በጉራጌ ዞን የጌታ ወረዳ የመንግስት ኮምንኬሽን ጉ/ጽ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Wolkite
  • በጉራጌ ዞን የጌታ ወረዳ የመንግስት ኮምንኬሽን ጉ/ጽ/ቤት

በጉራጌ ዞን የጌታ ወረዳ የመንግስት ኮምንኬሽን ጉ/ጽ/ቤት ይህ በጉራጌ ዞን የጌታ ወረዳ የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት ነው

‎እነሆ የማይቀርበት ቀጠሮ  ደረሰ !!!‎‎የጘታ ወረዳ አስተዳደር በአዲስ አበባና ከክፍለ ሀገር ከሚገኙ የአካባቢው ተወላጆችና ልማት ወዳዶች ጋር ሊያደርግ ያሰበው ታላቅ የውይይት መድረክ ሁለ...
28/08/2026

‎እነሆ የማይቀርበት ቀጠሮ ደረሰ !!!

‎የጘታ ወረዳ አስተዳደር በአዲስ አበባና ከክፍለ ሀገር ከሚገኙ የአካባቢው ተወላጆችና ልማት ወዳዶች ጋር ሊያደርግ ያሰበው ታላቅ የውይይት መድረክ ሁለት ቀን ብቻ ቀረው።

‎የጘታ ክፍለ ሕዝብ የልማት ኮሚቴ ከጘታ ወረዳ አስተዳደር ጋር በመተባበር ያዘጋጁት ታላቅ የውይይት መድረክ ላይ በአዲስ አበባና ክፍለ ሀገር የምትገኙ የወረዳችን ተወላጆችና ልማት ወዳዶች በአጠቃላይ የፕሮግራሙ ተሳታፊ እንድትሆኑ የወረዳው መንግስት የከበረ ጥሪውን ያስተላልፋል።

‎" ኑ የጌታ ወረዳን በጋራ እናልማ!! "
‎መጪው ነሐሴ 24/2018 ዓ.ም እሁድ ከጠዋቱ 3:00 አዲስ አበባ ሰሜን ሆቴል የመሰብሰቢያ አዳራሽ አይቀርም።

‎የጌታ ወረዳ አስተዳደር

የውጭ ሀገር ስራ ስምሪት አቋራጭ መንገድ የለውም የጌታ ወረዳ ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳዮች ጽህፈት ቤት21/12/2018ዓ.ም(ቋንጤ )በጌታ ወረዳ ህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርን ለመግታት እንዲሁም ህ...
27/08/2026

የውጭ ሀገር ስራ ስምሪት አቋራጭ መንገድ የለውም የጌታ ወረዳ ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳዮች ጽህፈት ቤት

21/12/2018ዓ.ም(ቋንጤ )
በጌታ ወረዳ ህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርን ለመግታት እንዲሁም ህጋዊ የስራ ስምሪትን ለማጠናከር ያለመ በወረዳው ሰራተኛና ማህበራዊ ጉ/ጽ/ቤትና ከወረ ኢንተርፕራይዝ ጽ/ቤት በጋራ በመሆን ወረዳዊ የንቅናቄ መድረክ በቋንጤ ከተማ ተካሄደ።

የወረዳው ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ፖለቲካ ዘርፍ ሀላፊና አብይ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ሀምዱ ንዳ የወረዳችን ዜጎች ሰልጥነውና በቅተው በሕጋዊ መንገድ ሰብአዊ መብታቸው፣ ደህንነታቸው እና ክብራቸው ተጠብቆ በውጭ ሀገር የስራ ዕድል ተጠቃሚ ማድረግ ላይ በትኩረት መስራ ይገባል ብለዋል ።

ግሎባላይዜሽንና የሰራተኛ ፍልሰት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳቸው ከፍተኛ ቢሆንም፣ ሕጋዊ ያልሆነና ስልታዊ ቁጥጥር ያልተደረገበት የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ዜጎች በሰብአዊ መብታቸው ላይ ከፍተኛ ጥሰት እንዲደርስባቸው፣ ለስቃይና ለሕገወጥ አዘዋዋሪዎች ሰለባ እንዲሆኑ አድርጓል።

ሀገራችን ሕጋዊ፣ ደህንነቱ የተጠበቀ እና ሰብአዊ መብትን ያከበረ የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ሥርዓት ለመዘርጋት አዋጆችንና መመሪያዎችን አሻሽላ ተግባራዊ እያደረገች ትገኛለችም ብለዋል።

የአብይ ኮሚቴ ሰብሳቢዉ አያይዘዉም በወረዳው የዜጎችን ደህንነትና መብት ለማስጠበቅ፣ ሕገወጥ የሰዎች ዝውውርን ለመከላከል እና ሕጋዊ ሂደቱን ለማስረጽ የባለድርሻ አካላትን ግንዛቤ ማሳደግ ወሳኝ ነው ብለዉ ተጠናክሮ መሄድ እንዳለበት አመላክቷል ።

