ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 09 አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት

  • Koti
  • Suomi
  • Lemi
  • ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 09 አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት

ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 09 አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት ትክክለኛ መረጃን ለህብረተሰቡ ተደራሽ እናደርጋለን

ቀን 01/03/2018"ወርቃማው ሰኞ ለወርቃማ ስኬቶች"ዛሬ ማለዳ ከመደበኛው የስራ ሰዓት አስቀድሞ የወርቃማው ሰኞ የዕውቀት ሽግግር ውይይት ተከናውኗል።     የወረዳ 09 አስተዳደር አመራሮች...
10/11/2025

ቀን 01/03/2018
"ወርቃማው ሰኞ ለወርቃማ ስኬቶች"

ዛሬ ማለዳ ከመደበኛው የስራ ሰዓት አስቀድሞ የወርቃማው ሰኞ የዕውቀት ሽግግር ውይይት ተከናውኗል።


የወረዳ 09 አስተዳደር አመራሮችና ሰራተኞች ሁለንተናዊ አንድነትን አጠናክሮ ወደ ተፈለገው ከፍታ ሊያሻግረን የሚያስችለውን የወርቃማው ሰኞ የዕውቀት ሽግግር የውይይት መድረክ "ወርቃማው ሰኞ ለወርቃማ ስኬቶች" በሚል መሪ ቃል ውይይት አድርገዋል።
በዛሬው የወርቃማው ሰኞ የዕውቀት ሽግግር መድረክ ላይ ያላቸውን የስራ ላይ ልምድና በሂወት ጉዟቸው ያካበቱትን የልምድ ልዉዉጥ በየተቋሙ በየሳምንቱ በተሚመረጡ ባለሞያዋች ቀርቦ የእዉቀት ሽግግር ተደርጎ ተጠናቋል።

ለሚ ኩራ ወረዳ 09 ፐ/ሰ/ሰ/ኃ/ል/ጽ/ቤት
01/03/2018

የአገልግሎት አሰጣጥ መማክርት ጉባኤ ተመሰረተ።**********************************************************************************በለሚ ኩራ ክ/...
07/11/2025

የአገልግሎት አሰጣጥ መማክርት ጉባኤ ተመሰረተ።
*****************************************
*****************************************
በለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 09 ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ጽ/ቤት የሚሰጠውን አገልግሎት ፈጣን ቀልጣፋና ተደራሽ ለማድረግ ‘’የአገልግሎት አሰጣጥ መማክርት ጉባኤ’’ መስርቷል።

የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ አስራት አምሳሉ የአገልግሎት አሰጣጥ መማክርት ጉባኤ መመስረት በየተቋማቱ ያለውን የአገልግሎት አሰጣጥ ቀልጣፋ በማድረግ የደንበኞችን እርካታ ከፍ እንዲል የሚረዳ መሆኑን አንስተው ከተገልጋይ፣ከሲቪክ ማህበራትና ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅርበት በመስራት ተጨባጭ ለውጥ ለማምጣት ትልቅ ሚና ያለው መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡

የአገልግሎት አሰጣጥ ድጋፍ ክትትል እና ምዘና ቡድን መሪ አቶ ነፃነት ጫኔ በበኩላቸው የመማክርት ጉባኤው በአገልግሎት አሰጣጥ ሂደት ላይ የተገልጋዮችን የባለቤትነት መንፈስ በማሳድግ በተቋማት የአገልግሎት አቅርቦትና በተገልጋይ ፍላጎት መካከል ያለውን ክፍተት ለመሙላት የሚያስችሉና የማስፈፀም አቅምን የሚያዳብሩ የመፍትሄ ሀሳቦችን በማመንጨት ለመተግበር የሚያግዝ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

በመጨረሻም ከጽ/ቤቱ፣ ከባለድርሻ አካላት፣ ከሲቪክ ማህበራትና ከተገልጋዩ ህብረተሰብ ከምክር ቤት የተወጣጡ 40 አባላትን የያዘ የመማክርት ጉባኤ የተመሰረተ ሲሆን ሰባት የስራ አስፈፃሚ ኮሜቴዎች ያሉት የመማክርት ጉባኤ ተመስርቷል፡፡

ለሚ ኩራ ወረዳ 09 ፐ/ሰ/ሰ/ኃ/ል/ጽ/ቤት
ጥቅምት 28/02/2018 ዓ/ም

በለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 09 ፐ/ሰ/ሰ/ኃ/ል/ጽ/ቤት የ2018 በጀት ዓመት ለመንግስት ሰራተኛች በተለያዩ ርዕሶች የአቅም ግንባታ ስልጠና ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው።በዛሬው እለት ለባለሙያዎች...
05/11/2025

በለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 09 ፐ/ሰ/ሰ/ኃ/ል/ጽ/ቤት የ2018 በጀት ዓመት ለመንግስት ሰራተኛች በተለያዩ ርዕሶች የአቅም ግንባታ ስልጠና ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው።

በዛሬው እለት ለባለሙያዎች ስልጠና መስጠት የተጀመረ ሲሆን ስልጠናው ለተከታታይ ሁለት ቀናት የሚቆይ መሆኑ ተገልጿል።

በዛሬው እለት ለባለሙያዎች የተሰጠ ያለው በካይዘን በቀን ውሎ አመዘጋገብ ጥራት ያለው እቅድ እና ሪፖርት አዘገጃጀት እንዲሁም በአዋጅ 87/2017 ዙሪያ ለ2ቀናት የሚቆይ ስልጠና መሰጠት ተጀመረ።

በስልጠናው መክፈቻ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የጽ/ቤቱ ሀላፊ አስራቱ አምሳሉ ይህ ስልጠና በአገልግሎት አሰጣጥ እና የተቋማትን እቅድና ሪፖርት በጥራት ተዘጋጅተው ተደራሽ ለማድረግና በዘርፉ የሚታዩ ክፍተቶችን ለመቅረፍ ትልቅ አቅም የሚፈጥር መሆኑን ገልፀዋል።

በመጨረሻም ስልጠናው ለተከታታይ 2ት ቀን የሚሰጥ ሲሆን በቀጣይም እንዲሁም ለሴት ፈፃሚዎች የሚሰጥ በመሆኑን በዲሲፕሊን መከታተል ያስፈልጋል ሲሉ ገልጿል ።

ወረዳ 09 ፐ/ሰ/ሰ/ኃ/ል/ጽ/ቤት
ጥቅምት 2018

05/11/2025
04/11/2025
04/11/2025
የእንጠያየቅ መድረክ በከተማችን የሚስተዋሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት እንዲሁም ለቀልጣፋ አገልግሎት መፍትሄ እንድናበጅና ልማታችንን እንድናሳልጥ ያስቻለ ትልቅ መድረክ መሆኑ ተገለ...
04/11/2025

የእንጠያየቅ መድረክ በከተማችን የሚስተዋሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት እንዲሁም ለቀልጣፋ አገልግሎት መፍትሄ እንድናበጅና ልማታችንን እንድናሳልጥ ያስቻለ ትልቅ መድረክ መሆኑ ተገለፀ።

በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የወረዳ 09 ፐብሊክ ሰርቪስ ጽ/ቤት ኮሙንኬሽን ፅ/ቤት የዋና ስራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት፣ በጋራ በመሆን የወረዳው ነዋሪ የተሳፈበት የአገልግሎት አሰጣጥ ፣ መልካም አስተዳደርና በልማት ላይ የእንጠያየቅ መድክ አካሂዷል።

በተካሄደው የእንጠያየቅ መድረክ ተገኝተው የመክፈቻ መልዕክት ያስተላለፉት የወረዳዉ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ምክትል ፓርቲና ፖለቲካ ዘርፍ ሃላፊ ወ/ሮ ጀምበር ተክሌ ከምናገለግለው ህዝብ ጋር ፊት ለፊት በመነጋገር የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በጋራ በመታገል የህዝባችንን ጥያዌ ምላሽ መስጠት ይገባል ያሉ ሲሆን ይህም የሚፈጠሩ ችግሮች ለማረም እንደሚጠቅም ተናግረዋል።

የወረዳው ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ሃላፊ ወ/ሮ ሰብለ ተዘራ እንደገለፁት እንጠያየቅ መድረክ መንግስትና ህዝብን ከሚያለያዩ ኃሳቦችን ችግሮችን ፊት ለፊት በመነጋገር ለችግሩ መፍትሄ በማምጣት የበለጸገች ኢትዮጺያን እውን ለማድረግ እንደሚጠቅም ገልጸዋል።

የወረዳዉ ፐ/ሰ/የሰ/ሀ/ለማት ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ አስራት አምሳሉ የእንጠያየቅ መድረኩ ህብረተሰቡ ለሚያነሳቸው ጥያቄዎች ምላሽ እንዲያገኝ እድል የሚሰጥ ብቻ ሳይሆን ቀጣይ እንዴት መስተካከል እንዳለበት አቅጣጫ የሚያስቀምጥ ነው ብለዋል።

አክሎም የእንጠያየቅ መድረክ በወረዳው ላሉ የመልካም አስተዳደር ፣ የአገልግሎት አሰጣጥ እና የልማት ችግሮችን መቅረፍ የሚያስችል እንዲሁም የግልፀኝነት ክፍተቶችን የሚሞላ በመሆኑ ተጠናክሮ የሚቀጥል ተገልጿል።

የውይይቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው የእንጠያየቅ መድረክ ለችግሮቻችን የጋራ መፍትሄን እንድናበጅና ልማታችንን እንድናሳልጥ የሚያስችለን በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አሳስበዋል።

ጥቅምት 2018 ዓ.ም
ለሚ ኩራ ወረዳ 09 ፐ/ሰ/ሰ/ሀ/ል/ጽ/ቤት

የወርቃማው ሰኞ የእውቀት  ሽግግር የውይይት መድረክ በወረዳ 09 አስተዳደር በደመቀ መልኩ ተካሆደ።በለሚ ኩራ ክ/ከተማ  ወረዳ 09 አስተዳደር ዘወትር ሰኞ ማለዳ የሚካሄደውንና ሁሉም ተቋማት ...
03/11/2025

የወርቃማው ሰኞ የእውቀት ሽግግር የውይይት መድረክ በወረዳ 09 አስተዳደር በደመቀ መልኩ ተካሆደ።

በለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 09 አስተዳደር ዘወትር ሰኞ ማለዳ የሚካሄደውንና ሁሉም ተቋማት ከሰራተኞች ጋር የእርስ በርስ ተሞክሮ የሚለዋወጡበትንና የሚማማሩበትን የወርቃማው ሰኞ የእውቀት ሽግግር በወረዳዉ በሁሉም ተቋማት በድምቀት ተካሂዷል ።

የወርቃማው ሰኞ ውይይት መጀመር በሰራተኞች መካከል ያለውን ትስስር በማጠናከር በአገልግሎት አሰጣጥ ጥራትና ቅልጥፍና ላይ አወንታዊ ለውጦችን እያመጣ በመሆኑ ይበልጥ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት በአስተዳደሩ የሚገኙ ባለሞያዎች ገልጸዋል ።

ለሚ ኩራ ወረዳ 09 ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት

ጥቅምት 24/2018 ዓ.ም

በለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 09 አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት የ2018 በጀት ዓመት የሴክተሮች የ1ኛ ሩብ ዓመት የዝግጅት ምዕራፍ ስራዎች ያለበት ደረጃ ድጋፍ ማካሄድ...
16/10/2025

በለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 09 አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት የ2018 በጀት ዓመት የሴክተሮች የ1ኛ ሩብ ዓመት የዝግጅት ምዕራፍ ስራዎች ያለበት ደረጃ ድጋፍ ማካሄድ ጀመረ።

*******************
ለሚኩራ ወረዳ 09 አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስና ሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት
ጥቅምት 6/2018 ዓ.ም

የለሚ ኩራ ክ/ከ ወረዳ 09 አስተዳደር የፐብሊክ ሰርቢስ እና የሰዉ ሀብት ልማት ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ አስራት አምሳሉ እንደገለጽት የድጋፍ ክትትሉ ሁሉንም ሴክተር መስሪያ ቤቶች ያካተተ መሆኑን ገልጸዉ ይህም ለተከታታይ አራት ቀናት የሚቆይ መሆኑን ጠቁመዋል ።

13/10/2025

ስኬቶቻችን የሰንደቃችን ከፍታ የሚጨምሩ ናቸው

ኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት የለውጥ ዓመታት እመርታዊ ስኬቶችን እያስመዘገበች የሚመጥናትን ከፍታ እየያዘች ትገኛለች። ለዘመናት የቁጭት እና እንጉርጉሮ ትርክት ምንጭ የነበረዉን ዓባይን ገርታ የኃይል እና ብርሃን ምንጭ አድርጋለች፡፡

በንጋት ኃይቅ በምግብ ሉዓላዊነቷ ላይ ጉልህ ሚና የሚጫወት የዓሣ ምርት ማግኘት ችላለች፤ ዐዲስ የቱሪዝም መዳረሻ ደሴቶችንና ከተሞችን ፈጥራለች፡፡ የዓባይን የቁጭት ትርክት ወደ ድል እና አሸናፊነት ብስራት ቀይራለች፡፡

ተጨማሪ የኃይል ምንጮችን ከውኃ እስከ እንፋሎት፣ ከፀሐይ ብርሃን እስከ ኑውክሊየር ኃይል እና ነፋስ በመገንባት ላይ ናት፡፡ እነዚህ ሁሉ የሰንደቋን ከፍታ እና ተምሳሌትነት የሚያጎሉ ናቸው፡፡

