው ባገኘነው እውቀት በኛ ደረጃ ያለንን አቅም ተጠቅመን ዓለም አቀፍ የኦዲት ደረጃዎችን/ስታንደርድ/ የጠበቀ የኦዲት ሥራ መስራት ይጠብቅብናል ያሉት ዋና ኦዲተሯ ኦዲተሮቹ ከስልጠናው ያገኙትን እውቀትና ልምድ ተጠቅመውና ራሳቸውን በየጊዜው በማሻሻል ተወዳዳሪ በመሆን ደረጃውን የጠበቀ የኦዲት ሥራ መስራት እንዳለባቸው አሳስባዋል፡፡

በፌዴራል ዋና ኦዲተር መ/ቤት የትምህርትና ሥልጠና ክፍል አሰልጣኞች እንደተናገሩት ከpre-requisit እስከ Reporting የተካተቱ 7 የኦዲት ፌዞች ላይ ያተኮረ ስልጠና ሲሆን የአለም አቀፍ ኦዲት ተቋም በየጊዜዉ ወቅቱን ያማከለ ,ስጋትን መሰረት ያደረገ ኦዲት የሚከናወንበት ማንዋል ያዘጋጃል በመሆኑም የአለም አቀፍ ኦዲት ስታንዳርድ የሚከተል ተቋም ለመገንባት የተሻሻሉ ማንዋሎች ላይ ኦዲተሮች በቂ እዉቀት እንዲጨብጡ በማድረግ ስጋትን መሰረት ያደረገ በዜጎች ዘንድ ተአማኒነት ያለዉ ነፃ ገለልተኛ እና ጥራቱን የጠበቀ ኦዲት ለማከናወን ያግዛል ብለዋል::

የስልጠናው ተሳታፊ ኦዲተሮች በበኩላቸው ሥልጠናው አዳዲስ የኦዲት አሰራሮችን የቀሰሙበትና ይበልጥ ለሥራ ያነሳሳቸው መሆኑን ገልጸው በተለይም በቅርቡ ወደ ኦዲት ሥራ ለተቀላቀሉ ኦተሮች የሥልጠናው አስፈላጊነት የጎላ ነው በማለት አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡

ዘገባው የኮሙኒኬሽንና የሚዲያ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ነው!

ለመ/ቤቱ ፋይናንሻልና ህጋዊነት ኦዲተሮች እየተሰጠ ያለው ስልጠና የዛሬ ውሎ በፎቶ
05/05/2026

ለመ/ቤቱ ፋይናንሻልና ህጋዊነት ኦዲተሮች እየተሰጠ ያለው ስልጠና የዛሬ ውሎ በፎቶ

የማእከላዊ ኢትዮጲያ ክልል መንግስት ዋና ኦዲተር መ/ቤት በተሻሻለው የፋይናንሻልና እና  ክዋኔ ኦዲት ማኑዋል  ላይ  ለመ/ቤቱለፋይናንሻል እና  ለክዋኔ ኦዲተሮች ስልጠና  መስጠት ተጀመረ"""...
04/05/2026

የማእከላዊ ኢትዮጲያ ክልል መንግስት ዋና ኦዲተር መ/ቤት በተሻሻለው የፋይናንሻልና እና ክዋኔ ኦዲት ማኑዋል ላይ ለመ/ቤቱ
ለፋይናንሻል እና ለክዋኔ ኦዲተሮች ስልጠና መስጠት ተጀመረ
""""26/8/2018 ቡታጅራ ""
ስልጠናውን በንግግር ያስጀመሩት የማእከላዊ ኢትዮጲያ ክልል መንግስት ምክትል ዋና ኦዲተር አቶ መሀመድ አብደላ የኦዲት ስራ በየጊዜው ራስን በእውቀት ማሳደግና አዳዲስ አሰራሮች ጋር ማስተዋወቅ የሚጠይቅ ስራ በመሆኑ መ/ቤቱ የኦዲተሮችን አቅም በስልጠና ለመገንባትና የተመርማሪ ተቋማትን የአሰራር ችግሮች በመፈተሽ ወደ ተሻለ አፈጻጸም ለማሻገር የሚረዳ ስልጠና ነው ብለዋል፡፡ ምክትል ኦዲተሩ አክለውም ስልጠናው በስራ ላይ የሚያጋጥሙ ችግሮችን ለመፍታት የሚረዱ አዳዲስ ልምዶችን የምንቀስምበትና ለቀጣይ ስራችንም እንደ ግብዓት የምንጠቀምበት መሆን ይገባዋል ሲሉ አሳስበዋል፡፡

ስልጠናው የሚሰጠው በፌደራል ዋና ኦዲተር መ/ቤት የስልጠና ኢንስተራክተሮች አቶ ኢዮብ ጉታ፣ አቶ ቴዎድሮስ ሽመልስ ፣አቶ መልካሙ ባሻ እና አቶ ጌትነት አለሙ ሲሆን በተሻሻለው የፋይናንሻል እና ክዋኔ ኦዲት ማኑዋሎች እና ሌሎችም ይዘት ያላቸዉ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ስልጠና ይሰጣል።

ዘገባው የመ/ቤቱ የኮሙኒኬሽንና የሚዲያ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ነው።

Address

Wolkite

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when CERG Office of Auditor General የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ዋና ኦዲተር መ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share