የወረዳው ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ሀላፊ ወይዘሮ ደስታ ገብሬ በበኩላቸው ሕገወጥ ደላላዎችን መከላከልበህገወጥ የሰዎች ዝውውር ላይ የሚንቀሳቀሱ አካላትን በመከላከል ረገድ የኅብረተሰቡን እና የባለድርሻ አካላትን ንቁ ተሳትፎ ሊኖር እንደሚገባ አሳስበዋል ።

የንቅናቄው አላማ የዜጎች መብት፣ ደህንነትና ክብር ተጠብቆ በውጭ ሀገር እንዲሰሩ ለማድረግ ነው ብለዉ በሰው የመነገድና ሰውን በሕገ-ወጥ መንገድ የማሻገር ወንጀልን ለመከላከል ሕጋዊ የስምሪት መስመሮችን ለማጠናከር መሆኑ አስገንዝበዋል ።

ማንኛውም ስምሪት በሚኒስቴሩ የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓት ውስጥ መመዝገብ እንዳለበት አንስተው ሚኒስቴሩ የሥራና ሠራተኛ ማገናኘት ፈቃድ ካልሰጠው በስተቀር ማንኛውም ሰው ሠራተኛ መመልመል ወይም መላክ አይችልም ብለዋል ።

መንግስት የዜጎች መብትና ደህንነት ከሚከበርባቸው እንደ ሳውዲ አረቢያ፣ የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ፣ ጆርዳን፣ ኳታር፣ ሊባኖስ (ቤሩት) እና ኩዌት ከመሳሰሉ የመዳረሻ ሀገራት ጋር አስተማማኝ የሁለትዮሽ ስምምነት መፈራረሙን አስታውቀዋል።

የወረዳው ኢንተርፕራይዝ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ አክመል ተካ በወረዳችን ባለዉ ELMIS ኪት ለውጭ ሀገር የስራ ስምሪት ምዝገባ ብቁ ለማድረግእየተሰራ መሆኑ አንስተው የስራ ፈላጊ ዜጎች ምዝገባ ያለምንም መጉላላት የተቀላጠፈ አገልግሎት እንዲሰጡ ጠንካራ ክትትል እየተደረገ ነዉ ብለዋል ።

ብቁ ዜጎች እንደ የክህሎት ደረጃቸውን በመለየት ወደ ተለያዩ መዳረሻ ሀገራትና የሥራ ዘርፎች የመመደብ ሥርዓት ላይ የሚሰሩ ስራዎች ጥሩ መሆናቸው ገልፀው በወረዳዉ የሚገኝ ሥራ ፈላጊ ዜጋ ELMIS ላይ በራሱ ወይም በአቅራቢያው በሚገኝ የስራ ማዕከል አገልግሎት (Job Center) በነፃ እንዲመዘገብ እየተደረገ ነዉ ብለዋል

ተሳታፊዎች በበኩላቸው ህገወጥ የሰዎች ዝዉዉር ሰውን እንደ እቃ መሸጥ መሆኑ አንስተው ወጣቶች ከዚህ እኩይ ተግባር በመቆጠብ ራሳቸውን ከአደጋ ሊጠብቁ ይገባል ብለዉ የሚመለከታቸው አካላት አስፈላጊውን ግንዛቤ ሊሰጡ ይገባል ብለዋል ።

ዘገባው የወረዳው መ/ኮ/ጉ/ጽ/ቤት ነዉ ለበለጠ መረጃ ቴሌግራም https://t.me/+6-UPogtuRUM1YmU0
ፌስቡክ
https://www.facebook.com/share/18CS3XZhS5/
ቲክቶክ
https://www.tiktok.com/.werda?_r=1&_t=ZS-994GIjxZmir

ዩቲዩብ
https://youtube.com/channel/UC3TnBlY5-j5dZBt_aBjNKuw?si=OI8PgBxWBv6QcTX5

ኢንስታግራም
https://www.instagram.com/geta92544?igsi=MWZ4ZDI5NXE2c3lhbg==

በቀበሌ ደረጃ የሚገኙ የብልጽግና ፓርቲ አደረጃጀቶች በድጋፋዊ ሱፐርቪዥን በማጠናከር የ2019 በጀት አመት የፓርቲ ተግባራት  በስኬት መምራት እንደሚገባ ተጠቆመ ።21/12/2018ዓ.ም(ቋንጤ)...
27/08/2026

በቀበሌ ደረጃ የሚገኙ የብልጽግና ፓርቲ አደረጃጀቶች በድጋፋዊ ሱፐርቪዥን በማጠናከር የ2019 በጀት አመት የፓርቲ ተግባራት በስኬት መምራት እንደሚገባ ተጠቆመ ።

21/12/2018ዓ.ም(ቋንጤ)
የጌታ ወረዳ ብ/ፓ/ቅ/ፅ/ቤት በ2019 በጀት አመት የዝግጅት ምዕራፍ ላይ በተደረገው ድጋፋዊ ሱፐርቪዥን በጠንካራና በጉለት በታዩ ተግባራት የግብረ መልስ ሪፖርት የወረዳው አመራር በተገኙበት በቋንጤ ከተማ ገመገመ ።

