Qajeelcha Poolisii Godina Booranaa

Qajeelcha Poolisii Godina Booranaa seeing a modern borena police force.

21/07/2026
ያቤሎ፤ ሐምሌ 14/2018 (የቦረና ዞን ፖሊስ)‎‎ፈጣን ፍርድ (RTD)‎‎በቦረና ዞን በጎሞሌ ወረዳ ተከሳሽ የሆነው አቶ አዲሱ ሹኑኩ ዋቆ በ14/11/2018 ዓ.ም. ከጠዋቱ 12:30 ሰዓት ...
21/07/2026

ያቤሎ፤ ሐምሌ 14/2018 (የቦረና ዞን ፖሊስ)

‎ፈጣን ፍርድ (RTD)

‎በቦረና ዞን በጎሞሌ ወረዳ ተከሳሽ የሆነው አቶ አዲሱ ሹኑኩ ዋቆ በ14/11/2018 ዓ.ም. ከጠዋቱ 12:30 ሰዓት አካባቢ የሰሌዳ ቁጥሩ 1/A48099 O/R የሆነ ባለሶስት ጎማ ባጃጅ በመጠቀም 220 ሊትር ቤንዚን (20 ሊትር የሚይዙ 11 ጄሪካኖች) ከምዕራብ ጉጂ ዞን ዱግዳ ዳዋ ወረዳ ወደ ቦረና ዞን ያቤሎ በሕገ-ወጥ መንገድ ሲያጓጉዝ መሆኑን ከአካባቢው ህብረተሰብ በደረሰ ጥቆማ መሰረት፣ የወረዳው ፖሊስ በሱሩፋ ከተማ ቀበሌ ካራቦሬ በተባለ ቦታ ተከታትሎ ተጠርጣሪውን ከማስረጃው ጋር በቁጥጥር ስር አውሏል።

‎የወንጀል ምርመራና የህግ አስከባሪ ቡድኑ የማስረጃ ፋይሉን አጠናቆ ለአቃቤ ህግ አቅርቦ፣ አቃቤ ህጉም በጎሞሌ ወረዳ ፍርድ ቤት ክስ ከፍቶ ተከሳሹን ለችሎት አቅርቧል።

‎ተከሳሹ የተከሰሰበትን ወንጀል ሙሉ በሙሉ በማመኑ፣ ፍርድ ቤቱ የአቃቤ ህግን ተጨማሪ ማስረጃ ሳይሰማ እሱንና መሰል ድርጊት ፈጻሚዎችን ለማስተማር በ14/11/2018 ዓ.ም. በተዋለው ችሎት ፈጣን ፍርድ (RTD) በመስጠት ተከሳሹን 1 ዓመት ከ8 ወር ቀላል እስራት፣ ለ2 ዓመት የእገዳ ቅጣት እና 15,000 (አስራ አምስት ሺህ) ብር ቅጣት እንዲከፍል መወሰኑን የጎሞሌ ወረዳ ፖሊስ የወንጀል መከላከል ክፍል ምክትል ኃላፊ ኢንስፔክተር ቱራ ዱባ አስታውቀዋል።

ያቤሎ፤ ሐምሌ 12/2018 (የቦረና ዞን ፖሊስ መምሪያ)በቦረና ዞን ፖሊስ መምሪያበቦረና ዞን ፖሊስ መምሪያ የሁለት ቀናት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ ተጀምሯል። በግምገማውም አዛዦች፣ አመራሮች፣ ...
19/07/2026

ያቤሎ፤ ሐምሌ 12/2018 (የቦረና ዞን ፖሊስ መምሪያ)

በቦረና ዞን ፖሊስ መምሪያ

በቦረና ዞን ፖሊስ መምሪያ የሁለት ቀናት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ ተጀምሯል። በግምገማውም አዛዦች፣ አመራሮች፣ የወረዳ አስተባባሪዎች፣ የፈጣን ምላሽ ኃይልና የሪፎርም ኃላፊዎች፣ እንዲሁም የመምሪያው አመራሮችና የስታፍ ክፍሎች ተሳትፈዋል።

ግምገማው ባለፈው ዓመት በተከናወኑ ሥራዎች ላይ በማተኮር የታዩትን ጠንካራ ጎኖችና ክፍተቶች በዝርዝር በመመርመር፣ ምክንያቶቻቸውን በመለየት እና ዘላቂ መፍትሄዎችን ለማስቀመጥ ያለመ ነው። በተጨማሪም ለወደፊቱ ሥራ ግልጽ ዕቅድና አቅጣጫ በማስቀመጥ የፖሊስ አገልግሎትን፣ የጸጥታ ሥራንና መልካም አስተዳደርን ለማጠናከር ውይይት በመካሄድ ላይ ይገኛል።

የቦረና ዞን ፖሊስ መምሪያ የተጣለበትን ኃላፊነት በታማኝነት፣ በግልጽነትና በውጤታማነት ለመወጣት፣ እንዲህ ዓይነት የሥራ ግምገማዎችን በየጊዜው በማካሄድ ያሉትን ክፍተቶች ለማረምና ጠንካራ ጎኖቹን የበለጠ ለማጠናከር በቁርጠኝነት ይሰራል።

18/07/2026
ያቤሎ፤ ሐምሌ 11/2018 (የቦረና ዞን ፖሊስ መምሪያ)የቦረና ዞን ፖሊስ መምሪያ የዱቡሉቅ ወረዳ ፖሊስ ጽሕፈት ቤትበ10/11/2018 ዓ.ም. ከቀኑ በግምት 12፡30 ሰዓት ላይ፣ የሕዝብ ማመ...
18/07/2026