ኢትዮጵያ ከገጸ ምድር ባሸገር በከርሰ ምድር ያሉ ሀብቶቿን ወደመጠቀም ተሸጋግራለች፡፡ በተፈጥሮ ጋዝ ማውጣት የታየዉን ስኬት ለማላቅ፣ በነዳጅ ዘይትም ለመድገም ግዙፍ ፕሮጀክቶችን ጀምራለች፡፡ የግብርና ዘርፉን ውጤታማነት ለማሳደግ የዐፈር ማዳበሪያ በራሷ ለማምረት ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሳለች፡፡ ይህም የምግብ ሉዓላዊነታችንን ለማረጋገጥ የተጀመረውን ሥራ ይበልጥ የሚጠናክር ሆኗል።

የሕዝቧን የአኗኗር ዘይቤ ለመቀየር ከቢሮ እስከ ግቢ በሚል ጀምራ፣ ከከተማ እስከ ገጠር ወደሚል ተሸጋግራለች፡፡ በአዲስ አበባ የተጀመረዉ የከተሞችን ገጽታ የመቀየር ንቅናቄ ዘመናዊነትን፣ የስማርት ሲቲ ጽንሰ ሐሳብን እና ሰውን ከተፈጥሮ የማስማማት ልምምድን ያስተዋወቀ ነው፡፡ ይህም የዲፕሎማሲ ማእከል የሆነችውን መዲናችንን በዓለማቀፍ ደረጃ ያላትን ገጽታ የሚያጎላ፣ የሰንደቃችንን ከፍታ የሚጨምር ነው፡፡

ከተማችንን የማዘመኑን ጅማሮ ወንዞቻችን በማከም የተፋሰሶችን ደኅንነት የሚያረጋግጥ ሆኗል፡፡ ከእንጦጦ ጀምሮ እየተሠራ ያለዉ የወንዞች ዳርቻ ልማት የአዋሽ ተፋሰስን ሥነ ምኅዳር ጭምር የሚያክም ለአካባቢ ጥበቃ አብነት ነው፡፡ የገጠር አኗኗር ዘይቤያችንን በማዘመን ኢትዮጵያን በበጎ የምትመሰል ሀገር የማድረግ ጥረታችንም ፍሬው እየታየ ነው፡፡ እነዚህ ሁሉ የሰንደቃችንን በኩራት መውለብለብ የሚያጎሉ የትጋታችን ውጤቶች ናቸው፡፡

ዛሬ የምናከብረው የሰንደቅ ዓላማ ቀን በነፃነት ቀን የተገኘ አይደለም፤ ነፃ ሆኖ ለሌሎች ነፃነት ከፍ ብሎ ሲውለበለብ የታየ የነፃነት ምልክት እንጅ፡፡ ነፃነቱን ለማስከበር ግን ቀደምቶቻችን ደም፣ ሥጋ እና ዐጥንት ገብረዋል፡፡ ኢትዮጵያን የዓለም የነፃነት ቀንዲል አድርገዉ አስረክበውናል፡፡

ዛሬም እንደትናንቱ የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት በደም እና በዐጥንት ለማስበር የቆረጡ ጀግኖች አሉን፡፡ በምድር፣ በአየር፣ በባሕር እና በሳይበር የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት በማስከበር ሰንደቋ የነፃነት ተምሳትነቱ እንዲቀጥል የሚተጉ ጀግኖቻችን አሉ፡፡

የሰንደቅ ዓላማ ቀንን የምናከብረዉ በሁሉም ግንባር፣ በሁሉም ዓውድ ስለኢትዮጵያ ዋጋ የሚከፍሉ ጀግኖቻችን በማመስገን፣ ሰንደቃችንም በክብር ከፍ አድርገን በማውለብለብ፣ ለላቀ ከፍታዉ እንደምንተጋ ቃል በመግባት ነው፡፡ የተጀመሩ ትልልቅ የሰንደቅ ዓላማ ፕሮጀክቶች ለማሳካት ደግሞ ያለስስት በጋራ መጣር፣ የኢትዮጵያን ብልጽግና እውን ለማድረግ ማናቸዉንም ዋጋ መክፈል ከዜጎች ይጠበቃል፡፡

እንኳን ለሰንደቅ ዓላማ ቀን አደረሳችሁ!

የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
ጥቅምት 3/2018 ዓ/ም

Osoite

Addis Ababa
Lemi
2098

Hälytykset

Tiedä ensimmäisenä ja anna meille oikeus lähettää sinulle sähköpostitse uutisia ja promootioita ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 09 አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት :ltä. Sähköpostiosoitettasi ei käytetä muihin tarkoituksiin, ja voit perua milloin tahansa.

Ota Yhteyttä Organisaatio

Lähetä viesti ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 09 አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት :lle:

Jaa