የጌታ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ሀላፊ አቶ ሀምዱ ንዳ የሱፐርቪዥን ሥራው ዋና ዓላማ በቀበሌ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች እና አደረጃጀቶች የ2019 በጀት ዓመት የፓርቲ ተግባራት በድጋፋዊ ሱፐርቪዥን በጥልቀት በማየት ጉድለቶችን በፍጥነት ማረም ይገባል ።

ሀላፊዉ አያይዘዉም ምርጥ ተሞክሮዎችን ቀምሮ ማጎልበት፤ የአመለካከትና የተግባር መቀራረብ /መመጣጠን መፍጠር እና ለ2019 በጀት አመት ተልዐኮ በሁለንተናዊ መልኩ በብቃት መፈጸም ይኖርብናል ብለዋል ፡፡

የወረዳው ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አደረጃጀት ዘርፍ ሀላፊ አቶ ዲንሰፋ ሀቢብ በበኩላቸው በቀበሌ ደረጃ በ5ቱም ክላስተር የተደረገው ድጋፋዊ ሱፐርቪዥን አበረታች ተግባራት መኖራቸው አንስተው ከመረጃ አያያዝ ጋር በተገቢው መስራት እንደሚገባ አመላክቷል ።

በ2019 በጀት አመት ከእቅድ ዝግጅት ጀምሮ የፖርቲ የመንግስት ተልዕኮዎችን በተገቢው ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑ ምልከታና ድጋፍ በማድረግ ጥንካሬዎቹ ለማስቀጠል እና ጉድለቶቹ ላይ ማስተካከያ ለማድረግ ያለመ እንደ ነበር አንስተዋል ።

ጠንካራ አደረጃጀት ለጠንካራ ፓርቲ ወሳኝ መሆኑ ያነሱት አቶ ዲሰፋ ሁሉም ባለ ድርሻ አካላት አጠናክረው ሊመሩ እንደሚገባ አሳስበዋል ።

ተሳታፊዎች በበኩላቸው መድረኩ ወቅታዊ መሆኑ አንስተው ከእቅድ ጀምሮ ህዝብን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ስራዎች ለመስራት አደረጃጀቶች አጠናክረው እንደሚመሩም አመላክቷል ።
ዘገባው የወረዳው መ/ኮ/ጉ/ጽ/ቤት ነው ።

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በዞኑ የሌማት ትሩፋትና የተቀናጀ የግብርና ልማት ስራዎች ይበልጥ በማጠናከር ከድህነት የተላቀቀ ማህበረሰብ ለመፍጠር በትኩረት ተሰርቷል፦ ክቡር አቶ ላጫ ጋሩማነሀሴ 2...
27/08/2026

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በዞኑ የሌማት ትሩፋትና የተቀናጀ የግብርና ልማት ስራዎች ይበልጥ በማጠናከር ከድህነት የተላቀቀ ማህበረሰብ ለመፍጠር በትኩረት ተሰርቷል፦ ክቡር አቶ ላጫ ጋሩማ

ነሀሴ 21/2018 (ቋንጤ)

የጉራጌ ዞን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 4ኛ ዙር 13ኛ አመት 31ኛ መደበኛ ጉባኤ በወልቂጤ ከተማ እያካሄደ ይገኛል።

የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ላጫ ጋሩማ እንዳሉት በአንድ ዓመት እስከ 4 ጊዜ በማምረት የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ፣ የአርሶ አደሮችን ገቢ ማሳደግና የማህበረሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት ማሻሻል ተችሏል።

በጉራጌ ዞን በመንግስት ድጋፍና በአጋር ተቋማት ትብብር በግብርናው ዘርፍ አበረታች ለውጦች ተመዝግባል ብለዋል።

የዞኑ ግብርና ከባህላዊ አመራረት ወጥቶ ወደ ክላስተር እና ከዚያም ወደ ሜጋ ክላስተር በመሸጋገሩ በሀገር ደረጃ ትኩረት የሳበ ውጤት አስመዝግቧል።

ለአብነትም በአበሽጌ ወረዳ ከ36 ሺህ ሄክታር መሬት በላይ በአንድ ወጥ ማሳ መታረሱ እንደ ሀገር ተሞክሮ የተወሰደ ተግባር መሆኑ ገልጸዋል።

ሁሉም ወረዳዎች ያላቸውን የተፈጥሮ ጸጋ መሰረት በማድረግ በቆሎ፣ጤፍ፣ቡና፣ቅመማ ቅመም፣ ድንች፣ ስንዴ፣ ገብስ፣ ቃሪያ፣ የጓሮ አትክልትና ሌሎች ሰብሎችን በስፋት በማምረት የምግብ ዋስትናቸውን እያረጋገጡ ይገኛሉ ብለዋል።