ያቤሎ፤ ሐምሌ 11/2018 (የቦረና ዞን ፖሊስ መምሪያ)

የቦረና ዞን ፖሊስ መምሪያ
የዱቡሉቅ ወረዳ ፖሊስ ጽሕፈት ቤት

በ10/11/2018 ዓ.ም. ከቀኑ በግምት 12፡30 ሰዓት ላይ፣ የሕዝብ ማመላለሻ ሚኒባስ የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3/63588 O/R ከያቤሎ ከተማ ወደ ሞያሌ ከተማ በመጓዝ ላይ እያለ፣ በቅቤና መሪ ጋር ሃሺሽ ተብሎ የሚጠራ አደንዛዥ ዕፅ በድብቅ ጭኖ እያጓጓዘ እንደነበር ታውቋል።

ከህብረተሰቡ በደረሰ ጥቆማ መሰረት፣ የዱቡሉቅ ወረዳ ፖሊስ አባላት ፈጣን እርምጃ በመውሰድ በዱቡሉቅ ከተማ ከሊደት ምግብ ቤት ፊት ለፊት ተሽከርካሪውን በመከታተል በህግ ቁጥጥር ስር ማዋላቸውን የዱቡሉቅ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ ዋና ኢንስፔክተር. ጃርሶ ጉዮ ገልጸዋል።

የቦረና ዞን ፖሊስ ኮሚሽን ለህብረተሰቡ ንቁ ተሳትፎ ምስጋና በማቅረብ፣ ህብረተሰቡ ሕገወጥ ድርጊቶችን በሚያይበት ጊዜ በፍጥነት ለጸጥታ አካላት ጥቆማ መስጠቱ ወንጀልን በመከላከልና ዘላቂ ሰላምን በማረጋገጥ ከፍተኛ ሚና እንዳለው አሳስቧል።

17/07/2026
17/07/2026
17/07/2026
የቦረና ዞን ፖሊስ መምሪያ እና የቦረና ዞን ትራንስፖርት ኤጀንሲ በጋራ የተሽከርካሪ ቁጥጥርና ክትትል ሥራ አከናወኑያቤሎ፤ ሐምሌ 09/2018 (ቦ.ዞ.ፖ.መ)የቦረና ዞን ፖሊስ መምሪያ እና የቦ...
16/07/2026

የቦረና ዞን ፖሊስ መምሪያ እና የቦረና ዞን ትራንስፖርት ኤጀንሲ በጋራ የተሽከርካሪ ቁጥጥርና ክትትል ሥራ አከናወኑ

ያቤሎ፤ ሐምሌ 09/2018 (ቦ.ዞ.ፖ.መ)

የቦረና ዞን ፖሊስ መምሪያ እና የቦረና ዞን ትራንስፖርት ኤጀንሲ በቅንጅት በመስራት በመሬት ላይ የሚከናወነውን የተሽከርካሪ ቁጥጥርና ክትትል ሥራ ለማጠናከር ከ02/11/2018 እስከ 07/11/2018 ድረስ የዞን ደረጃ የሱፐርቪዥን ቡድን ወደሚከተሉት ወረዳዎች አሰማርቷል።

👉 ሞያሌ ወረዳ
👉 ሚዮ ወረዳ
👉 ያቤሎ ወረዳ
👉 ኤል-ወዬ ወረዳ

የሱፐርቪዥን ቡድኑ እንደ ራዳር (Radar) ያሉ ዘመናዊ የቁጥጥር መሣሪያዎችን በመጠቀም ሰፊ የተሽከርካሪ ቁጥጥር ሥራ አከናውኗል። ከሥራው በኋላም በቀረበው ሪፖርት የታዩ ጠንካራ ጎኖችና ድክመቶች ተለይተው በስፋት ተወያይተዋል።

ከታዩት ዋና ዋና ጉድለቶች መካከል፦

🚔 ከአቅም በላይ ጭነት (Overloading)
🚨 ከተፈቀደ የማቆሚያ ቦታ ውጭ ጭነት መጫንና ማራገፍ
🚑 ከተፈቀደው ፍጥነት በላይ ማሽከርከር
🚓 የደህንነት ቀበቶ (Seat Belt) አለመጠቀም
🏍 ያለፈቃድ ማሽከርከር
🚍 የሪፎርምና የጣቢያ መዝገቦችን በተሟላ ሁኔታ አለመያዝ

በተከናወነው ቁጥጥር አጠቃላይ፦

👉 ቅጣት የተወሰደባቸው ተሽከርካሪዎች፦ 161
👉 ለመንግሥት የተሰበሰበ ገቢ፦ 355,050 ብር

በመጨረሻም በሥራ ሂደት የታዩ ጉድለቶች ላይ በዞን ደረጃ ሰፊ ውይይት ተካሂዶ፣ የትራፊክ ቁጥጥርና የመጓጓዣ ደህንነት ሥራን ለማጠናከር ሁሉም ተቆጣጣሪዎች በቁርጠኝነት፣ በኃላፊነትና በሥነ ምግባር እንዲሠሩ የሥራ አቅጣጫ ተሰጥቶ መርሃ ግብሩ መጠናቀቁን የቦረና ዞን ፖሊስ መምሪያ የትራፊክ ደህንነት ክፍል ኃላፊ ኢንስፔክተር ሰለሞን ሞክነን ገልጸዋል።

Address

Borena, Oromia
Yabelo

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Qajeelcha Poolisii Godina Booranaa posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Qajeelcha Poolisii Godina Booranaa:

Shortcuts

Share