በዞኑ ለግብርናው ዘርፍ በተሰጠው ልዩ ትኩረት 6ቱ የግብርና መሰሶዎችን በተጨባጭ ተግባራዊ ተደርጓል ያሉት አቶ ላጫ ለአብነትም ዘርፉ ለበርካታ ወጣቶች የስራ እድል በመፍጠር ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚ አድርጓል ሲሉ ገልጸዋል።

በዞኑ ከዚህ በፊት በአመት አንድና ሁለት ጊዜ ብቻ ይመረት ከነበረበት አሁን በአብዛኛው መዋቅር 3ጊዜና ከዛ በላይ በማምረት ምርትና ምርታማነትን በእጥፍ መጨመሩ አስታውቀዋል።

የሌማት ትሩፋትና የተቀናጀ የግብርና ልማት ስራዎች ይበልጥ በማጠናከር ከድህነት የተላቀቀ ማህበረሰብ ለመፍጠር በቁርጠኝነት እየተሰራ እንደሆነ በመግለፅ በተቀናጀ የግብርና ስራና በሌማት ትሩፋት የተጀመሩ ስራዎች ይበልጥ በማሳደግ ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል።

በዞኑ ምርታማነት ከጊዜ ወደ ጊዜ መጨመሩ ጠቁመው በሞዴል አርሶ አደሮች 120 ኩንታል በቆሎ፣ 320 ኩንታል ድንች፣ 33 ኩንታል ገብስና 48 ኩንታል ስንዴ በሄክታር ማምረት ተችሏል ሲሉ ተናግረዋል።

በ2018/19 የመኸር ወቅት 177ሺ 806 ሄክታር መሬት በተለያዩ ሰብሎች ለመሸፈን ታቅዶ መሰራቱና 26 ሺ 953 ሄክታር መሬት በመስኖ ልማት ማልማት መቻሉ በሪፖርታቸው ገልፀዋል።

በዞኑ የተቀናጀ ግብርና ስራና የሌማት ትሩፋት ስራዎች ውጤታማ ሲሆኑ የስጋ፣ የወተት፣ የዶሮ፣ የማርና የዓሣ መንደሮች በመቋቋማቸው የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ለብዙ ዜጎች የገቢ ምንጭ ሆነዋል ብለዋል።

የእንሰት በሽታን ለመከላከል ከዩኒቨርሲቲዎችና ከምርምር ተቋማት ጋር የተቀናጀ ሥራ እየተሰራ ሲሆን በዘንድሮው ዓመት ከ33 ሚሊዮን በላይ ፎንፎ ይገኛል ተብሎ ይጠበቃል።

በቀጣይም የተጀመሩትን የግብርና ልማት ሥራዎች በጥራት፣ በፍጥነትና በስፋት በማስቀጠል የአርሶ አደሩን ገቢ በማሳደግ፣ የምግብ ዋስትናን በማጠናከርና የዞኑን ህዝብ በላቀ ደረጃ ተጠቃሚ እንዲሆን በትኩረት ይሰራል ብለዋል።
ዘገባው የዞኑ መ/ኮ/ጉ/ መምሪያ ነው

‎የዞኑ የልማት ጸጋዎችና እሴቶች አጉልቶ ለማውጣት የኮሚኒኬሽንና ሚዲያ ዘርፉ በሰው ሀይል፣ በቁሳቁስና በበጀት መደገፍ ይገባል፦አቶ አበራ ወንድሙ‎‎ነሀሴ 20/2018(ቋንጤ)‎‎መምሪያው የ20...
26/08/2026

‎የዞኑ የልማት ጸጋዎችና እሴቶች አጉልቶ ለማውጣት የኮሚኒኬሽንና ሚዲያ ዘርፉ በሰው ሀይል፣ በቁሳቁስና በበጀት መደገፍ ይገባል፦አቶ አበራ ወንድሙ

‎ነሀሴ 20/2018(ቋንጤ)

‎መምሪያው የ2018 የስራ አፈጻጸም እና የ2019 እቅድ ላይ ያተኮር የውይይትና የምክክር መድረክ በወልቂጤ ከተማ አካሂዷል።

‎የጉራጌ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ሃላፊ አቶ አበራ ወንድሙ ሚዲያ በዞኑ እየተሰሩ ባሉ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች ላይ ህዝብና መንግስትን የሚያገናኝ ድልድይ መሆኑን ገልጸዋል።

‎የዞኑ የልማት ጸጋዎችና እሴቶች አጉልቶ ለማውጣት የኮሚኒኬሽንና ሚዲያ ዘርፉ በሰው ሀይል፣ በቁሳቁስና በበጀት መደገፍ ይገባል፦አቶ አበራ ወንድሙ

‎በዞኑ ጀፎረን ጨምሮ በርካታ ያልታዩና ያልተጎበኙ ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ ፀጋዎች መኖራቸውን ጠቁመው እነዚህ ሃብቶችን በማልማት በሃገር ደረጃ እንዲታወቁ በባለቤትነት መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

‎የጉራጌ ዞን የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ አቶ ሸምሱ አማን በዚህ ወቅት እንዳሉት ለተቋሙ የአመለካከት ለውጥ በማድረግ በሰው ሀይል፣ በቁሳቁስና በበጀት መደገፍ ይገባል።

‎የሚሰሩ የሚዲያ ስራዎች በጥራት በፍጥነትና በተደራሽነት በመስራት የዞኑ ማህበረሰብ የሚመጥን የሚዲያ ስራ መስራት ያስፈልጋል ብለዋል።

‎አቶ ሸምሱ አክለውም የጉራጊኛ ቋንቋ ለማሳደግ ሚዲያ የአንበሳውን ድርሻ ይወስዷል ያሉ ሲሆን ዘገባዎችን በጉራጊኛ መስራት እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል።

‎የሚዲያ ስራዎችን በገጽ ለገጽ፣በኤሌክትሮኒክስ ፣በህትመትና በማህበራዊ ሚዲያዎች ፕላትፎርሞች በመስፋት በመስራት የዞኑ ጸጋ፣እሴትችና ልማቶች ለአለም ማስተዋወቅ እንደሚገባ አስታውቀዋል።

‎ለኮሚኒኬሽንና ሚዲያ ስራዎች ውጤታማነት ከሚመለከታቸው ተቋሟትና ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እንዲሰራ የተናግረዋል።

‎በቀጣይ በጀት አመትም የጉራጌ የማህበረሰብ ቴሌቪዥን ስራ ለማስጀመር የዞኑ መንግስት በልዩ ትኩረት እየሰራ መሆኑን አቶ ሸምሱ አመላክተዋል።

‎የዞኑ የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ሃላፊ አቶ ሃዲሞ ሃሰን በኮሙኒኬሽን ዘርፉ የሚከናወኑ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን በመግለጽ በቀጣይም ማህበረሰቡን የሚመጥኑና ትውልድ ተሻጋሪ ተግባራትን መስራት እንደሚገባ አመልክተዋል።

‎የመድረኩ ተሳታፊዎች በበኩላቸው መምሪያው መረጃን ተደራሽ ለማድረግ የሚያደርገው ጥረት አበረታች መሆኑን ገልጸው በቀጣይም ለስራ ማነቆ የሆኑ የግብዓትና የባለሙያ ውስንነቶችን በመቅረፍ በጥራት ላይ የተመሰረተ መረጃ ለህዝብ ማድረስ እንደሚገባ አሳስበዋል።

‎የተለያዩ የሚዲያ አድማሶች በማስፋትና በማሰራጨት በበዞኑ በሚዲያ የበለጸገ ማህበረሰብ መፍጠር ይገባል ብለው ለዚህ ደግሞ አመራሩና ባለሙያዎች ስራቸው የበለጠ ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል ነው ያሉት።

‎በ2018 የተገኙ ጠንካራ ውጤቶች በማስቀጠልና ክፍተቶች በማስተካከል በ2019 የተሻለ ስራ ለመስራት አቅደው እንደሚሰሩ ገልጸዋል።

‎በመጨረሻም መምሪያው ከሁሉም መዋቅሮች የ2019 እቅድ ላይ የግብ ስምምነት በማድረግ በ2018 የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ መዋቅሮች እና ተቋማት እውቅናና ሽልማት አበርክቶላቸዋል።

‎በዚህም እኖር እና ምሁር አክሊል ወረዳዎች 1ኛ፣ቸሀ ወረዳ ደግሞ 2ኛ ሲወጡ በከተሞች ወልቂጤ ከተማ 1ኛ በመሆን እውቅናና ሽልማት አግኝተዋል።

የጉራጌ ዞን የመንግስት ኮሚኒኬሽን መምሪያ የ2018 የስራ አፈጻጸም እና የ2019 እቅድ ተኮር የውይይትና የምክክር መድረክ በወልቂጤ ከተማ ማካሄድ ጀመረ።ነሀሴ 20/2018(ቋንጤ)የጉራጌ ዞን...
26/08/2026

የጉራጌ ዞን የመንግስት ኮሚኒኬሽን መምሪያ የ2018 የስራ አፈጻጸም እና የ2019 እቅድ ተኮር የውይይትና የምክክር መድረክ በወልቂጤ ከተማ ማካሄድ ጀመረ።

ነሀሴ 20/2018(ቋንጤ)
የጉራጌ ዞን የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ የ2018 ዓ.ም ስራ አፈጻጸምና የ2019 እቅድ ጉባኤ በወልቂጤ ከተማ እያካሄደ ይገኛል።

የሚዲያ ዓላማ ወቅታዊ፣ ተዓማኒና ሚዛናዊ የሆነ መረጃን በማሰባሰብ ለማህበረሰቡ የመረጃ ፍላጎት ማሟላትና ተደራሽ ማድረግ ነው።

የጉራጌ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ እና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አበራ ወንድሙ በመክፈቻ ንግግራቸው መምሪያው በአመቱ በሰራቸው ስራዎች የዞኑ ጸጋዎችን ጎልተው እንዲወጡ አስችሏል ብለዋል።

ለአብነትም በዞኑ እየተከናወኑ ያሉ የተለያዩ የልማት ስራዎች፣የጉራጌ ማህበረሰብ በባህል እና ታሪክ፣ የህዝቦች የእርስ በርስ ግንኙነት እንዲጎለበት የማድረግ እና ሌሎችም ስራዎች መሰራታቸው በቀጣይ ተጠናክረው እንዲቀጥሉ አስገንዝበዋል አቶ አበራ።

የጉራጌ ዞን የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ አቶ ሸምሱ አማን እንዳሉት መምሪያዉ እስከ ታችኛው መዋቅር ድረስ በየወቅቱ የድጋፍና የክትትል ስራዎችን በመስራት ጠንካራ የኮሚኒኬሽን ተቋም እንዲገነባ ሲሰራ ቆይቷል።

የተለያዩ የመረጃ አማራጮች በመጠቀም ማህበረሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርግ ወቅታዊ፣ ሚዛናዊና ተዓማኒነት ያለው መረጃ ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት በመሰራቱ ውጤት ማስመዝገብ መቻሉ ገልጸዋል።

በተጨማሪ ዞናዊ፣ ክልላዊ፣ ሀገራዊና አለም አቀፋዊ መረጃዎችን ለህብረተሰቡ በፍጥነት እና በጥራት በማዳረስ ረገድ አበረታች ውጤቶችን ተመዝግቧል ብሏል አቶ ሸምሱ አማን።

በመድረኩም የጉራጌ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ እና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አበራ ወንድሙ ፣የጉራጌ ዞን የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ አቶ ሸምሱ አማን፣የጉራጌ ዞን ምክር ቤት የሴቶችና ወጣቶች ማህበራዊ ዘርፍ ቋሚ ሰብሳቢ ወ/ሮ ጥሩነሽ ምኑታ፣ የወረዳና የከተማ አስተዳደር ረዳት የመንግስት ተጠሪዎች፣ የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጽ/ቤት ኃላፊዎች እና ባለሙያዎች ተገኝተዋል።

የጉራጌ ዞን መንግስት ኣትራህቦት ጥፈት ሸመነ  የ2018 ዘበር የቾችዮ ሜና ግምገማም የ2019 ዘበር ኣትያኖት ያትኸኸርᎄ መድረክ በወርቕጤ ቤሮ (ከተማ) ቈነቪምናሴ 20/2018 (ዘበር) የጉ...
26/08/2026

የጉራጌ ዞን መንግስት ኣትራህቦት ጥፈት ሸመነ የ2018 ዘበር የቾችዮ ሜና ግምገማም የ2019 ዘበር ኣትያኖት ያትኸኸርᎄ መድረክ በወርቕጤ ቤሮ (ከተማ) ቈነቪም

ናሴ 20/2018 (ዘበር)

የጉራጌ ዞን መንግስት ኣትራህቦት መምሪያ ቦረ የ2018 ዘበር የቾችዮ ሜና ግምገማም የ2019 ዘበር ኣትያኖት ያትኸኸርᎄ መድረክ በወርቕጤ ቤሮ (ከተማ) ቈነቪም

የጉራጌ ዞን ይትኸተሮ ኣራባሪም ቹቻ ጥፈት ሸመነ ዳነ ኣበቃጥ ኣበራ ወንድሙ መድረክዌ በዘንጎት ባትቀነሶᎄ ግዝየ በዞንዌ ይቾችዮ ቡችር ቡችር ሜና ያትኸኸሪዬ የቾችዮ ሜና ያነንደ ደረግ ኣትኸነᎄም ባሮም።

ዞነንዳ የቱሪስት መደር ያᎀሪዬ የቈነሺዮ ሜና ባትቦት ያነንደ ፏር፣ ዋሻ፣ የቅራውዮ ድብር፣ ገዳም፣ መስጊድ፣ ጀፎረም ንᎀንዳ ይትኸኸሮዬ የመንግስት ኣትራሕቦት መዋቅር ሜነነ ይርቅ ሜና ወቶት ነረዎ ባሮም።

የዞንዌ መንግስት አትራህቦት መምሪያ ኣትራሕቦት ዳነ ኣበቃጥ ሸምሱ ኣማን መድረክዌ በዘንጎት ቲከፍቶ የዞንዌ ሐልቅ ተመንግስት ያትራክዊዬ የቾችዮ ሜና ወሔ ውጤት ኣትረከበም ባሮም።

መምሪያዌ የሐልቅዌ መረጃ በሕትመት፣ በኤሌክትሮኒክስ፣ በሶሻል ሚዲያ ያሰራ ቲሐር በዞነንዳ በሐልቅ፣ በመንግስት፣ በደንገነ ጨናትም፣ ብንጘድ አጉዣ ቢሐሮ ድርጅት የቾችዮ ሜና የሐልቄ ያሰሬ ባሮም።

በመድረክዌ የጉራጌ ዞን ወባጀ ቤት የማሕበራዊ ዘርፍ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እመዌቸ ጥሩነሽ ምኑታ፣ የጉራጌ ዞን የመንግስት ኣትራሕቦት መምሪያ ይትኸተሮ ዳነ ኣበቃጥ ዱላ ወርቁ፣ የዞንዌ ዝፓና ፓርቲ የኮሚኒኬሽን ዘርፍ ዳነ ኣበቃጥ ሓዲሞ ሓሰን፣ የወርቕጤ ኤፍ ኤም ቡር ዳነ ኣበቃጥ ፍቃዱ ዘለቀ፣ ያቤም ፕሮሞሽን ዳነ ኣበቃጥ ይታገሱ ማሞ፣ የጉራጌ ሐልቅ ቴሌቪዥን ዳነ ኣበቃጥ ሓሺም ጀማል፣ ይንም ወረዳም ከተማ ኣተድር የፖለቲካ ዘርፍ ዳነ፣ የመዋቅርዌ ዳነም ተርማሞትም ኣትያኖት ሜነነ ተረከዎም።

በየደረጃው የሚሰሩ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ስራዎችን በማጠናከር የምግብ ሉአላዊነታችንን በራስ አቅም መሸፈን እንደሚገባ ተገለፀ።ነሐሴ 19/2018 ዓ.ም [ቋንጤ]በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...
25/08/2026

በየደረጃው የሚሰሩ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ስራዎችን በማጠናከር የምግብ ሉአላዊነታችንን በራስ አቅም መሸፈን እንደሚገባ ተገለፀ።

ነሐሴ 19/2018 ዓ.ም [ቋንጤ]
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የተመደበው የሱፐርቪዥን ቡድን በጉራጌ ዞን ጌታ ወረዳ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ምልከታ አካሄደ።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ራህመቶ ቦካ የተመራ የኢንስፔክሽን ልዑክ በጌታ ወረዳ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት የሰብአዊ ድጋፍ ሉአላዊነት ማብሰሪያ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ተዘዋውሮ ጎብኝቷል።

ቡድኑ በወረዳና ቀበሌ ደረጃ እንደ ክልል የፊታችን ጥቅምት 30 ክልላዊ ሰብአዊ ድጋፍ ሉአላዊነት ለማብሰር እየተሰሩ ያሉ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ያሉበትን ደረጃ ተዘዋውሮ በመመልከት ለወረዳው አብይና ቴክኒክ ኮሚቴዎች የቃል ግብረ መልስ ሰጥቷል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ራህመቶ ቦካና የባለስልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ቀድሩ አብድላ በጋራ በሰጡት አስተያየት በወረዳው ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ኢኒሼቲቭ የምግብ ሉአላዊነት ራስን ለመቻል እየተሰሩ ያሉ ስራዎች በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ ገልፀዋል።

እንደ የኢንስፔክሽን ቡድኑ ገለፃ ተግባሩን በብቃት ለመምራት የሚያስችሉ ከወረዳ ጀምሮ እስከ ቀበሌ ድረስ የአብይና ቴክኒክ ኮሚቴዎች እንዲሁም ሌሎች ኮሚቴዎች በአግባቡ መደራጀታቸውንና ወደ ስራ መግባታቸውን ተናግረዋል።

በወረዳው ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ኢንሼቲቭ አካል የሆነው ወረዳዊ እቅድ 30 ሄክታር የገብስ ማሳ አሁናዊ ሁኔታን ተዘዋውረው በመጎብኘት ማሳው በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝና በቀጣይም ተገቢውን እንክብካቤና ክትትል በማድረግ ለውጤት ማብቃት እንዳለባቸው ገልፀዋል።

የወረዳው አብይና ቴክኒክ ኮሚቴዎችም ክልሉ በወረዳው ያደረገው የኢንስፔክሽን ስራ ወቅታዊ ከመሆኑም በላይ እንደ ወረዳ እየተሰሩ ባሉ የአደጋና ቅድመ መከላከል ስራዎች ጥንካሬና ጉድለቶችን በመለየት ጉድለቶቹን በፍጥነት በማረም የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ እድል የሰጠ ነው ብለዋል።

አክለውም እንደ ወረዳችን ተረጂ ባይኖርም ተጎጂዎች ሊኖሩ ስለሚችሉ በሚል ከ10 ሚሊየን ክብር በላይ ሀብት ለማሰባሰብ ግብ ተጥሎ እየተሰራ መሆኑንም ገልፀዋል።

በመጨረሻም በቀሪ ጊዜያቶች ክልሉ በመጪው ጥቅምት 30 ከተረጂነት በመውጣት ክልላዊ ሰብአዊ ድጋፍ ሉአላዊነት ለማብሰር የያዘውን ግብ እንደ ወረዳም ለማሳካት በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ ተናግረዋል።

በእለቱም የጉራጌ ዞን ውሃ ማዕድንና ኢነርጂ መምሪያ ሀላፊ አቶ አየለ ፈቀደ፣ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ በህሩ ኸይረዲንና የወረዳው ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ዘውዱ ዘፕሬን ጨምሮ የወረዳው የአደጋ ስጋት ቅድመ ማስጠንቀቂያ አብይና ቴክኒክ ኮሚቴ አመራርና አባላት ተገኝተዋል።
ዘገባው የወረዳው መንግስት ኮ/ጉ/ጽ/ቤት ነው።

ክቡር የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) ለ1ሺህ 501ኛው የነብዩ መሐመድ (ሰ•ዐ•ወ) የመውሊድ በዓል የእንኳን አደረሰችሁ መልዕክት አስተላለፉእንኳን ለ1501ኛው የነቢዩ መሐ...
24/08/2026

ክቡር የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) ለ1ሺህ 501ኛው የነብዩ መሐመድ (ሰ•ዐ•ወ) የመውሊድ በዓል የእንኳን አደረሰችሁ መልዕክት አስተላለፉ

እንኳን ለ1501ኛው የነቢዩ መሐመድ(ሰዐወ) የመውሊድ በዓል አደረሳችሁ

የነቢዩ መሐመድ ታሪክ ትውልድን ለበጎ ከሚቀርጹ ታሪኮች መካከል አንዱ ነው፡፡ የተጠሩበትን ዓላማ ማክበር፤ ለተጠሩበት ዓላማ ዋጋ መክፈል፤ የተጠሩበትን ለሌሎች ማካፈል፤ የተጠሩበትን አክብሮ መኖር - እነዚህ ሁሉ ሺ መጻሕፍት የሚወጧቸው ትምህርቶች ናቸው፡፡

ነቢዩ የተጠሩበትን ዓላማ በሚገባ ስለተገነዘቡ አክብረው ኖረዋል፡፡ የተጠሩት ለተራና ርካሽ ነገር እንዳልሆነ ተገንዝበዋል፡፡ የተጠሩት ትውልድን ለመቅረጽና ታሪክን ለመቀየር መሆኑን አምነዋል፡፡ ያንንም በቃላቸው፣ በሥራቸውና በኑሯቸው አክብረውት ነኖረዋል፡፡ ለታላቅ ሀገራዊ ዓላማ ተጠርተናል ብለን የምናምን ከሆነ ይህ የነቢዩ ሕይወት ታላቅ ትምህርት ይሆነናል፡፡ የተጠራንበትን ዓላማ በንግግራችን፣ በሥራችንና በሕይወታችን እንግለጠው፡፡

ነቢዩ ለተጠሩበት ዓላማ ዋጋ ከፍለዋል፡፡ ከቦታቸው ተሰደዋል፤ ምግብና መጠለያ ተነፍገዋል፤ ከቤተሰቦቻቸው ተለይተዋል፡፡ ለሞት በሚያበቁ ፈተናዎች ውስጥ አልፈዋል፡፡ ጦርነት ተከፍቶባቸዋል፡፡ ነገር ግን ሁሉንም በአላህ ኃይል አሸንፈዋል፡፡ ክብር ያለ መከራ አይገኝምና፡፡ እውነተኛ ሰው ለዓላማው እንደ ነቢዩ መሐመድ(ሰዐወ)ዋጋ ይከፍላል፡፡ ዓላማው የሚያስገኘውን ክብርና ጥቅም ብቻ ሳይሆን ዓላማው የሚያስከፍለውን መሥዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ ይሆናል፡፡

ነቢዩ መሐመድ(ሰዐወ) ከአላህ የደረሳቸውን መልእክት ለራሳቸው ብቻ አላስቀሩም፡፡ የተጠሩበትን ለሌሎች ለማካፈል ተግተዋል፡፡ መጀመሪያ በጣት ለሚቆጠሩ ሰዎች፣ በኋላም ለቅርብ ሱሐባዎች፣ በመጨረሻም ለዓለም መልእክቱን አዳርሰዋል ፡፡ እሳቸው የዘሩት ዘር እያፈራና እየጎመራ ተጉዟል፡፡ ዓላማችንን እኛ ማወቃችንና ማመናችን ብቻ ጥቅም የለውም፡፡ ሌሎች እንዲያውቁና እንዲያምኑ ልክ እንደነቢዩ ተገትተን መድከም አለብን፡፡

የነቢዩን መውሊድ ስናከብር ከሕይወታቸው እየተማርን፤ የተማርነውንም ለሀገረ መንግሥት ግንባታችን እየተጠቀምን እንዲሆን አደራ እላለሁ፡፡

በድጋሚ መልካም የመውሊድ በዓል ይሁንልን።

ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር!!
ፈጣሪ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ነሐሴ 19 ቀን 2018 ዓ.ም

Address

Geta
Wolkite

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when በጉራጌ ዞን የጌታ ወረዳ የመንግስት ኮምንኬሽን ጉ/ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share